Get Mystery Box with random crypto!

ዘማሪ ዲ/ን ፍፁም ከበደ

የቴሌግራም ቻናል አርማ zdfitsumkebe — ዘማሪ ዲ/ን ፍፁም ከበደ
የቴሌግራም ቻናል አርማ zdfitsumkebe — ዘማሪ ዲ/ን ፍፁም ከበደ
የሰርጥ አድራሻ: @zdfitsumkebe
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 22.71K
የሰርጥ መግለጫ

ዘማሪ ዲያቆን ፍፁም ከበደ

Ratings & Reviews

5.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

2

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 12

2022-11-19 22:17:22
እንደዚህ ውብ የሆኑ የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ስዕሎችንና ፎቶዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉ

https://t.me/+YkS5xznutqNjZTE0
https://t.me/+YkS5xznutqNjZTE0
275 views✞£iŧsûm✞, 19:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-19 08:24:30 ፓይስዮስ Paisios "ነፍሳችን በውስጧ የሚነሡትን ሐሳቦች ሳትቆጣጠር ግድ የለሽ ኾና ከኖረች፥ በቆሸሹና አታላይ በኾኑ ሐሳቦች የምትመላ ትኾናለች።" ስለዚህ የልልና የቀሊል ሐሳብ መነሻው ይሄ ግድየለሽነት ነው። ብዙ ማስመሰሎችና ርኩስ ድርጊቶች የሚተገበሩትም በግድየለሽነት ግንድ ላይ በቅለው ነው። ስለ ሃይማኖትና ሃይማኖታዊ ሥርዓትም ከጥልቃችን የማይሰማን በግድየለሽነት ሕማም በጽኑ ስለ ተጎዳን ነው። ሐሳባችንም ጠባብና ሌሎች ሰዎችን አላስገባ ያለው በዚህ ሕማም ከመታመማችን የተነሣ ነው። ወዳጄ ሆይ የክርስቲያን ሐሳብ እንደ ቅዱስ ጳውሎስ ሰፊና ኹሉን መያዝ የሚችል መኾን እንዳለበት ልብ ብለህ አስተውል። ቀጥለህ ደግሞ የሕማምህን የጉዳት መጠን ለመረዳት የአንተን የሐሳብ ጥበት አስተውል። እንኳን ለሌላው ለራሳችን ራሱ የራሳችን ሐሳብ ጠባብ እስኪኾንብን ድረስ በጽኑ ታመናል።

መፍትሔው ወደ ፍቅር መመለስ ነው። ከሽንገላና ከማስመሰል ሕይወት መላቀቅ ነው። ሌሎችን ከልብ መውደድና ማክበር ነው። ሌሎችን ውስጣችን እስካላስገባን ድረስ በሌሎቹ ውስጥ መግባት አንችልም። በፍቅር ሌሎችን እኛ ውስጥ ስናደርግ እነርሱ ደግሞ እነርሱ ውስጥ እኛን ያገኙናል። አእምሯችን ለሁሉ የሚኾን ወደ መኾን እጅግ ማደግ አለበት። ፍቅር የአእምሮን ጥበት የሚያፈርስ ኃይል ነው። በፍቅር ውስጥ ለመግባት ልምምድ ከጀመርን አእምሯችን ሁሉ ገብቶ የሚኖርበት የሰላም ከተማ ኾኖ እናገኘዋለን። ያኔ ልክ እንደ ገነት ከአእምሯችን ለዓለም የሚኾን የሰላም ውኃ ይፈልቃል። ዓለምን በፍቅር ውስጥ ከትተን ከጥበቷ እንገላግላታለን። ኦርቶዶክሳዊ መኾን ማለት ይህ ነው። በርቱዕ ፍቅር ውስጥ ገብቶ ሌሎችንም ወደዚያ ማስገባት። ከሰዎች ሕሊና ውስጥ የጠባብነት ሐሳቦችን መንቀል፤ በክርስቶስ ፍቅር ውስጥ ገብተው እንዲያርፉ ማስቻል፤ ይህ ነው ኦርቶዶክሳዊነት።

(~ዲ/ን ዮሐንስ ጌታቸው~)
1.2K viewsሞቱማ ቸርነት, edited  05:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-18 22:23:58 ስለ ሀይማኖቴ ማወቅ ግዴታዬ ነው የሚል ሊቀላቀሉት የሚገባ ቻናል ነው።
በቻናሉ ጥያቄ ይጠየቃል ምዕመኑም ይሳተፋል
ቻናሉን ለመቀላቀል)

ቤተ ክርስቲያን ከሕግ በላይ ናት
ኢየሱስ ክርስቶስ የሕግ ፍጻሜ ነው ማለት ምን ማለት ነው
ሕግ መቼ ተመሠረተ
ለምንስ ተመሠረተ

@EOTC_-OPEN_channel
@EOTC_-OPEN_channel
@EOTC_-OPEN_channel
482 views✞£iŧsûm✞, 19:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-18 22:23:39
እንደዚህ ውብ የሆኑ የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ስዕሎችንና ፎቶዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉ

https://t.me/+YkS5xznutqNjZTE0
https://t.me/+YkS5xznutqNjZTE0
227 views✞£iŧsûm✞, 19:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-18 07:55:16 (ከማሁኬ ፡ ይብራህ ፡ ብርሃን ክሙ ፡ በቅድመ ሰብእ። ) መልካም ስራቹሁን አይተው በሰማያት ያለውን አባታቹሁን እንዲያከብሩ ብርሃናቹሁ እንዲሁ በሰው ፈት ይብራ (ማቴ 5:16) ። በተራራ ላይ የታነጸች መንደር ልሰወር ብትል መሰወር አንዳይቻላት የተራራው ከፍታ እንዲገልጻት ። በመቅረዝ ላይ ያለች ፍና ልሰወር ብትል መሰወር እንዳይቻላት የመቅረዙ ከፍታ እንደገልጻት እናንተም ስራውን አብዝታቹሁ ስሩ በተአምራት ይገልጽላቹሀል ።
405 views✞£iŧsûm✞, 04:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-17 10:04:20
~የዲላ ፍሬዎች~*

ሼር ሼር ሼር

የክርስትና ጣዕሙና ሕይወቱ ሚታወቀው በፈተና ውስጥ ማለፍ እስከተቻለ ነው ። በዚህም ውስጥ ማለፍ ልናማርርበት ሳይሆን ልንማርበት ሚገባው ነው ። ብዙ መራራዎች ሲበዙ የብዙ ደስታ መግቢያ በር እንደሆነ ማወቅ ነው ትልቁ ። ዲላ በተሐድሶ እና በዙሪያው ባሉ በአሕዛብ መከበብ ፈተናዎቿ ናቸው የእነሱ መብዛት እና የትምሕርት እውነተኝነት አይደለም እንድንወድቅ ምክንያት ሚሆነን የኛ አለመማር ድንቁርና ነው ይህን ለማስወገድ የተለያዩ ጉባኤያት እየተካሔዱ ነው ይሄ ጥሩ ነው ቀጣይነት ያለው መሆን አለበት ። ከእነዚሕ አይነት አከባቢ የሚወጡ አገልጋዮች ወንድሞቻችንን መደገፍ አለብን የሚመቱት ሚስማር ይጠነክራል እንዲባል ጥናካሬዎቻቸው የኛን እገዛ ይፈልጋል ። መጥፎ ነገር ሲመጣ ጩህቱ እንደሚበዛ እንዲህ አይነት መልካም ስራዎችንም ስናይ ከዚያ በበለጠ መሆን አለበት ፤ በሶስት ቋንቋዎች ነው ዝማሬዎቹን የሰሩት ቤተክርስቲያን በሁሉም ቋንቋ ክርስትናን ማስተማሯ ሐላፈነቷ ነውና የሁሉንም ቋንቋ ማስተማር ግን ግዴታዋም ደግሞ አይደለም ።

ፈጣሪ ያግዛቹሁ ወንድሞቼ ሼር ሼር በማድረግ እናግዛቸው !!!!

ዘማሪ ዲያቆን ፍፁም ከበደ
4.3K views✞£iŧsûm✞, edited  07:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-16 09:55:08
"ሚሊየን መፅሀፍ የተሸከመች አህያ ያው አህያ ናት አትማርም፤ ሚሊየን አመት ውቅያኖስ ውስጥ የኖረ ድንጋይ ያው ድንጋይ ነው አይዋኝም!!!"

ይሄን ምን አሳሰበኝ ሁለት፣ ሶስት ዲግሪ ጭነው፣ ተምረው ተመራምረው፣ እልፍ መፅሀፍ አንብበው፣ ራሳቸው ፅፈው አሳትመው፣በየዩኒቨርሲቲው እና በሚዲያ ሌክቸር ሰጥተው፣ ነገር ግን እውቀት አእምሯቸውን ጥበብ ልባቸውን ያልነካው፣ በጥላቻ የተሞሉ፥ ለወንድሞቻቸው እንጥፍጣፊ ፍቅር የሌላቸው፣ የተማሩ መሳይ ቅብ-ምሁር፥ ፋቅ ፋቅ ቢያደርጓቸው ድንቁርናቸው ያገጠጠ፥ ፊደል እንጂ ጥበብ ያልቆጠሩ የትውልድ ሸክሞች ናቸው።

( Book for ALL facebook page )

ዘማሪ ዲያቆን ፍፁም ከበደ
3.2K views✞£iŧsûm✞, edited  06:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-15 07:09:25 ~ ደብረ ቁስቋም~

ህዳር ስድስት

እመቤታችን ከልጇ ከወዷጇ ከጌታችን ጋር ከስደት ወደሀገሯ የተመለሰችበት ቀን ነው

ይህም ቀን ቁስቋም ተብሎ ተሰይሟል።

ደብረ ዘይት ማለት የወይራ ተራራ ማለት እንደሆነ

ደብረ ታቦር ማለትም የታቦር ተራራ ማለት እንደሆነ

ደብረ ሲና ማለት የሲና ተራራ ማለት እንደሆነ።

ደብረ ሊባኖስ ማለትም የሊባኖስ ተራራ ማለት እንደሆነ።

ደብረ ቁስቋም ማለት የቁስቋም ተራራ ማለት ነው

ጌታችን ታምራት በሰራባቸው ተራራዎች በአሉ በተራራዎች ተሰይሞ ይከበራል።

ቁስቋምም እመቤታችን ከስደት ስትመለስ ከልጇ ከጌታችን ከፃድቁ ከዮሴፍ ከቅድስት ሰሎሜ ጋራ ያረፈችበት ተራራ ነው ።

ስለዚህ በአሉ ቁስቋም ተብሎ ይከበራል።

እመቤታችን ከልጇ ጋራ 42 ወር ተሰዳ በግብፅ ከኖረች በሇላ አሳዳጃው ሄሮድስ ሰለሞተ ወደሀገራ እንድትመለስ መልአኩ ለዮሴፍ ነግሮት ሲመለሱ በዚህ ተራራ ላይ አርፈዋል።

በዚም ተራራ ላይ ቅዱሳን መላእክት ክንፋቸውን ዘርግተው በእመቤታችን እና በጌታችን ላይ ረበዋል

ሊቁ ቅዱስ ያሬድም

~ዮም ፀለሉ መላእክት ላእለ ማርያም ወላእለ ወልዳ ክርስቶስ በደብረ ቁስቋም~

ብሎ እንደተናገራው በዚህ ተራራ መላእክት ረበው ዘምረውበታል አመስግነውበታል

እመቤታችን ተአምራት ባደረገችበት ዕለትና ተራራ ተሰይሞ በአለ ክብሯ ይከበራል።

ስለዚህ ቁስቋም ማለት ማርያም ማለት አይደለም እመቤታችን ያረፈችበት ተራራ ነው እንጂ

ልደታ በአታ ኪዳነ ምህረት ፍልሰታ ማለትም ማርያም ማለት ሳይሆን ልዩ ልዩ ታሪኳ የተከናወነበት ቀን ነው

ልደታ ብለን የምናከብረው የተወለደችበትን ቀን ነው

በአታ ብለን የምናከብረው ቤተ መቅደስ የገባችበት ቀን ነው

ኪዳነ ምህረት ብለን የምናከብረው የምህረት ቃል ኪዳን የተቀበለችበትን ቀን ነው

ፍልሰታ ብለን የምናከብረው ተነስታ ሥጋዋ ወደሰማይ

በእርገት የፈለሰበትን ቀን ነው

መናፍቃን እንደሚሉት ተራራ አናመልክም

ሰው የተወለደበትን ቀን እንደሚያከብር

እኛም እመቤታችን የተወለደችበትን ከስደት የመለሰችበትን ከሞት የተነሳችበትን ቀን እናከብራለን

በዘመናችን ያሉ ሰዎች

የአህያ ቀን

የውሻ ቀን

የበሽታ ቀን እያከበረ

የእመቤታችን የጌታችን የፃድቃንን ክብረ በአል ቀን ማክበር ያቅተዋል ።

ህዳር 5/2010

አዲስ አበባ

(~ መጋቤ ሐዲስ ሄኖክ ፈንቴ~)


እንኳን አደረሳቹሁ የቻናሌ ቤተሰቦች !!!

ዘማሪ ዲያቆን ፍፁም ከበደ
8.5K views✞£iŧsûm✞, edited  04:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-14 08:53:34
" ሰውን ምንለካበት ሰው እሸቱ "

አንዳንዱ ቁምነገረኛ ነው ብለህ ካሜራ ፊት ስታቀርበው ህዝብ ከህዝብ የሚያፋጅ በትውልድ መሃል እሾህ የሚተክል እልፍ ቀላጅ ሰው ሞልቷል።

ፓለቲከኛ፣ዝነኛ፣ካህን፣ፓስተር በሚሉ ስሞች የተደበቁ ትውልድ አምካኝ የበረሃ ምድርን የሚናፍቁ ከአንደበታቸው እሳት የሚተፉ ፣ጸጋቸው ማጫረስ የሆኑ ሰዎችን ይህቺ ጥቂት አመታት አሳይታናለች።

ቀልደኛ ነው ያልከው አንዳንድ ሰው ደግሞ ቁምነገር እራሱ እንዲህ እስኪቀናበት ድረስ ይተጋል።

አውደ ምህረት ሳይዙ፣ክህነት ሳይኖራቸው፣በልጅነት ፍቅር ብቻ ከቤተክህነት በላይ ሆነው የተጠሩ ሰዎች ስለመኖራቸው እሸቱ ትልቅ ምስክር ነው።

ቤተክርስቲያን ለእዚህ ነው ከጉያዋ ካሉት ይልቅ ከዓለም ላሉ ልጆቿ የምትሰደደው፣ድምጿን ከፍ አድርጋ የምትጣራው።

ይህቺ መቅደስ ካዝናዋ ልጆቿ፣ሐብቷ የእራሷ ጉባኤ እንደሆነ ይህ የተሳካ ዘመቻ በቂ ማሳያዋ ነው።

ወንድማችን ሆይ ....ካልተገለጠ ግብርህ ይልቅ የተገለጠው በጎነትህን አስቦ እግዚአብሄር መንግስቱን ይሸልምህ ።

እግዚአብሔር ይመስገን !

Kune Demelash kassaye -Arba Minch
8.2K views✞£iŧsûm✞, edited  05:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-13 12:11:37 ስለ እኛ ከሰማያት ወረደ

የጥያቄ መልስ

እኛን ለማዳን ስለ እኛ ከሰማያት ወረደ ተብሎ በዘወትር ጸሎት ( ጸሎተ ሃይማኖት ) ይጸለያል ለምን ? ከነ ትርጓሜው መልስ ቢሰጥ ብላቹህ ጥያቄ ለጠየቃቹሁኝ እነሆ የመጀመርያው ስለ እኛ ሚለውን ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን በመጽሐፍቶቻቸው እንዳስተማሩት በመተርጎም ልጀምር ፦

1. ስለእኛ ፦ ስለእኛ ሰው ሆነ ስንል አምላክ ሰው በመሆኑ እኛን የጠቀመው እንጂ እርሱ የተጠቀመው ነገር ስለሌለ ስለእኛ ስለሰው ልጆች ሰው ሆነ እንላለን ። አምላክ ሰው በመሆኑ በስጋዌ የሰው ስጋ ገንዘቡ በማድረጉ ምክንያት የተደረጉልን ነገሮች ሁሉ በእንቲአነ ( ስለእኛ ) የሚል መገለጫ ይሰጣቸዋል። ለምሳሌ ፦ ተሰብአ በእንቲአነ ፣ ሞተ በእንቲአነ ፣ ተሰቅለ በእንቲአነ ፣ ተንስአ በእንቲአነ ፣ ወርገ በእንቲአነ ፣ ዳግም ይመጽእ በእንቲአነ እያልን እስከ ዳግም ምጽአት ድረስ ያለውን አማላካችን በእኛ ፈት እስከሚያደርጋት የመጨረሻ የፍርድ ቀን መናገር እንችላለን ። ሌላው ፃድቃን ሰማዕታት እንዲሁም የሰው ልጅም ጭምር መከራ ቢቀበሉ መንግስተ ሰማያትን ተስፍ አድርገው ነው ክርስቶስ ግን ሰው የሆነው የሞተው ስለ ሰው ልጆች ስለ እኛ እንጂ ስለመንግስተ ሰማያት አይደለም ። መንግስተ ሰማያት የተከለከለችበት አዳምን መንግስተ እግዚአብሔር መንግስተ እግዚአብሔር ሊያወርሰው ሰው ሆነ እንጂ እርሱ እግዚአብሔር በመንግስተ እግዚአብሔር የተከለከለችበት ሆኖ በምድር ላይ ባደረገው አገልግሎት መንግስተ የተመለሰችለት አይደለም ።

ክርስቶስ ሰው የሆነው አዳም ያስወሰደውን ሕይወት ሊያስመልስልን ስለእኛ ነው ። እርሱም መልካም እያደረገ ለዲያብሎስ የተገዙትን ሁሉ እየፈወሰ ዞረ መባሉም ለዚህ ነው ። ሰይጣን በሚገዛው አለም ውስጥ ገብቶ ሰይጣንን ድል ነስቶ ሰውን ነፃ ለማውጣት ወደ ዓለም ስለመጣ ዘበእንቲ አነ ለሰብእ ወበእንተ መድኃኒትነ ወረደ እምሰማያት ፤ ስለእኛ ስለሰዎች እኛንም ስለማዳን ሰው ሆነ እያልን እንናገራለን ።


2 . ከሰማያት ወረደ ፦

ከሰማያት ወረደ ፦ እግዚአብሔር ከሰማያት ወረደ ማለት አብርሃም ወደ ግብፅ ወረደ ፤ ዮሴፍ ወደ ግብፅ ወረደ ዘፍ 12-10 ፣ 39፥1 እንደ ማለት ቀላል አይደለም ። ምክንያቱም አብርሃም ያዕቆብ ወደ ግብፅ ቢወርዱ ምን ቁም ነገር ነው ? ለባሕርያቸው ። ለአካላቸው መውጣት መውረድ ይስማማዋልና ። ነገር ግን ለአካሉም ሆነ ለባሕርዩ መውጣት መውረድ የማይሰማማው እግዚአብሔር ወረደ መባሉ ሰለምን ይሆን ? ዘፀ 19፥ 18 ፣ 34፥5 በታሕታዊ ዓለም በታሕታዊ ግብር ለሚኖሩት ለነቢያት የገለጣት ሚስጢሩ ወረደ አሰኝታዋለች ። ይህም ትልቅ ትርጓሜ ነው ያባቶቻችን እንዲህ ብለው ተርጉመውታል ፦ በምስጢረ ስጋዌ ውስጥ "ወረደ" ሰው ሆነ ይተረጎማል ። ምክንያቱም ለመለኮታዊው ባሕርይ ወደዚህ መጣ ፤ ወደዚያ ሄደ ተብሎ ሊነገር የማይገባው ሰለሆነ ።

፦ የአንፆቂያው ሊቀ ጳጳስ ቅዱስ ዮሐንስ ሰማይ ወምድር ምሉዐን እምኔሁ ፤ ሰማይና ምድር ከባሕርዩ ምሉዕነት የተነሳ ምሉዐን ናቸው ዮሐ. ክፍ 1፥8 ብሏል ።
ታድያ ወረደ ማለት ምን ማለት ነው ?

ሰማይ ዙፍኔ ነው ምድርም የእግሩ መረገጫ ናት ብሎ የተናገረ እግዚአብሔር አሁን ሰማይን ምድር ፣ ምድርንም ሰማይ አደረጋት ፤ ምድር የእግሩ መረገጫ ሳትሆን ዙፍኑ ሆነች። ሊቁ እንደተናገረው ዐለምኒ ኮነ ሰማየ ወሰማይኒ ኮነ ዓለመ ፤ ምድር ሰማይን ሆነች ሰማይም ምድርን ሆነች።

የሰማይ ኃይላትን ከምድራውያን ሰዎች ፣ ምድራውያን ሰዎች ከሰማያውያን ኅይላት አገናኛቸው ፤ ሰማያውያኑ በሰማይ የሚሰሩትን ስራቸውን ቅዳሴውን በምድር ሰሩት ። የሰው ልጆችም የመላእክትን ስራ ተሳተፍ ። እንዱ መልአክ ከሌላው መልአክ ጋር በዙፍኑ ዙሪያ ከበው የሚያመሰግኑት ምስጋና ከሰው ጋር ያመሰግኑ ዘንድ የሰው ልጆች ኑ እናመስግን ብለው ለምስጋ አብረዋቸው እንዲቆሙ ወደ እግዚአብሔር ማደርያ መጥራት ጀምረዋል ኢሳ 6 ፥1 ሉቃ 2፥12 አሁን በሰማይ በምድር መካከል ምን ልዩ ነት አለ ?

ይህን ፁሑፍ ሙሉ በሚባል እኔ የጥያቄውን መልስ ለመመልስ እና ለመረዳት ባጭሩ ያግዝ እንዳይበዛ ከማሳጠር ውጪ ያደረኩት እንደሌለ ትረዱልኝ ዘንድ መልእክቴ ነው የሊቁን መጽሐፍ ( "ተንከተም" ሊቀ ሊቃውን ስምዐ ኮነ መልአክ ) ታነቡት ትማሩበት ዘንድ መልእክቴ ነው ።


ዘማሪ ዲያቆን ፍፁም ከበደ
ኅዳር 4 2015 ዓ.ም ዲላ
1.1K views✞£iŧsûm✞, edited  09:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ