Get Mystery Box with random crypto!

የፍቅር ጎጆ

የቴሌግራም ቻናል አርማ yefiker_gojo — የፍቅር ጎጆ
የቴሌግራም ቻናል አርማ yefiker_gojo — የፍቅር ጎጆ
የሰርጥ አድራሻ: @yefiker_gojo
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 479
የሰርጥ መግለጫ

Call us if you want to promote your product and service !!
FOR ANY PROMOTION
CONTACT ☎️ 251923715770 📩 @AbenaG

Ratings & Reviews

3.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

2

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 5

2023-04-15 20:27:37
3.4K views♕𝙰𝙱𝙴𝙽𝙸 𝙹𝙲❥̟, 17:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-15 17:04:27 ምኞት

ክፍል 51

ደራሲ ጥላሁን ተስፋዬ
.
.
.
ምኛትን አዲስ አበባ ይዟት መመለስ ፈራ ወዴት ወስጄ ልደብቅሽ
ወዴት ይዥሽ ልሽሽ ምኛቴ ?ይዘሀትጥፋ ጥፋ አለው ከዛ በፊት
ግን ነገውኑ ምኛትን እዛው ሀዋሳ እንድትሆን በማድረግ የሆነ
ምክንያት ፈጥሮ ወደ አዲስ አበባ በመሄድ የሚኪን ሁኔታ
ማጣራት ።
ሚኪን አጋጣሚ እንዳገኘው መስሎ አግኝቶት ስሜቱን መረዳት
ፈለገ ። በዚህ ሁኔታ እዚህ መቆየት አልፈልግም ነገውኑ ወደ
አዲስ አበባ ተመልሼ ሚኪን አገኘዋለሁ አለ•••
•••ፅናት ሚኪ ጋር እንደደረሰች የሚኪ ሁኔታ ያልጠበቀችው ነበርና
በጣም ደነገጠች።
ፊቱ ላይ ያነበበችው ተስፋ የመቁረጥ ስሜት እና ልክ እንዳያት
ያሳያት ሁኔታ ለሱ ባትነግረውም በውስጣ አፍና የያዘችው ፍቅር
ላለባት ፅናት በዛ ደረጃ ሚኪን ማየት ከባድ ነበር።
በዛ ሁኔታ ውስጥ ሆኖ ምን ሆነህ ነው ብሎ ለመጠየቅ ድፍረት
አጥታ ዝም ብላ አጠገቡ ተቀምጣ አይን አይኑን ስትመለከተው
ከቆየች ቡሀላ "እባክህ ሚኪዬ መጠጡ ይበቃሀል ወደ ቤት
እንኺድ እያለች ጥያቄ ባዘሉ አይኖቿ ስትመለከተው
ባትጠይቀውም ከሷ ውጪ መከፋቱን ማዘኑን የሚተነፍስበት
የሌለው ሚኪ ግን ከተለያዩበት ቀን አንስቶ ምን እንደተፈጠረ አንድ
ባንድ በንባ እያራሰ አወራት። በንባ እየራሰች አደመጠችው።
ይዛው ከሆቴሉ ወጣች። ወደቤት አስገብታ ካስተኛችው ቡኻላ
አባቷ እንዳያዝኑባት ስለሰጋች እኔ እዛኛው ክፍል ልተኛ ብላው
በመውጣት ወደ ቤታ ኼደች ።በጥዋት ሚኪ ሳይነቃ ተነስታ ወደ
ሚኪ ቤት መጣችና አንዱ ክፍል ውስጥ ጋደም ብላ ማታ ከነገራት
ታሪክ ውስጥ ሚኪን ከሀገር ሀገር ያንከራተተችው በጭራሽ ምኛት
ልትሆን እንደማትችል ውስጧ ጠርጥሮ ስትብከነከን ያደረችበትን
ሀሳብ ለሚኪ ለመንገር እስኪነቃ ትጠብቀው ጀመር። ፅናት።
መሳይ እስከ እኩለ ለሊት በሀሳብ ሲገላበጥ ቆይቶ እኩለ ለሊት
ላይ እንቅልፍ ጣለው። ጥዋት 12:15 ላይ ከእንቅልፉ ነቃ።
አልጋው ጠርዝ ላይ ተቀምጦ ወደ አዲስ አበባ ግድ የሚያስኬድ
ነገር ስለገጠመው ደርሶ እስኪመለስ ምኛት እዛው ሀዋሳ
እንድትጠብቀው ምን ብሎ ሊሳምናት እንደሚችል እያሰበ
የመጡለትን የተለያዩ የማሳመኛ ምክንያቶች ጭንቅላቱ ውስጥ
ሲፅፍ ሲቀድ ቆየ። የተሻለውን ሀሳብ አፅድቆ ሲያበቃ ተነስቶ
መለባበስ ጀመረ።
ክፍሏን በማንኴኴት ማንነቱን ተናገረ። ተነስታ ከፈተችለትና "
በሰላም ነው መስ? አለችው እንደቆመች።
"አይ•••እምምምም••አዋ ደላላው ነዋ •••ደላላው በለሊት ደውሎ
ቤቱን እግኝቻለሁ ነገር ግን በጥዋት መጥተህ ክራዩን ቅድሚያ
የሶስት ወር ካልከፈልክ ለሌላ ሰው አሳልፎ ያከራይብናል ፈጠን
ብሎኝ። ደርሼ ልምጣ ምኛቴ አንቺ እዚሁ እስከማታ እመለሳለሁ
።" ሲላት•••
ከድሬ እንደመጣች ሚኪ ቤቱ እስኪታደስ በሚል ሰበብ እዛ
ኮንደሚንየም ውስጥ አስቀምጧት መጣሁ ጠብቂኝ ብሎ የውሀ
ሽታ ሲሆን ውስጣ የተፈጠረው መጥፎ ስሜት መጣባት። ውስጣ
ተገለባበጠባት። "አይሆንም። በፍፁም መሄድ ካለብንም አብረን
እንሄዳለን እንጂ ለሰከንዶች እዚህ ብቻዬን አልሆንም ብቻዬን
ትተከኝ አትህዲ መስዬ እኔ ብቻዬን መሆን እፈራለሁ እባክህ
ጥለከኝ አትሂድ!" ብላ ተጠመጠመችበት መሳይ የሚይዝ
የሚጨብጠው ጠፋበት ምኛትን ድንገት የቀየራት ስሜት ምን
እንደሆነ ሲገባው "የትም አልሄድም ምኛቴ ምንም ሁኚ ምንም
የኔም ሁኚ የሌላ ወደ መቃብር ካልሆነ ሌላ ወደ የትም ጥዬሽ
አልሄድም የኔ መዳኒት የትም አልሄድም በቃ አብረን ሄደን
እንመለሳለን ። በጭራሽ ጥዬሽ አልሄድም የኔ ምኛት !" አለ
አጥብቆ እያቀፋት።
ወደ አዲስ አበባ ጉዞ እንደጀመሩ "አሁን ቤቱ ተገኝቷል ብያት
ስንደርስ ምን ልላት ነው?" ብሎ እየተጨነቀ ስልኩን አነሳና ወደ
ደላላው ደወለ።
ደላላው ስልኩን አንስቶ "ሀሎ ልደውልልህ ስል ደወልክ አዲሷ
ሙሽራህ እድለኛ ነች ባክህ ምርጥ ቤት ከነ ሙሉ እቃው
አግኝቼልሀለሁ!" ሲለው እሺ ከአንድ ከሁለት ሰአት ቡሀላ
እደውልልሀለሁ "ብሎ ለምክንያት የፈጠረው የቤት መገኘት ሰበብ
እውነት መሆኑ እያስደመመው አዲሷ ሙሽራ የኔ ትሁን የሌላ መች
ለየና እስቲ እንዳፍህ ያድርግልኝ አለ ለራሱ መሳይ በውስጡ።
ብሩኬን ሆስፒታል እንዳደረሱት የኪስ ዋሌቱን እና የጅ ስልኩን ይዞ
የተከተለው ሰው እዛው ለነበረ ዶክተር አስረክቦ ብሩክን
እንደማያውቀውና እሱ በመኪና አደጋ ሚስቱን ስላጣ አዝኖ
እንደተከተለው ተናግሮ ደና ስለሆነ ለቤተሰቦቹ በማታ ደውላችሁ
ባታስደነግጧቸው ጥሩ ነው ብሎ አስተያየቱን አክሎ ከሆስፒታሉ
ወጥቶ ሄደ።
ጥዋት ላይ አንዲት ነርስ ወደተንጋለለው ብሩክ ጠጋ ብላ እባክህን
የስልክህን መክፈቻ እዚህ ላይ ፃፍልኝ ወይ ክፈትልኝና ወደ
ቤተሰብ ልደውል አለችናው። እያቃሰተ ነገራት እና " ትንሹ"
የሚለው ላይ ደውይ ታናሽ ወንድሜ ነው እናቴ ልብ ድካም አለባት
እንዳትደነግጥ " አላት ። ከብሩክ ስልክ ላይ ትንሹ የሚል ስልክ
እየፈለገች ከክፍሉ ወጣች ለመደወል።
ትንሹ ስልክ ላይ ስትደውል ስልኩ አይጠራም ዝግ ነው። ግራ
ገባት። አደጋው ከመድረሱ በፊት ብሩክ ወደ ደወለባቸው ስልኮች
መደወል አሰበች። መጀመሪያ የደወለችው ወደ እነ ፅናት ሰራተኛ
ነበር ። ሰራተኛዋ ስልኳን እክፍሏ ውስጥ ትታው ቁርስ
እያቀራረበች ስለነበር አላነሳችውም። ወድያው ጨራርሳ ወደ
ክፍላ ስትመለስ ሚስ ኮል አየች ማታ ጥዋት ሚስኮል
እንዳደረኩልሽ እቅድ ሁለትን ቀጥይ ብሏት ነበር ብሩኬ።
ወድያው ወደ ሚኪ ደወለች ሚኪ ከንቅልፉ ባኖ አይኑን እያሻሸ
ስልኩን አነሳው።
ብሩኬ ባስጠናት መሰረት ፅናትና ወንድሟ በምኛት ላይ ምን
እንደፈፀሙ በአሳማኝ ሁኔታ ጋተችው።
ሚኪ ዞረበት። ቢዥ ሲልበት ታወቀው ። ፅናት እንደዛ ታደርጋለች
ብሎ መቀበል ቸገረው። ትንሽ ቆይቶ ከክፍሉ ወጥቶ ሰራተኛዋን "
ፅኑ የት ነች ?" አላት ። በአገጯ ያለችበትን ክፍል አሳየችው።
ዘው ብሎ ሲገባ ፅኑ እንቅልፍ ላይ ነች ተኝታለች ከነ ልብሷ።
ተጠግቶ በመቆም ቁልቁል እየተመለከታት የሰራተኛዋ ስልክ
አልነሳ ያላት ነርስ ዝቅ ስትል ፅናትን አገኘቻት። ፅናት ላይ
ደወለች። ፅናት ብንን ስትል ቁልቁል ያፈጠጠባትን ሚኪን አይታው
ደነገጠች።
"ምንድን ነው ሚኪ?!" አለች ተፈናጥራ በመነሳት።
"አይ ምንም ግን ልትነግሪኝ ፈልገሽ የደበቅሽኝ ሆን ብለሽ ሳይሆን
በስሜት ተገፋፍተሽ እኔን የሚያሳዝን ነገር ሰርተሽ ይሆን ?ፅናቴ! "
በጭራሽ ሚኪ ለምን እንዲህ አልከኝ ?"ስልኩን አንሺው ብሏት"
ወጣ ዳግም ሲጠራ።
ሚኪ ምን እንደሚል ምን እንደሚያረግ ግራ ግብት አለው።
ፅናት ግራ እንደተጋባች ስልኩን አነሳችው ነርሷ የብሩክን በመኪና
አደጋ ሆስፒታል መግባት ስትነግራት ደነገጠች ። ሮጣ በመውጣት
ለሚኪ ነግረችውና ተያይዘው ወደ ብሩክ እየሄዱ ቅድም ለምን
እንደዛ ብሎ እንደጠየቃት እንዲነግራት ስትወተውተው ፈራ ተባ
እያለ ነገራት "ለኔ ተወው ሚኪዬ እሄ የማን ሸር እንደሆነ ይገባኛል
ስላመንከኝ ግን ከልብ አመሰግናለሁ። አለች በንዴት ጣቶቿን ፀጉራ
መሀል ሽጣ እያበጠረችው።
ሆስፒታል ደርሰው ብሩክ ብዙም አለመጎዳቱን እንዳረጋገጡ
የደወለችላትን ነርስ በአይኗ ጠርታት ከክፍሉ ወጣች ወድያው
ቤተሰብ ጋር ለመደወል ስለፈለገች የብሩክን ስልክ ከፍታ
እንድትሰጣት ጠየቀቻት። ሰጠቻት። ወድያው የቤታቸውን ሰራተኛ
ስልክ ላይ የተላኩትን መልክቶች አገኘቻቸው። ደወለችላት። "
እቅድ ሁለትን ለሚኪ ደውዬ ነግሬዋለሁ ጌታው!" አለች ሰራተኛዋ።
ስልኩን ጠርቅማባት። እንደ እብድ እያደረጋት ወደ ክፍሉ
በመግባት " ፈጣሪ

ምላሽ ስለሰጠህ እኔ ምንም አልልህም!" ብላ
ስልኩን ብሩኬ ላይ ወርውራ ሚኪን እየጎተተች ከክፍሉ ይዛው
4.0K viewsflawoless , 14:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-15 17:04:27 ምኞት

ክፍል 50

ደራሲ ጥላሁን ተስፋዬ
.
.
.
"ምኛትዬ" ወዬ መስ ምነው ?
"ሚኪ እንደው ምናልባት ባንቺ ላይ ያደረገው ነገር ስተት እንደነበር
ተረድቶ ይቅርታ ቢጠይቅሽ ይቅርታውን ተቀብለሽ ታርቀሽው
አብረሽው ትኖሪያለሽ?•••
አይጠይቀኝም! ምክንያቱም ይቅርታ የሚጠይቀውን ስተትን ተሳስቶ
የፈፀመ ብቻ ነው። ሚኪ ደሞ ለሱ ትክክል የሆነውን ነገር አስቦና
ወስኖ ስላደረገ በምን ምክንያት ?ዛሬ ምን ተገኝቶ ይቅርታ
ይጠይቀኛል!
መልሷ ያልተዋጠለት መሳይ " ምኛትዬ ሰው በመጀመሪያ ለራሱ
ትክክል ነው ስተት መፈፀሙን የሚያምነው ስተት እንደነበር
መቀበል ሲፈልግ አልያም ስተት እንደነበር ሲረዳ ነው ። ትናንት
ትክክል መስሎን የሰራነው ወይም የወሰነው ውሳኔ ከቆይታ ቡሀላ
ትክክል እንድዳልነበርን ሲገለጥልን ከአንዳንዶቻችን በስተቀር ስተት
እንደሰራን ከተረዳንበት ቅፅበት አንስቶ የህሊና እረፍት እናጣለን
ስተቱን ወደ ዃላ ሄደን ማስተካከል ባይሆነልንም በኛ ስተት የተጎዳ
ሰው ካለ ያንን ሰው አግኝተን ይቅርታ እስከምንጠይቀው እንቅልፍ
የማይወስደን ብዙዎች ነን!" አላትና ምላሿን መጠባበቅ ጀመረ•••
ታድያ ዛሬ ላይ ትክክል እንዳልነበረ ገብቶት የሚጠይቀኝ ይቅርታ
ትክክክል እንዳልነበረ ማመኑን እንጂ ታርቆኝ ከኔ ጋር አብሮ
የመኖር ፍላጎት እንዳለው አያመለክትም እኮ።
አየህ መስዬ የጥፋተኝነት ስሜት እና አብሮ የመሆን ፍላጎት
የተለያዩ ነገሮች ናቸው።
ለዚህ ነው አንዳንድ ፍቅረኛሞች ሀምሳ ግዜ እየተጣሉ ሀምሳ ግዜ
ይቅርታ እየተባባሉ የሚታረቁት። ይቅርታ አብዛኛውን ግዜ ያለፈን
ስተት የማመን ጉዳይ እንጂ መጪውን ሒወት ለማቅናት በፍቅር
እና በደስታ ተሳስቦ ለመኖር የመወሰን ወይም የመለወጥ ጉዳይን
ያካተተ ነው ብሎ ማሰብ ከባድ ነው።ምክንያቱም አንዳንድ
ይቅርታዎች ስላለፈው ጉዳይ እንጂ ስለመጪው ሒወት የመወሰን
አቅማቸው ምንም ነው። ያንን የመወሰን ሙሉ አቅም ያለው
እውነተኛ ፍቅር ብቻ ነው ስለዚህ ሚኪ እኔ ላይ የፈፀመው በደል
አላስቀምጥ ሲለው ከኽሊና ወቀሳ ለመዳን ይቅርታ ጠየቀኝ ማለት
ከኔ ጋር ታርቆ ደስተኛ አርጎኝ ለመኖር የሚያስችል ፍቅር በውስጡ
መኖሩን አረጋገጠልኝ ማለት አይደለም። አለችው።
መሳይ ምኛት ለነገሮች ያላት ጠለቅ ያለ ምልከታ ከገመተው በላይ
ሆነ በትና ታድያ ምን ብሎ ቢጠይቃት ነው ይቅርታው በፍቅር አብሮ
የመኖር ዋስትናንም የሚያካትተው እያለ ሲያሰላስል•••
እሱ ዝም በማለቱ ምኛት ግዜ አገኘች። እሷም በተራዋ የመልስ
ምት የሚሆን ሚሳኤል የሆነ ጥያቄ ወደ መሳይ አስወነጨፈች•••
ናርዶስ ጥላህ ለመጥፋቷ በቂ ምክንያት ይዛ ዛሬ ብትመጣ ይቅር
ብለሀት አብረህ ለመኖር የማሰቢያ ግዜ ያስፈልግኻል?መስዬ?
አለችው•••
በመሳይ በኩል ትንፋሽ ጠፋ። እኼውልህ መስዬ መልሱን
ስለማውቀው አትንገረኝ እስካሁን እየሆነ ያለው ነገር እኔ ወይም
አንተ ቀድመን ያቀድነው ሳይሆን መኾን ያለበት ነው እየሆነ ያለው
ስለዚህ መሆን ያለበትን ነገር ለነገ እንተወው።
ኑሮ ወይም ሂወትን በቅድ ለመምራት ይቻል ይሆናል ፍቅርን ግን
በእቅድና ቀድሞ በተናገረው መንገድ የመራ ሰው የለም ፍቅር
ስሜት ነውና በእቅድ አይመራም ።
እኔ አንተን ከሚኪ ፍቅር መሸሸግያ ላደርግህ አልፈልግም! አንተም
የናርዶስን ፍቅር በኔ ውስጥ እንድትደበቀው አልፈልግም።
ግንኮ እኮ እኔ እየወደድኩሽ ነው ምኛቴ? አላት እጅግ በሚያሳዝን
ሁኔታ።
ግን መቸኮል የለብንማ መስዬ!! ውስጣችን ማለት የኔም ያንተም
ልብ ያልደመሰሰው ፍቅር አለ። ግኑኝነታችን የእውነት እንዲሆን
አሁን ባለንበት ከነገሮች ነፃ በሆነ እና መተሳሰብ በሞላበት
ፍቅራችን ትንሽ እንቆይ ግን መስዬ እንዳትናደድብኝ! ካንተ
የተደበቀ ምክንያት ኖሮኝ ሳይሆን ቸኩሎ መጣዱን ፈርቼው ነው
እባክህን ግዜ ስጠኝ ! አለችው።
ላንቺ ያለኝን ሁሉንም ስሜት አልነግርሽም አንቺ ዝግጁ
እስከምትሆኚ ብቻዬን አጣጥመዋለሁ ። እንዳልሽውም አንዱን
ስሜት ለመሸሽ ዘለን ገብተን ዘለን የምንወጣበት የወረት ፍቅር
እንዲሆን እኔም አልፈልግም። ነገር ግን የኔ ብትሆኝም ባትሆኝም
እንደነብሴ ከምወዳት ታናሽ እህቴ ከራሴ አስቀድሜ የማይሽ!
ተጎድቼ ባስደስህሽ ቅር የማይለኝ! በስስት እና በናፍቆት
የምጠብቅሽ ዳግም ለመኖሬ ምክንያት እንድትሆኚ መርጦ የላከሽ
የፈጣሪ ስጦታዬ እንደሆንሽ እወቂ!
ብሏት ቀና ሲል የሱ ብቻ ሳይሆኑ የሷም አይኖች በእምባ
መሞላታቸውን አስተዋለ ተያዩ እንባ ባጠለሉ አይኖቻችው ዝም
ብለው ተያዩ " ግን አሁንም የመጀመሪያው ጥያቄዬ
አልተመለሰልኝም አጠር አድርገሽ እንድትመልሽልኝ ጥያቄዬን
አስተካክዬ በድጋሚ እጠይቅሻለሁ••
ሚኪ ካንቺ ጋር በፍቅር ለመኖር ፍላጎት እንዳለው አረጋግጦ
ይቅርታ ቢጠይቅሽ ትቀበይዋለሽ?ምላሽሽ ምን ይሆናል?
መልሼልሀለሁ። አለችው።
አልመለሽልኝም ምኛቴ አላት።
አቦ ተወኛ አንተ ደረቅ የሆንክ ነገር አለችው። ተሳሳቁ እንባ ካዘሉ
አይኖች ስር የፈለቀ ንፁህ የፍቅር ሳቅ። ተነስቶ እንባዋን ጠረገና
ጉንጯን ሳማት ። ተያይዘው ጎን ለጎን ወደያዟቸው ክፍሎች
አመሩ። ሁለቱም ቁልፎቻቸውን እበሩ ቀዳዳ ውስጥ አስገብተው
በሩን ከመክፈታቸው በፊት ተያዩ ። ደና እደር መስ። አለችው። ደና
እደሪ ምኛቴ አላት ቁልፉን ዘወሩት። በሩን ከፍተው ከመግባታቸው
በፊት በድጋሚ "ደና እደሪ መልካም እንቅልፍ አላት። አሜን ብላው
ወደ ክፍሏ ገባች።
ትንሽ ቆመና እሱም ወደ ክፍሉ ገባ ።
አንቺ ትችይ ይሆናል እኔ ግን አልችልም ምኛት አለ አልጋው ላይ
ተደፍቶ። መሳይ በቀላሉ ፍቅር የሚያጠቃው አይነት ሰው ነው
ምኛት በዚች አጭር ግዜ ውስጥ ውስጡ ገብታ ልትነግስ
ተደላድላ ለመቀመጥ የሚሆናትን የልቡን ዙፋን ለመቆጣጠር ልቡ
ላይ ተሰንቅራ የቆየችውን ናርዶስን ጠራርጋ ለማስወጣት ናርዶስ
በመሳይ ልብ ለመንገሷ ፣ ለመፈቀራ ፣ በናርዶስ ለመሸነፉ
ምክንያት የሆኑትን ነገሮች በሙሉ በተሻለ ኹኔታ እየተካቻቸው
መኾኑን ሲረዳ ልቡ ፈራ።
" ቸኩሎ መጣዱን ፈርቼው ነው" ያለችው ነገር ደጋግሞ
ያቃጭልበታል እኔኮ ተጥጄ በፍቅርሽ መሞቅ ጀምሬአለሁ ምኛቴ !
አለ ጮክ ብሎ ምኛት አጠገቡ የለችምና አልሰማችውም።
ምኛትን አዲስ አበባ ይዟት መመለስ ፈራ ወዴት ወስጄ ልደብቅሽ
ወዴት ይዥሽ ልሽሽ ምኛቴ ?ይዘሀት ጥፋ ጥፋ አለው ከዛ በፊት
ግን ነገውኑ ምኛትን እዛው ሀዋሳ እንድትሆን በማድረግ የሆነ
ምክንያት ፈጥሮ ወደ አዲስ አበባ በመሄድ የሚኪን ሁኔታ
ማጣራት ።
ሚኪን አጋጣሚ እንዳገኘው መስሎ አግኝቶት ስሜቱን መረዳት
ፈለገ ። በዚህ ሁኔታ እዚህ መቆየት አልፈልግም ነገውኑ ወደ
አዲስ አበባ ተመልሼ ሚኪን አገኘዋለሁ አለ..........

#ሊጠናቀቅ ሁለት የመጨረሻ ክፍሎች ብቻ ይቀሩታል!! ቀጣዮቹን ክፍሎች የLike ተሳትፏችሁን አይቼ በፍጥነት እለቃለሁ እስኪ ታሪኩን ስንቶቻችሁ ወዳችሁታል? እየገጫችሁ።

.............ይቀጥላል............

ቀጣዩን#ክፍል እንዲቀጥልLike ማድረግ እንዳይረሳ ለወዳጅዎ #ሼር ያድርጉ
አሰተያየት ካላችሁ
3.6K viewsflawoless , 14:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-15 17:04:27 ምኞት

ክፍል 49

ደራሲ ጥላሁን ተስፋዬ
.
.
#ሊጠናቀቅ ሁለት የመጨረሻ ክፍሎች ብቻ ይቀሩታል!! ቀጣዮቹን ክፍሎች የLike ተሳትፏችሁን አይቼ በፍጥነት እለቃለሁ እስኪ ታሪኩን ስንቶቻችሁ ወዳችሁታል? እየገጫችሁ።
.
.
"ተርፏል ብዙ አልተጎዳም መሰለኝ እናውጣው እስቲ በዛ በኩል
ክፈቱት ኑ እባካችሁ እንፍጠን!" አለ ብሩክ መኪና ጋር ቀድሞ
የደረሰው ሰው ከፊት በተጨራመተው መኪናው ውስጥ ፊቱ በደም
የተጨማለቀውን ብሩክን ለማዳን አልከፈት ያለውን በር ለመክፈት
እየታገለ።
"ኧረ ተው እባካችሁ ትራፊክ ሳይመጣ መነካካቱ ጥሩ
አይመስለኝም አለች አንዲት ሴትዬ ወደመኪናው እየተጠጋች ።
አንድ አጠገባ የነበረ ሰው ብሽቅ ብሎ " እኔኮ እማይገባኝ ትራፊክ
እስኪመጣ ውስጥ ያለው ሰው ደሙ ፈሶ ይሙት ነው እምትይው?
ጥፋተኛው እንደሆነ ከውኻላ መጥቶ የገጨው እራሱ እንደሆነ
ይታወቃል! ደሞ ባይታወቅስ አንድ አደጋ ሲደርስ ትራፊክ
እስኪመጣ ፖሊስ እስኪመጣ እያልን ባደጋ የተጎዳው ሰው
እስኪሞት መጠበቁ ተገቢ ነው? ፈጣሪ ምናልባት በኛ ምክንያት
ዳን ብሎት ቢሆንስ የኛ እንቢተኝነት ምን እሚሉት ነው?
ተጠያቂነትን ለመሸሽ በሰው ስቃይና ነብስ መፍረድ ሰው ከሆነ
ፍጡር አይጠበቅም። " እሱስ ልክ ነው አለች ሴትዮዋ የሰውየው
ብስጭት አስደንግጧት።
ብሩክን ከመኪኖው ውስጥ ተጋግዘው አወጡት። ግንባሩ አከባቢ
በፍንጥርጣሪ ከመፈንከቱና ከጉልበቱ በታች መጠነኛ ጉዳት
ከመድረሱ ውጪ ብዙ የሚያሰጋ ጉዳት አልደረሰበትም።
"ፈጣሪ ይመስገን ኧረ ምንም አልተጎዳም ቀበቶ ማሰሩ በጀው!"
አለ ከመሀላቸው አንደኛው። ማን እንደደወለ ባይታወቅም
ከደቂቃዎች ቡኻላ አንድ አንፑላንስ እያቃንጨለች ቦታው ደረሰች
አፋፍሰው አስገቡት አንድ የብሩክን ሞባይል እና የኪስ ዋሌት የያዘ
ግለሰብ አብሮት ወደ ሆስፒታል ሄደ።
ብሩኬ ከሌላ መኪና ጋር በተላተመበት ተመሰሳይ ሰአት ላይ
በሀዋሳ ሁለት ወይን እስከወገባቸው የያዙ ብርጭቆዎች እርስ
በርስ ተላተሙ።
ምኛት እና መሳይ ሀዋሳ ከደረሱ ቡሀላ ስለምንም ጉዳይ ሳያወሩ
መዝናናትና መዝናናት ላይ ብቻ በማተኮር ታስራ እንደተለቀቀች
ጥጃ በሀዋሳ ምድር ሲቦርቁ ሲሽከረከሩ ሲስቁ ሲበሻሸቁ ዋሉ።
ከምሽቱ ሁለት ሰአት አከባቢ አልጋ ወደያዙበት ሄቴል አምርተው
እራት በልተው ከጨረሱ ቡሀላ የብሩኬ መኪና ስትጋጭ እነሱ
ለፍቅራቸው ወይን የተቀዳበት ብርጭቋቸውን አጋጩ።
መሳይ ጎንጨት አለና ውስጡ ሲከነክነው የነበረውን ነገር አነሳ
"የፍቅር ታሪክሽን እንጂ ፍቅረኛሽ ስለነበረው ሰው ማንነት እኮ
አልነገርሽኝም አላት ።
እሄን ርእስ እንደጦር በፍርሀት ስትጠብቀው ነበርና ደነገጠች
ፍርሀቱን የጫሩባት ሁለት ምክንያቶች ነበሯት ።
አንደኛው የርእሱ መነሳት ወደ ነበሩበት ጥሩ ያልሆነ ስሜት
እንዳይከታቸው መፍራቷ ሲሆን ሁለተኛው ስጓቷ ደግሞ ሚኪ
በመጀመሪያው አዲስ አበባ በመጣችበት ቀን በቤቱ መታደስ
ሰበብ ወደዛ ኮንዶሚንየም ሲያመጣት ኮንዶሚንየሙን የተከራዩት
እሱና ሌሎች ጓደኛቹ በጋራ ሆነው እንደነበር ነግሯታል ። መሳይን
ወደዛ ኮንደሚንየም ያመጣው ደሞ አባቱ ነው። አባትየው
ከተከራዮቹ አንድ ከሆነ ደሞ ከሚኪ ጋር ይተዋወቃሉ ማለት ነው ።
የመሳይ አባትና ሚኪ ከተዋወቁ ደግሞ መሳይ ሚኪን ሊያውቀው
ይችላል እኼንን ስታስብ ለምን እንደሆነ ለራሳም ባይገባትም እዛ
ኮንደሚንየም ውስጥ አምጥቶ የጣላት ፍቅረኛዋ ሚኪ መሆኑን
ለመሳይ መናገሩ አስፈራት። ግን እስከመቼ?
ትንሽ ተቁነጠነጠችና እሄውልህ መስዬ•••
አሁን ለግዜው አንተም ከናርዶስ አለም እኔም የኔ ከነበረው ሰው
አለም ወጥተን በራሳችን አለም ውስጥ የምናሳልፍበት ግዜ ቢሆን
አይሻልም መስዬ እስከመጨረሻው ባንድ ግዜ አውጥተን መጣል
ባንችልም እስቲ ትንሽ ግዜ አንተን ለአመት እኔን ለወራት
ሲያስጨንቁን የነበሩትን ሀሳቦች ፊት እንንሳቸው!? አለችው
" ግድ የለሽም ምኛትዬ በሙሉ ልብ ወደራሳችን አለም ለመግባት
መመለስ ያለባቸው ጥያቄዎች ስላሉ ነው ቀለል አርጊው እና
ንገሪኝ እባክሽ ?"አላት።
አቦ ያበጠው ይፈንዳ ምን አስጨነቀኝሳ አለች በውስጧ ወድያው
ሚኪ •••ማለት ሚክያስ ይባላል ።ለብዙ አመት ከሀገር ውጪ
ቆይቶ በቅርብ ግዜ ነው ወደ የመጣው ስትለው •••
መሳይ አፉን ተሻግሮ ጉሮሮው ላይ ደርሶ የነበረው ወይን ትን
ብሎት ሊወጣ ሲል እንደምንም አከሸፈው ።
ደነገጠ ሚኪን በደንብ ያውቀዋል ከአባቱ ጋር በእድሜ
የማይደራረሱ ሚኪ ገና በጎልማሳዎቹ እድሜ ውስጥ ያለ ሰው
ቢሆንም ከአባትየው ጋር ጓደኛ ነው እቤታቸው ብዙ ግዜ ይመጣል
ከሱም ጋር በጣም ይግባባሉ ።
ምን እንዳስደነገጠው አሰበ እቺን ልጅ እየወደድኳት ነው መሰለኝ
ፈጣሪዬ ባክህ ዳግም ለጉዳት አታጋልጠኝ አለ በውስጡ።
ዝምታው ያስፈራት ምኛት ምነው ዝም አልክ መስ ታውቀዋለህ
እንዴ? አለችው
"ኧረ በጭራሽ አላውቀውም ያስጨነኩሽ መሎኝ ነው ዝም ያልኩት
ብሎ መልሶ ፀጥ አለ።
ዝምታ በመሀላቸው ሰፈነ ተያዩ መሳይ ከዝምታው መሀል ድንገት
ያልታሰበ እና ቦንብ የሆነ ጥያቄ አስወነጨፈ።
"ምኛትዬ" ወዬ መስ ምነው ?
" ሚኪ እንደው ምናልባት ባንቺ ላይ ያደረገው ነገር ስተት
እንደነበር ተረድቶ ይቅርታ ቢጠይቅሽ ይቅርታውን ተቀብለሽ
ታርቀሽው አብረሽው ትኖሪያለሽ...

.............ይቀጥላል............

150 ከገባ#ክፍል 50 ዛሬ ይለቀቃል
3.6K viewsflawoless , 14:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-15 16:55:58
ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች ቤተሰቦቻችን እንኳን ለብርሃነ ትንሳኤው በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን!
መልካም የፋሲካ በአል
3.8K views Call King , 13:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-15 08:25:15
እንኳን ለጌታችን ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የስቅለት በአል በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን

''አንዱ ስለ ሁሉ ሞተ''
(2ቆሮ5÷14)

@yefiker_gojo
4.8K viewsAbela ŵiž ~V~, 05:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-15 00:18:36
በሕይወታችን ውስጥ ሁለቱ ወሳኝ ነገሮች ትእግስት እና ጊዜ ናቸው። እያንዳንዱ መጥፎ እድል በትእግስት ይረታል። ጊዜም የማይጠቅም የድንጋይ ከሰል ቅሪትን ወደ ዲያመንድ የመቀየር ኃይል እንዳለው ሁሉ የእኛንም ሕይወት መስመር ለማስያዝ ወሳኝ ነገር ነው።
ዛሬ ላይ የሚሰማን ህመም ነገ ላይ ለምንኖረው ሕይወት ጥንካሬ ነው። የሚያጋጥመንን እያንዳንዱ ፈተና በትክክል ከተጠቀምንበት ጥሩ የመለወጥ እድል ይፈጥርልናል።
(ከሰርድዮን መጽሐፍ የተቀነጨበ

@yefiker_gojo
5.0K viewsAbela ŵiž ~V~, edited  21:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-15 00:16:57
የተሸነፍኩት በጠይም ቆንጆ ፊቷ አይደለም፤ የተማረኩት በጥቁር ዞማ ፀጉሯ አይደለም ፤ ያሸነፈችኝ በየዋህነቷ ነው ።

ለመድመቅ አለመፍጨርጨሯ ነው ፤ ተፈላጊነቷን ለማሳየት አትዳክርም ፤ ያላትን ለማጉላት አትታከክም ።

የምወዳት ፍቅሯን ለመግለፅ አውላላ መንገድ ላይ በነፃነት ስለምትጠመጠምብኝ ነው ፤ የገዛኝ ብቻዬን ስለምትወደኝ ነው።

ሲሳካልኝ እና ስወድቅ ከጎኔ እንደምትሆን ስለምታሰማኝ ነው።

የምወዳት ከወዳጆቻችን ጋ ስንሰባሰብ እኔ ሳወራ ከሁሉም በላይ ቀልቧን ስለምትሰጠኝ ነው ፤ የነገርኳትን ወሬ ደገምከው ሳትለኝ ስለምትሰማኝ ። የወደድኩትን ነገረ ስለምትወድልኝ ነው ።

የምወዳት ተስፋ ቆርጬ ፤ ተናድጄ ፤ አዝኜ ሳወራ በዝምታ እረጋ ብላ ስለምታፅናናኝ ነው።

የምወዳት ተቀይማኝ ተናዳብኝ አንገቷ ስር ስስማት በዝምታ ስትሳምልኝ ፤ ተናዳ በትንሽ ልፋት ስለምትረጋጋልኝ ነው ።

የምወዳት ልቧ አምኖኝ ፍለጋ ስላቆመች ነው። ከመታመን በላይ ሃላፊነት የት አለ ?

የምወዳት ስታናድደኝ እና ስናደድ በፍቅር ይቅርታ ስለምጠይቀኝ ነው ።

የምትፈልገውን እንዳደርግላት የምታደርገኝ ትህትና በተጠቀጠቀበት ልምምጥ ነው ። ስትለማመጥ በትሯ አይኗ ነው አይኗ ያሳዝናል፤ እሷ ላይ ስልጣን እንዳለኝ ይሰማኛል እንደምትታዘዘኝ ስታስዳስሰኝ ፍፁም ታዛዥ እሆናለሁ ።

@yefiker_gojo
5.1K viewsAbela ŵiž ~V~, edited  21:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-14 19:54:00 ይሄ ንፁህ ሳቅሽ ጥርሴን አስገለጠኝ
እሄ ተአምር ቃልሽ እምባዬን አስዋጠኝ
ሳይዉል ሳያድር ጨነቀኝ
በሀሳብ ገምቦ ተገፋው
ግዜያዊ ሳቅሽን ሳስብ
ከመሞት በላይ ተከፋው




    
,,,,,,,,,,, ,,,,,,,,,,
        •═••• •••═•
  
    
@Yefiker_Gojo    ,, @AbenaG
━━━━━✦ ✿ ✦━━━━━
5.7K views♕𝙰𝙱𝙴𝙽𝙸 𝙹𝙲❥̟, 16:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-14 19:52:40 አይንሽ ሲርበኝ ሳቅሽ ሲጠማኝ
ህመምሽ ህመም ሆኖ ሲሰማኝ
ስሜ ይመስል ስምሽ ሲጠራ
ድንግጥ እርብትብት ስል እያየሽኝ
.
.
.
''ጠላሁሽ ስልሽ ለምን አመንሽኝ''



    
,,,,,,,,,,, ,,,,,,,,,,
        •═••• •••═•
  
    
@Yefiker_Gojo    ,, @AbenaG
━━━━━✦ ✿ ✦━━━━━
5.4K views♕𝙰𝙱𝙴𝙽𝙸 𝙹𝙲❥̟, 16:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ