Get Mystery Box with random crypto!

YeneTube

የሰርጥ አድራሻ: @yenetube
ምድቦች: ፖለቲካ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 131.53K
የሰርጥ መግለጫ

መረጃዎችን ለመላክ @Fikerassefa

Ratings & Reviews

3.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 10

2024-03-02 08:45:36
128ኛ የዐድዋ ድል በአዲስ አበባ እየተከበረ ሲሆን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ተመስገን ጥሩ ነህ በፖሊስ ማርች ታጅበው በአፄ ምኒሊክ ሀውልት ስር ጉንጉን አበባ አኑረዋል።

በዓድዋ ድል መታሰቢያም ልዩ ልዩ ፕሮግራሞች እየተከናወኑ ይገኛሉ።
13.1K views05:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-01 19:05:55
በጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ ተከስቷል በተባለ የኮሌራ በሽታ ከአራት መቶ የማያንሱ ተማሪዎች መያዛቸውን በዩኒቨርሲቲው ትምህርታቸውን እየተከታተሉ የሚገኙ ተማሪዎች ተናገሩ።

ከተከሰተ አንድ ሳምንት ግድም ሆኖታል ስለተባለው ኮሌራም ሆነ በበሽታው ሳቢያ ስለደረሰ ጉዳት ከዩኒቨርሲቲውም ሆነ ከክልሉ ጤና ቢሮ ተጨማሪ ማብራሪያ ለማግኘት ያደረግነው ሙከራ ባለመሳካቱ ሀሳባቸውን ማካተት አልተቻለም።ይሁን እንጂ አስተያየት የሰጡ ተማሪዎች በበሽታው ተይዘው ህክምና ሲደረግላቸው ነበሩ ከተባሉ መካከል አንዳንዶቹ እያገገሙ መሆናቸውን ገልጸዋል።

በዩኒቨርሲቲው ተከሰተ ስለተባለው ወረርሽኝ ለተማሪዎች በይፋ የተገለጸ ነገር የለም ። ይሁንና የበሽታዉ መንስኤ በአንድ በኩል "በውኃ ብክለት" በሌላ በኩል "የግል ንፅህና ባለመጠበቅ" የመጣ ነው የሚል አስተያየቶች ተሰምተዋል።በዚህም ምክንያት ተማሪዎች ወደ መመገቢያ አዳራሾች ሲገቡ ለጥንቃቄ እንዲታጠቡ ሲደረግ ነበር ተብሏል።

ከተከሰተ አንድ ሳምንት ግድም ሆኖታል ስለተባለው ኮሌራም ሆነ በበሽታው ሳቢያ ስለደረሰ ጉዳት ከዩኒቨርሲቲውም ሆነ ከክልሉ ጤና ቢሮ ኃላፊ ተጨማሪ ማብራሪያ ለማግኘት ይህ ዘገባ እስከተጠናከረበት ሰዓት የሞባይል ስልክ ባለመነሳቱ እና ባለመስራቱ ሳቢያ ሀሳባቸውን ማካተት አልተቻለም።በሶማሌ ክልል መቀመጫ ጅግጅጋ ከተማ የሚገኘው ይኸው ዩኒቨርሲቲ ከቀናት በኃላ የተማሪዎች ምረቃ መርሀ ግብር ያከናዉናል ተብሎ ይጠበቃል።

Via DW
@YeneTube @FikerAssefa
14.3K views16:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-01 17:41:10 የኢትዮጵያ አየር መንገድ በሶማሊያ የአየር ክልል በኩል መብረር አቆመ!

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ እስያ አገራት ለሚያደርጋቸው በረራዎች ይጠቀምበት በነበረው የሶማሊያ የአየር ክልል በኩል መብረር ማቆሙን አስታወቀ።አየር መንገዱ እዚህ ውሳኔ ላይ የደረሰው ከሶማሊያ የአየር ትራፊክ ተቆጣጣሪዎች “አስተማማኝ የአየር ትራፊክ አገልግሎት” ባለማግኘቱ እንደሆነ ዋና ሥራ አስፈጻሚው አቶ መስፍን ጣሰው ለቢቢሲ አማርኛ ተናግረዋል።

ኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ እስያ ለሚደርጋቸው በረራዎች “ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ” ይጠቀምበት በነበረው የሶማሊያ አየር ክልል መብረር ያቆመው፤ የአየር መንገዱ አውሮፕላን ባለፈው ሳምንት ቅዳሜ የካቲት 16/2016 ዓ.ም. በአገሪቱ የአየር ክልል ውስጥ ካጋጠመው ክስተት ጋር በተያያዘ መሆኑን አቶ መስፍን አስታውሰዋል።

ኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን፤ “በዓለም አቀፍ አሠራር መሠረት እንደዚህ ዓይነት ነገር ሲያጋጥም ለሚመለከታቸው የሲቪል አቪየሽን ባለሥልጣናት ሪፖርት እናደርጋለን። [የቅዳሜውን ክስተት በተመለከተም] ለሶማሊያ እና ለኢትዮጵያ የሲቪል አቪየሽን ባለሥልጣናት ሪፖርት ተደርጓል” ሲሉ ለቢቢሲ ተናግረዋል። ይሁንና እስካሁን ድረስ በጉዳዩ ላይ የተሰጠ ምላሽ አለመኖሩን አክለዋል።የቅዳሜ ዕለቱ ክስተት የኢትዮጵያ አየር መንገድ በሶማሊያ አየር ትራፊክ ተቆጣጣሪዎች የሚሰጠውን አገልግሎት “አስተማማኝ ሆኖ እንዳያገኘው” ማድረጉን አቶ መስፍን ገልጸዋል።

በዚህም ምክንያት ይህ ክስተት ካጋጠመበት ማግስት እሁድ የካቲት 17/2016 ዓ.ም. አንስቶ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የሶማሊያን አየር ክልል መጠቀም ለማቆም መወሰኑን አስታውቀዋል።አቶ መስፍን፤ ከክስተቱ በኋላ ካለው ቀን አንስቶ “አማራጭ ለመጠቀም ወስነናል። ለዚህም ዋናው ምክንያት [የቅዳሜ ዕለቱ ክስተት] ነው። እዚያ በነበረው ሁኔታ፤ የአየር ክልሉ አስተማማኝ የአየር ትራፊክ አገልግሎት ስላላገኘንበት ለደኅንነት ስንል አማራጭ መንገዶች እየተጠቀምን ነው” ሲሉ የአየር መንገዱን ውሳኔ አብራርተዋል።

አየር መንገዱ ወደ እስያ ለሚያደርጋቸው በረራዎች የሚጠቀመው የሶማሊያን የአየር ክልል እንደነበር ያስታወሱት ዋና ሥራ አስፈጻሚው፤ በአሁኑ ሰዓት እነዚህ በራረዎች የሚደረጉት በጂቡቲ አየር ክልል በኩል መሆኑን ገልጸዋል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ የጂቡቲን የአየር ክልል እየተጠቀመ ያለው “ተጨማሪ ወጪ በማያመጣ መልኩ” እንደሆነም አክለዋል።የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ሌለሎች አገራት ለሚደረጉ በራረዎች የሶማሊያን አየር ክልል መጠቀም ቢያቆምም ወደ ሞቃዲሾ እና ወደ የሶማሊላንድ ዋና ከተማ ሀርጌሳ ከተማዎች የሚያደርጋቸውን በራረዎች “ያለ ችግር” መቀጠሉን አብራርተዋል።

Via BBC
@YeneTube @FikerAssefa
13.9K views14:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-01 17:21:27
ከፈረንሳዊው ጋዜጠኛ ጋር በታሰሩት የኦነግ የፖለቲካ ኦፊሰር ላይ አምስት ተጨማሪ የምርመራ ቀናት በፍርድ ቤት ተፈቀደ!

ከፈረንሳዊው ጋዜጠኛ አንቷን ጋሊንዶ ጋር አብረው የታሰሩት፤ ፖለቲከኛው አቶ በቴ ኡርጌሳ ላይ ፍርድ ቤት ተጨማሪ አምስት የምርመራ ቀናት ፈቀደ። የአዲስ ከተማ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ቀናቱን የፈቀደው፤ ፖሊስ “የተጠርጣሪውን ስልክ ምርመራ ውጤት ለመቀበል” ተጨማሪ ጊዜ እንዲሰጠው ያቀረበውን ማመልከቻ በመቀበል ነው።

የኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ) የፖለቲካ ኦፊሰር የሆኑት አቶ በቴ፤ “አፍሪካ ኢንተለጀንስ” ለተሰኘው የዜና ድረ ገጽ ዘጋቢ ከሆነው አንቷን ጋር በቁጥጥር ስር የዋሉት ባለፈው ሳምንት ሐሙስ የካቲት 14፤ 2016 ነበር። የኦነጉ ፖለቲከኛ እና ፈረንሳዊው ጋዜጠኛ በአዲስ አበባ ከተማ የመጀመሪያ ፍርድ ቤት ቦሌ ምድብ ችሎት ባለፈው ቅዳሜ በቀረቡበት ወቅት፤ ፖሊስ “ከፋኖ እና ከኦነግ ሸኔ ጋር በመተባበር በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ ሁከት ለማስነሳት በመሞከር” እንደጠረጠራቸው መግለጹ ይታወሳል።

የአዲስ አበባ ከተማ የመጀመሪያ ፍርድ ቤት አስቀድሞ በሰጠው ቀጠሮ መሰረት የተጠርጣሪዎቹን ጉዳይ መመልከት ሲጀምር፤ ቅድሚያ የማስረዳት ዕድሉን የሰጠው ለመርማሪ ፖሊስ ነው። ፖሊስ በተሰጡት ስድስት ቀናት፤ የአንድ ሰው ቃል መቀበሉን እና የተጠርጣሪዎችን የሞባይል ስልክ ለማስመርመር ወደ ፌደራል ፖሊስ መላኩን አስረድቷል። ሆኖም የስልክ ምርመራ ውጤቱን ተቀብሎ ከምርመራ መዝገቡ ጋር ማያያዝ እንደሚቀረው ገልጿል።

Via Ethiopia Insider
@YeneTube @FikerAssefa
13.1K views14:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-01 13:28:09
ዛሬ አንዲት አህያ መንታ ልጅ ወለደች እኮ ሰምታችኃል ?

የዛሬው FBC ዘገባ ነው ይሄ እንግዲህ

መጠየቅ ለምትፈልጉ :- ቦታው ሀረርጌ ዞን ብርቅ አከባቢ ናት።
14.1K viewsedited  10:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-01 11:32:15 ተፈረደበት

* 1 ዓመት ና
* 2 ሺህ ብር

ኮሜዲያን ያሬድ ዘላለም (ልጅ ያሬድ) በ 1 ዓመት ቀላል እስራትና በ2 ሺህ ብር የገንዘብ መቀጮ እንዲቀጣ ተወሰነ

የቅጣት ውሳኔውን የወሰነው የፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ 1ኛ ህገመንግስታዊና በህገመንግስት ስርዓቱ ላይ የሚፈጸሙ የወንጀል ጉዳዮችን የሚመለከተው ችሎት ተከሳሹ ያቀረበውን አምስት የቅጣት ማቅለያ አስተያየቶችን ይዟል።

የፍትህ ሚኒስቴር የተደራጁና ድንበር ተሻጋሪ ወንጀል ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ዐቃቤ ሕግ በኮሜዲያን ያሬድ ዘላለም ላይ ሶስት ክሶችን አቅርቦበት ነበር።

ከቀረቡበት ክሶች መካከል በኮምፒዩተር የሚፈጸም ወንጀል ድንጋጌን መተላለፍ፣ የቤተክርስቲያንና የሰዎችን ክብርና መልካም ስም ማጉደፍ እንዲሁም የጥላቻ ንግግር ማሰራጨት የሚሉ ተደራራቢ ክሶች ይገኙበታል።

ኮሜዲያን ያሬድ ዘላለም የቀረበበት ክስ እንዲሻሻል የክስ መቃወሚያውን በጽሁፍ ያቀረበ ቢሆንም በዐቃቤ ሕግ በኩል ክሱ ሊሻሻል የሚችልበት የህግ አግባብ እንደሌለ ተጠቅሶ መልስ ሰጥቷል።

ፍርድ ቤቱም ግራ ቀኙን መርምሮ ተከሳሹ ያቀረበው የክስ መቃወሚያ ጥያቄ የህግ አግባብነት የለውም በማለት ውድቅ አድርጎታል።

ከዚህም በኋላ ተከሳሹ በክሱ ላይ የተጠቀሰውን የወንጀል ድርጊት አለመፈጸሙን በመጥቀስ የዕምነት ክህደት ቃሉን በመስጠቱ ዐቃቤ ሕግ የሰውና የሰነድ ማምረጃውን አቅርቧል።

የቀረበውን ማስረጃ የመረመረው ችሎቱ ተከሳሹ የቀረቡበት ሶስት ክሶች ተጠቃለው በአዋጅ ቁጥር 1185/2012 አንቀጽ 4 እና 7 መሰረት እንዲከላከል ብይን ሰጥቷል።

ሶስቱም ክስ በአንድ እንዲጠቃለል የታዘዘው የወንጀል ድርጊቱ በሀሳብ፣ በጊዜና በቦታ ተመሳሳይ መሆኑን በምክንያትነት ተጠቅሶ ነበር።

ተከሳሹ የመከላከያ ማስረጃ አለኝ ማለቱን ተከትሎ ፍርድ ቤቱ ተከሳሹ ያቀረባቸውን የሰው መከላከያ ማስረጃዎችን ቃል አዳምጧል።

ተከሳሹ የሰው የመከላከያ ማስረጃ ያቀረበ ቢሆንም የዐቃቤ ሕግ ማስረጃን በተገቢው መከላከል ባለመቻሉ እና በክስ ዝርዝሩ ላይ የተጠቀሰውን የወንጀል ድርጊት መፈጸሙ በፍርድ ቤቱ በመረጋገጡ በዛሬው ቀጠሮ የጥፋተኝነት ፍርድ ተሰጥቶበታል።

ዐቃቤ ሕግ ድርጊቱ ታስቦ የተፈጸመ መሆኑን ጠቅሶ ቅጣቱ ከብዶ እንዲጣል ጠይቋል።

ፍርድ ቤቱ ተከሳሹ ለአካባቢ ጥበቃ ያበረከተውን አስተዋጾኦ፣ የቤተሰብ አስተዳዳሪና የቀደመ የወንጀል ሪከርድ እንደሌለው ገልጾ ያቀረበውን የቅጣት ማቅለያ ይዞለታል።

ፍርድ ቤቱ በድርጊቱ የእርስ በእርስ ግጭት አለመፈጠሩንና ጉዳት አለመድረሱን ከግምት ውስጥ በማስገባት በዕርከን 6 መሰረት በአንድ ዓመት ቀላል እስራትና በሁለት ሺህ ብር የገንዘብ መቀጮ እንዲቀጣ ወስኗል።

የአዲስ አበባ ማረሚያ ቤት ተከሳሹ እጁ ከተያዘበት ከነሃሴ 26 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ ያለውን ጊዜ ታሳቢ እንዲያደርግ ታዟል።

Via:- ታሪክ አዱኛ
@Yenetube @Fikerassefa
13.7K views08:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-01 11:30:56 የተሽከርካሪ ዝግ የሚሆኑ መንገዶች!!

128ኛው የዓድዋ ድል መታሰቢያ ክብረ በዓል በአዲስ አበባ ይከበራል፡፡

በዓሉ ፒያሳ አካባቢ በሚገኘው የዓድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም እንደሚከበር ተገልጿል፡፡ ለበዓሉ መከበር አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት አጠናቆ ወደ ስራ መግባቱን የፀጥታና ደህንነት የጋራ ግብረ ኃይል አስታውቋል፡፡

የካቲት 23 ቀን 2016 ዓ.ም የሚከበረው 128ኛው የአድዋ ድል መታሰቢያ በዓል በስኬት እንዲከበር ለማስቻል ቅድመ ዝግጅቱን አጠናቆ ወደ ተግባር መግባቱን ማስታወቁ ይታወቃል፡፡

ክብረ በዓሉ በሚከበር ዕለት የትራፊክ መጨናነቅ እንዳያጋጥም እና አሽከርካሪዎች አማራጭ መንገዶችን እንዲጠቀሙ የተወሰኑ መንገዶች ለተሽከርካሪ ዝግ እንደሚሆኑም የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል፡፡

በዚህም መሰረት፡-
• ከአፍንጮ በር ወደ ቅ/ጊዮርጊስ ቤ/ክርስቲያን
• ከሰሜን ሆቴል ወደ ቅ/ጊዮርጊስ ቤ/ክርስቲያን
• ከዮሃንስ ቤተ ክርስቲያን ወደ አቡነ ጴጥሮስ
• ከአራት መንታ ወደ ጅንአድ
• ከይርጋ ሃይሌ የገበያ ማዕከል ወደ አቡነ ጴጥሮስ
• ከሃብተ ጊዮርጊስ ድልድይ ወደ ሱማሌ ተራ
• ከሱማሌ ተራ ወደ ኤሊያና ሆቴል(ባንኮዲሮማ) መስቀለኛ
• ከተክለ ሃይማኖት አደባባይ ወደ ቴዎድሮስ አደባባይ
• ከአገር አስተዳደር መብራት( ኢሚግሬሽን) ወደ ቴዎድሮስ አደባባይ
• ከንግድ ማተሚያ ቤት ወደ ቴዎድሮስ አደባባይ
• ከአሮጌው ቄራ ወደ ባንኮ ዲሮማ መብራት
• ከራስ መኮንን ድልድይ ወደ ደጎል አደባባይ
• ከራስ መኮንን ድልድይ ወደ ቅ/ጊዮርጊስ ቤ/ክርስቲያን
• ከመቅደላ ሆቴል ወደ ቅ/ጊዮርጊስ ቤ/ክርስቲያን
• ከቅ/ጊዮርጊስ ቤ/ክርስቲያን ወደ ቴሌ እና ወደ ቅ/ጊዮርጊስ ቤ/ክርስቲያን ፊት ለፊት ወደሚገኘው አደባባይ የሚወስዱት መንገዶች የካቲት 23 ቀን 2016 ዓ/ም ከንጋቱ 11 ሰዓት ጀምሮ ለተሽከርካሪ ዝግ ስለሚሆኑ አሽከርካሪዎች ይህንን ተገንዝበው አማራጭ መንገዶችን እንዲጠቀሙ እና የትራፊክ ፖሊሶች የሚጠቁሟቸውን አማራጭ አቅጣጫዎችን በመጠቀም አስፈላጊውን ትብብር እንዲያደርጉ የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል፡፡

ክብረ በዓሉ በሚከበርበት ዙሪያ ከዋዜማው ከየካቲት 22 ቀን 2016 ዓ/ም ጀምሮ በዓሉ እስከሚጠናቀቅ ድረስ ከላይ በተጠቀሱት መንገዶች እና ፕሮግሙ በሚካሄድበት በአድዋ መታሰቢያ ሙዚየም ዙሪያ ተሽከርካሪን ማሳደርም ሆነ ለአጭርም ሆነ ለረጀም ሰዓት አቁሞ መሄድ ፈፅሞ የተከለከለ መሆኑንም ፖሊስ አሳስቧል፡፡
@Yenetube @Fikerassefa
12.9K viewsedited  08:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-02-29 22:13:01
በ19ኛው ክፍለ ዘመን በብሪታኒያ ወታደሮች ከኢትዮጵያ የተወሰደውን ጋሻ የሀገሪቷ መንግስት ጫና ተከትሎ ዛሬ የሚደረገዉ የጨረታው ሽያጭ እንዲሰረዝ ተደርጓል!

እንግሊዝ በ 1968 ከመቅደላ የዘረፈችዉ "የጦር ጋሻ" ዛሬ ሐሙስ ለአለም አቀፍ ጨረታ መቅረብን ተከትሎ የኢትዮጵያ መንግሥት ጨረታዉ ተሰርዞ ወደ ትዉልድ ሀገሩ እንዲመለስ ደብዳቤ ፅፏል።እ.ኤ.አ በ 1868 በመቅደላ ጦርነት ወቅት የተዘረፈው የኢትዮጵያ ጋሻ ሐሙስ በኒዉካስል ታይን ላይ ለአለም አቀፍ ለጨረታ ክፍት እንደሚደረግ ካፒታል ዘግቦ ነበር።

ይህን ተከትሎ የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዛሬ በሰጠዉ በመግለጫው የጨረታ ቤቱን እና የጋሻው ባለቤት ሽያጩን ለመሰረዝ እና "ወደ አገሩ ለመመለስ ድርድር ለመጀመር የወሰዱትን ጥበብ የተሞላበት ውሳኔ" በደስታ እንደሚቀበለዉ ገልጿል።

በቱሪዝም ሚኒስቴር ስር የሚንቀሳቀሰው ባለስልጣኑ ይህ ውድ ሀብት ወደ ትውልድ አገሩና ወደ ህጋዊ ባለቤቶቹ፣ የኢትዮጵያ ህዝብና መንግስት የሚመለስበትን ውጤት ለማስገኘት ጥረቴን እቀጥላለሁ ብሏል።

በኒውካስል ታይን የሚገኘው አንደርሰን እና ጋርላንድ የጨረታ ቤት ጋሻው ዛሬ የካቲት 21፤2016 ይካሄድ በነበረው “ጨርታ ዝርዝር ዉስጥ የጦር ጋሻዉን አካቷል” ለዚህም ለጋሻዉ ግምታዊ ዋጋዉ ከ1,000 እስከ 1,500 ዶላር አካባቢ መቀመጡ ታዉቋል።

Via Capital
@YeneTube @FikerAseffa
13.2K views19:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-02-29 21:47:09
በሞተር ብስክሌት ላይ እስከ ሰኞ ገደብ ተጣለ

በአዲስ አበባ ከነገ አርብ የካቲት 22/2016 ዓ.ም ከጠዋቱ 12:00 ጀምሮ እስከ ሰኞ የካቲት 25/2016 ዓ.ም እስከ ጠዋት 12:00 ሰአት ድረስ ሞተር ብስክሌት ማሽከርከር ፍጹም  የተከለከለ መሆኑን የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ አሳውቋል።

ቢሮው ክልከላው ለምን እንደተጣለ በግልፅ ያሳወቀው ነገር የለም።

ክልከላው የፀጥታ እና የትራፊክ ቁጥጥር የሚሰሩ አካላትን አያካትትም ተብሏል።

የሞተር ብስክሌት ባለንብረቶች ሆኑ አሽከርካሪዎች እስከ ተጠቀሰው ቀን ድረስ በትዕግስት እንዲጠብቁ ቢሮው አሳስቦ ይህን መልእክት በሚተላለፉ አካላት ላይ እርምጃ ይወሰዳል ሲል አስጠንቅቋል።

ባለፈው ከአፍሪካ ሕብረት ጉባኤ ጋር በተያያዘ ለቀናት የሞተር ብስክሌት አሽከርካሪዎች የእንቅስቃሴ ገደብ ተጥሎባቸው እንደነበር ይታወሳል።

@Yenetube @Fikerassefa
13.3K viewsedited  18:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-02-29 14:00:12
ትሪፕ ኤክስ በአዳዲስ OFFER / አቅርቦት በአይነቱ ልዩ የሆነ እድል ይዞልዎት መጥቷል::

6% ክፍያ በመክፈል ወደ ሮማንያ ለስራ እንዲሁም፣

ከ3-6% ክፍያ በመክፈል ለጉብኝት ወደ:
ካናዳ
ጣልያን
አሜሪካ
ጀርመን
ፖላንድ
ስፔን እና
ወደ ተለያዩ የአውሮፓ ሀገራት በመመዝገብ የጉዞ ህልምዎን በትሪፕ ኤክስ እውን ያድርጉ!

በተጨማሪም የተለያዩ ቢዝነስ ኢቬንቶች ላይ መታደም ለሚፈልጉ የማማከር እና የማዘጋጀት አገልግሎት እንሰጣለን፡፡

ትሪፕ ኤክስ ፍላጎትዎን ለማሳካት እነሆ አለው ይላል!

ይምጡና ይጎብኙን! Trust us to get you there!

አድራሻ፡ ሃያ ሁለት-ከጎላጉል አጠገብ ኖህ ህንጻ -5ኛ ፎቅ


ስልክ፡
0926389973
14.5K viewsedited  11:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ