Get Mystery Box with random crypto!

ዘማሪ ዲ/ን ፍፁም ከበደ

የቴሌግራም ቻናል አርማ zdfitsumkebe — ዘማሪ ዲ/ን ፍፁም ከበደ
የቴሌግራም ቻናል አርማ zdfitsumkebe — ዘማሪ ዲ/ን ፍፁም ከበደ
የሰርጥ አድራሻ: @zdfitsumkebe
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 22.71K
የሰርጥ መግለጫ

ዘማሪ ዲያቆን ፍፁም ከበደ

Ratings & Reviews

5.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

2

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 9

2022-11-27 21:44:38 ስለ ምን ማወቅ ይፈልጋሉ
ስለ ስርአተ ቤተክርስቲያን:ስለ ምስጢረ ቁርባን፡ መንፈሰዊ ምክር፡ታሪክ የየእለቱ ስንክሳር ፡ የሚዘከርበት ፍፁም ኦርቶዶክሳዊ ቻናል። ናታኒም ቲዩብ
መቼ ነው ፍጹም ክርስቲያን የምትሆኑት ጊዜያችሁን አታባክኑ አሁኑኑ join ብላችሁ መንፈሳዊ ሰው ሁኑ ክርስቲያን መንፈሳዊ ሰው ነው



𝐉𝐎𝐈𝐍 𝐔𝐒
691 views✞£iŧsûm✞, 18:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-27 21:44:01
እንኳን ደስ አላችሁ በዩቲዩብ የምናውቀው #ማኅቶት_ቲዩብ አሁን ደግሞ በቴሌግራም መጥታል ለመቀላቀል ከስር Join የሚለውን ንኩት።

https://t.me/+SLPMr-p0D_QzRyzI
336 views✞£iŧsûm✞, 18:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-26 22:01:18 አዲስ የንስሐ ዝማሬ "የመዳን ቀን ዛሬ" በዘማሪ ዲ/ን አክሊሉ

ናታኒም ቲዩብ SUBSCRIBE በማድረግ አገልግሎቱን ይደግፉ ናታኒም ማለት የእግዚአብሔር ቤት ጠራጊ ታናሽ አገልጋይ ማለት ነውና።


498 viewsማኔ ቴቄል ፋሪስ, 19:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-26 21:21:53
እንኳን ደስ አላችሁ በዩቲዩብ የምናውቀው #ማኅቶት_ቲዩብ አሁን ደግሞ በቴሌግራም መጥታል ለመቀላቀል ከስር Join የሚለውን ንኩት።

https://t.me/+SLPMr-p0D_QzRyzI
126 views✞£iŧsûm✞, 18:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-26 21:21:53
.

ለፕሮፋይል ፒክቸር የሚሆኑ መንፈሳዊ ፎቶዎችን ማግኘት ይፈልጋሉ መልሶት አዎ ከሆነ ከስር ያለውን ሊንክ በመጠቀም ማግኘት ይችላሉ


https://t.me/+YkS5xznutqNjZTE0
https://t.me/+YkS5xznutqNjZTE0
https://t.me/+YkS5xznutqNjZTE0
97 views✞£iŧsûm✞, 18:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-26 18:32:05 ትክክለኛ ወቅታዊ ኦርቶዶክሳዊ መረጃ ማግኘት ይፈልጋሉ?
የተለያዩ የአውደምህረት ዝማሬ፣ ስብከት
ወቅታዊ የቤተክርስቲያን መረጃ
የቅዱሳን እና የገዳማት ታሪኮች
እነዚህን ለማግኘት ከስር ያለውን ሊንክ በመጫን እና ሰብስክራይብ በማድረግ ቤተሰብ እንሁን

subscribers subscribers
subscribers subscribers




970 viewsማኔ ቴቄል ፋሪስ, 15:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-26 16:08:09 ወደ ምስራቅ ተመልከቱ ማለት ምን ማለት ነው ??

በኦርቶዶክስ ተዋህዶ ሀይማኖታችን ቤተክርስቲያን የምትታነፀው ምስራቁን አቅጣጫ ጠብቃ ነው እዲሁም ከቤተክርስቲያኑ ጋር አብሮ የሚሰራው ቤተልሄም በስተምስራቅ በኩል ይደረጋል በፀሎት ሰዓትም ወደምስራቅ ዞረን ነው የምንፀልየው በስረአተ ቀብር ላይም የሞተ ሰው ሲቀበር ራሱ ወደ ምዕራብ እግሩ ወደ ምስራቅ ሆኖ ይቀበራል ሌላው ዲይቆኑ በስረአተ ቅዳሴው ላይ ወደምስራቅ ተመልከቱ ይላል ለምን ይሆን ?



፦ የአዳም አባታችን ጥንተ ርስት ገነት በምስራቅ ናት። ዘፍ 2፥8 ይች እርስታችን በአዳም በደል ምክኒያት በኪሩቤል ሰይፍ ተዘግታ ስትኖር ሞትን ድል አድርጎ በበደልን ክሶ ጌታችን መዳህኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በሞቱ ከፈተልን ሉቃ 23፥43 ወደምስራቅ በዞርን ቁጥር ወደገነት ለመግባት የተሰጠን ተስፍ ትዝ ይለናል የተከፈተችውም ቤታችን ገነት በእምነት ወለል ብላ ትታየናለች በክርስቶስ ያገኘነውን ፀጋ እናስባለን ምድራውያን አለመሆናችንም ይታወሰነል።



፦ጌታ የተወለደው በምስራቅ ነው። ሰብዓሰገል ኮከቡን ያዩት በምስራቅ ሲሆን ያኮከብ የምህረተ እግዚአብሄር ምሳሌ ነው እነርሱን ወደ እግዚአብሄር እዳደረሳቸው ሁሉ እኛንም ወደ ለመለመው መስክ ይመራናል ማቴ 2፥2 መዝ 22፥14 ወደ ምስራቅ በዞርን ቁጥር የጌታ መወለድ እና ያደረገልን ውለታ ይታወሰናል የምህረቱ ኮከብ እየመራን መሆኑ ትዝ ይለናል ።



፦ ምስራቅ የእመቤታችን ምሳሌ ነው። ከምስራቅ ጨለማውን የሚገፈው ፀሀይ እደሚወጣ ሁሉ ከእመቤታችን ከድንግል ማርያምም የአለምን የሀጥያት ጨለማ የሚገፍ ፀሀዬ ፅድቅ ኢየሱስ ክርስቶስ ወጥቶል (ተገኝቱል) ለእናንተ ስሜን ለምትፈሩ የፅድቅ ፀሀይ ትወጣላችሁለች ሚል 4፥1 ህዝ 44፥1፦4 ነብዩ ህዝቅየልም እመቤታችንን ያያት በምስራቅ ነው ስለዚህ ወደ ምስራቅ በዞርን ቁጥር እመቤታችን ትዝዝዝ ትለናለች የፅድቅ ፀሀይ ክርስቶስ ስለተወለደልን በጨለማ አለመሆናችን ትዝ እያለን ከሀጥያት እንርቃለን።



፦ የአለም ድህነት የተገኘው በምስራቅ ነው ። ጌታ የተሰቀለው እና አለምን ያዳነው በምስራቅ ነው እየሩስ አሌም ምስራቃዊት ከተማናት እና በመሆኑን ወደ ምስራቅ በዞርን ቁጥር የተሰቀለውን ክርስቶስን እና የተከፈለልንን ዋጋ እናስባለን።



፦ክርስትናና ቤተክርስቲያን የተመሰረቱት በምስራቅ ነው። የመጅመሪያው ቤተክርስቲያን የተመሰረተው በእየሩስ አሌም ሲሆን ወንጌል የተሰበከውም ከዚሁ በመነሳት ነው ።ስለዚህ ወደምስራቅ ስንዞር የቤተክርስቲያን ጉዞ የወንጌል መስፍፍት ና የህዝበ አለም መዳን ትዝ ይለናል።



፦ ምስራቅ የእግዚአብሄር ክብር መገለጫ ነው ። ኢሳ 28:13 እግዚአብሄርን በምስራቅ የእስራኤልንም አምላክ የእግዚአብሄርን ስም በባህር ደሴቶች አክብሩ ህዝ 43፦2 የእስራኤል አምላክ ክብር ከምስራቅ መንገድ መጣ።



~የጌታ ዳግም ምፅአትም ከምስራቅ ነው። ዘካ 14፥14 በዚያን ቀን እግሮቹ በእየሩስ አሌም ትይዩ በምስራቅ በኩል ይቆማሉ ሐዋ 1፦11 ይህ ከእናንተ ወደሰማይ የወጣው ኢየሱስ ወደሰማይ ሲርግ እዳያችሁት እንዲሁ ይመጣል ።
• ፦ ቅዱሳን አበው ሲፀልዩ ወደ ምድራቅ ይዞሩ ነበር ዳን 6፥9 ወደ እየሩስ አሌም ያለውን መስኮት ከፍቶ ይፀልይ ነበረ ነብዩ ዳንኤል እግዚአብሄር ምሉዕ በኩልሄ (የሌለበት ቦታ የሌለ) መሆኑን ያውቃል። ነገርግን ወደ እየሩስ አሌም መዞሩ ነፍሱ የምታስባት እዲኖራት ነው ።



፦ ታቦቱ በምስራቅ በኩል ባለው ቤተ መቅደስ አስቀምጠን ስጋወ ደሙ የሚፈተተው ጌታ በምስራቅ ሀገር ጎለጎታ ለኛ ስጋውን መቁረሱ ደሙን ማፍሰሱበማሰብ ነው ።

ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ወወላዲቱ ድንግል
ወለመስቀሉ ክቡር
አሜን!
2.3K views✞£iŧsûm✞, edited  13:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-25 23:24:08 +++ "ጌታ ሆይ አሰናብትልን" +++

ጌታ ሠላሳ ዓመት በምድረ በዳ የኖረ የዮሐንስ መጥምቅን ሞት በሰማ ጊዜ በታንኳ ወደ ምድረ በዳ ፈቀቅ ብሎ ሄደ። ብቸኛ ሆኖ ኖሮ የሞተውን ሰው ኃዘን ብቻውን ሆኖ ሊወጣ ወደ በረሃ ተሳፈረ። ነገር ግን የእርሱን መሄድ የሰሙት ሕዝቡ ብቻውን እንዲሆን አልተውትም። እርሱ በታንኳ ቢሄድ እነርሱ በእግር ተከትለውት መጡ። ጌታችንም ጠባቂ እንደ ሌለው መንጋ የሆኑትን ሕዝብ በፊቱ ባየ ጊዜ አዘነላቸው። እስኪመሽም ድረስ አስተማራቸው፤ ድውዮቻቸውንም ፈወሰ።

ታዲያ በዚህ መካከል የአገልግሎቱ አስተባባሪ የነበሩት ሐዋርያትን አንድ ነገር አሳሰባቸው፤ "ይህ ሁሉ ሕዝብ ምን ሊበላ ነው?" የሚለው የምግብ ጉዳይ። ይህን ጥያቄያቸውን ይዘው ወደ መድኃኒታችን መጡና "ቦታው ምድረ በዳ ነው አሁንም ሰዓቱ አልፎአል፤ ወደ መንደሮች ሄደው ለራሳቸው ምግብ እንዲገዙ ሕዝቡን አሰናብት" አሉት።(ማቴ 14፥15) ጌታችንም "አይይ ይህን የመሰለ ቃለ እግዚአብሔር ሲመገቡ አምሽተው እናንተ ስለ ምግብ ትጨነቃላችሁ? ባይበላስ?" ብሎ አላሳፈራቸውም። እርሱ የነፍስም የሥጋም ፈጣሪ ነው። በእለተ ማግሰኞ ለምግበ ሥጋ የሚሆኑ አዝርእትና ፍራፍሬን የፈጠረ አምላክ እንዴት የሰውን ረሃብ ቸል ይላል? ስለዚህም ለሐዋርያቱ "እናንተ የሚበሉትን ስጡአቸው እንጂ ሊሄዱ አያስፈልግም" አላቸው።(ማቴ 14፥16) ደቀ መዛሙርቱም ያለን ጥቂት ነው። ከሁለት ዓሣና ከአምስት እንጀራ በቀር ምንም የለንም አሉ።

ከሐዋርያቱ ጥያቄ እንደምንረዳው የምግብ ጭንቀታቸውን ያባባሰው አንደኛ ቦታው ምድረ በዳ መሆኑ፣ ሁለተኛ ደግሞ ሰዓቱ ማለፉ (መምሸቱ) ነው። ሙት ሲያስነሣ፣ ድውይ ሲፈውስ ያዩትን መምህራቸውን ምንም እንደ ቀደሙ አባቶቻቸው "እግዚአብሔር በምድረ በዳ ማዕድን ያሰናዳ ዘንድ ይችላልን?" ብለው ባያሙትም፣ በምድረ በዳ ሕዝቡን ይመግባል ብለው ግን አላመኑበትም ነበር።(መዝ 78፥19) አብሯቸው ያለው ጊዜ እና ቦታ የማይወስነው የብርሃኑን ጊዜ ቀን፣ የጨለማውን ጊዜ ደግሞ ማታ ብሎ ስም ያወጣላቸው በሰዓታት ላይ የሰለጠነ አምላክ መሆኑን አላስተዋሉም ነበር። 

ክርስቶስ ሐዋርያቱን "እናንተ የሚበሉትን ስጧቸው" ብሎ ሲያዝዝ ደቀ መዛሙርቱ ጥቂት ብቻ እንዳላቸው ሳያውቅ ቀርቶ አይደለም። ነገር ግን ቅዱስ ዮሐንስ ወንጌላዊ እንደሚነግረን እምነታቸውን ሊፈትን ነበር። በእርግጥም ፈተናቸው እንደ ጠበቀውም ዓይነት እምነት አላገኘባቸውም። "ያለን ጥቂት ነው" አሉት። ሐዋርያቱ ምን ያህል ቢይዙ ነበር አምስት ሺህ ሰው (ሴቶችና ሕፃናት ሳይቆጠሩ) መመገብ የሚችሉት? መቼም ቢሆን ለአምስት ገበያ ሕዝብ የሚሆን ምግብ ተሸክመው አይዞሩም። ስለዚህ አሁን ካላቸው አምስት እንጀራ እና ሁለት ዓሣ የሚበልጥ ምግብ ቢኖራቸው እንኳን ሕዝቡን ለማጥገብ የእግዚአብሔር በረከት ግድ ያስፈልግ ነበር። እነርሱ ያሰቡት በእጃቸው ያለውን ጥቂት ነገር እንጂ አብሯቸው ያለውን በብዙም በጥቂትም መሥራት የሚችለውን አምላክ አልነበረም። እርሱን ማሰብ ቢያስቀድሙ ኖሮ በጥቂቱ ነገር  አይጨነቁም በብዙውም ነገር አይኮሩም ነበር።

እኛስ እጃችን ላይ ያለውን ጥቂት ነገር ብቻ አይተን "አሰናብትልን" ያልንበት ጊዜ የለም? የምእመናኑ ጥያቄ እና የእኛ ዝግጅት አልመጣጠን ሲለን ጥቂቱን ነገር ማብዛት ወደሚችል አምላክ ቀርቦ ከመጠየቅ ይልቅ ስንት ጊዜ "ጌታ ሆይ አሰናብትልን?" እያል ከነገሩ ለመሸሽ ሞከርን? በትዳር ጉዳይ ምክር ፈልጌ ነበር? "ጌታ ሆይ አሰናብትልን?"፣ ልጆቼን እንዴት ላሳድግ? -"ጌታ ሆይ አሰናብትልን?"፣ ኑሮዬን መምራት ቸግሮኛል -"ጌታ ሆይ አሰናብትልን?"፣ ከሱስ እንዴት ልላቀቅ -"ጌታ ሆይ አሰናብትልን?"...

እግዚአብሔር ከሰው ብዙ አይፈልግም። እጅህ ላይ ያለው ጥቂት ነገር ይበቃዋል። ለአምስት ሺህ ሕዝብ አምስት እንጀራን፣ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩትን ሕዝብ ባሕረ ኤርትራን ለማሻገር አንድ የሙሴን በትር፣ አንድ ሺ ፍልስጥኤማውያንን ለመግደል አንድ የአህያ መንጋጋ ተጠቅሞ ድንቅ ሥራውን አሳይቶናል። ጥቂቱን ነገር ሲጠይቅህ እርሱን ለማቅረብ ወደ ኋላ አትበል። እርሱ ማብዛት፣ ማበርከት፣ ለብዙ ሕዝብ፣ ለብዙ ጉባኤ ማድረግን ያውቅበታል።

በዲያቆን አቤል ካሳሁን


https://t.me/akanim1wasen2
948 viewsወሰንየለው ባህሩ, 20:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-25 16:50:00 ~ ርቱዕ ተፈጥሯዊ ሕግ ~ (the natural law)

~ ወንጌል  ኦሪት እና ቁርኣን ~
                      ምን ዓይነት ሕግጋት ናቸው ~?

ክፍል-2

ርቱዕ ተፈጥሯዊ ሕግ ፦ (the natural law) ደግሞ የወንጌል ሕግ እስኪሰጥ ድረስ መዘጋጃ ሆኖ የተሰጠ እና ሰዎች ፍትሕን እና የክፋት ውጤትን በመፍራት መልካምነትን እየተከተሉ ይ'መሩበት ዘንድ(በዋናነት በሙሴ አማካነዠኝነት ለአብርሃም ልጆች ለእስራኤላውያን)የተሰጠ ሕግ ነው። ይህ ርቱዕ(ፍትሕ ያለበት)ሕግ ነው።
ይህ ሕግ ሰው የገደለ ራሱም ይገደል የሰረቀ እጁ ይቆረጥ ዓይን ያጠፋ አይኑ ይጥፋ ወ.ዘ.ተ የሚሉ ትዕዛዛትን የያዘ ሰዎች በሰማይ ብቻ ሳይሆን በምድር ላይ ጭምር የሚያጋጥማቸውን ቅጣት በመፍራት ሕግጋትን እንድያከብሩ ለማድረግ የተሰጠ የኦሪት ሕግ ነው።ዓለማውያን ሕግጋትም ወደዚህ ሰለሚቀርቡ አል-ኪንዲ ተፈጥሯዊ ሕግ(natural law) ይለዋል።

የሁለቱንም በሙሴ እና በክርስቶስ የተሰጡ ሕግጋት ግኑኝነት በማብራራት በክርስቶስ ሰው መሆን የተሰጠው የወንጌል ሕግ ከኦሪት ሕግ ይልቅ ፍጽምና ያለው በመሆኑ የወንጌሉ ሕግ የቀደመውን የኦሪት ሕግ ፍጹም አድርጎታል ከወንጌል በኋላ እንደገና ወደ ኦሪት ሕግ መመለስ አይገባም-ክርስቲያን ሊቃውንት ከእነዚህ መካካል የፓትርያርክ ጢሞቴዎስ ሐተታ ተጠቃሽ ነው።
ጢሞቴዎስ የቀደመው የኦሪት ሕግ(ተውራት) ምድራዊ ነገሮች ይበዙበት የነበር እና በክርስቶስ ሰው ሆኖ መምጣት ስለሚሰጠው ሰማያዊ ጸጋ የተስፋ ትንቢት የተነገረበት እንደነበር ያስረዳል።

በክርስቶስ የተሰጠች ወንጌል የዚህ ተርፋ ፍጻሜ ስለሆነች ሰማያዊ ጸጋ እና ፍቅርን የምታዝዝ እንጂ እንደ ኦሪት ምድራዊ አስተዳደርን የጦርነት ገድልን ሥጋዊ ሥርዓቶችን የምታዝዝ አይደለችም።

በመሆኑም የእግዚአብሔር ሕግጋት አሠራር(ከኦሪት ወደ ወንጌል የተደረገው ጉዞ ከምድራዊ ወደ ሰማያዊ ከጊዜያዊ ወደ ዘላለማዊ እሴቶች የተደረገ በመሆኑ ከዚህ በኋላ ስለ ምድራዊ ነገሮች ወደ ሚወስድ ሕግ መመለስ አይገባም ይህ ከእግዚአብሔር አይደለም እግዚአብሔር ያስጀመረውን ጉዞ ያስጨርሳል እንጂ ቀዠወደ ኋላ አይመልስምና-ይላል ጢሞቴዎስ።

በ15ኛው መ/ክ/ዘመን የተነሱ ስፔናውያን የምዕራብ ቤተክርስቲያን ሊቃውንትም ተመሳሳይ ሐሳብ አንሥተዋል። ከእነዚህ አንዱ ጴጥሮስ አልፎንሲ እንደሚለው የእስልምናው ነብይ ሙሐመድ የእስልምናን ሕግ ያዘጋጀው ተወግዘው ወደ ዐረብ የሸሹ ክርስቲያን መናፍቃን እና አይሁድ እያማከሩት እንደሆነ ጽፏል።በመሆኑም ሁሉም የራሳቸውን አስተምህሮ የሚያንጸባርቅ አስተምህሮ በማስገባታቸው የእስልምና ሕግ የክርስትና እና የሚሙሴ ሕግ ቅልቅል እንደሆነ አንዳንድ ቦታዎች ላይ ደግሞ በሁለቱ መካካል የቆመ እንደሆነ ያትታል።

ይቀጥላል ........

(~የልቦና ችሎት~ "በረከት አዝመራው")
1.9K views✞£iŧsûm✞, edited  13:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-25 10:06:32
~አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ~
981 views✞£iŧsûm✞, edited  07:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ