Get Mystery Box with random crypto!

ምኞት ክፍል 49 ደራሲ ጥላሁን ተስፋዬ . . #ሊጠናቀቅ ሁለት የመጨረሻ ክፍሎች ብቻ ይቀሩ | የፍቅር ጎጆ

ምኞት

ክፍል 49

ደራሲ ጥላሁን ተስፋዬ
.
.
#ሊጠናቀቅ ሁለት የመጨረሻ ክፍሎች ብቻ ይቀሩታል!! ቀጣዮቹን ክፍሎች የLike ተሳትፏችሁን አይቼ በፍጥነት እለቃለሁ እስኪ ታሪኩን ስንቶቻችሁ ወዳችሁታል? እየገጫችሁ።
.
.
"ተርፏል ብዙ አልተጎዳም መሰለኝ እናውጣው እስቲ በዛ በኩል
ክፈቱት ኑ እባካችሁ እንፍጠን!" አለ ብሩክ መኪና ጋር ቀድሞ
የደረሰው ሰው ከፊት በተጨራመተው መኪናው ውስጥ ፊቱ በደም
የተጨማለቀውን ብሩክን ለማዳን አልከፈት ያለውን በር ለመክፈት
እየታገለ።
"ኧረ ተው እባካችሁ ትራፊክ ሳይመጣ መነካካቱ ጥሩ
አይመስለኝም አለች አንዲት ሴትዬ ወደመኪናው እየተጠጋች ።
አንድ አጠገባ የነበረ ሰው ብሽቅ ብሎ " እኔኮ እማይገባኝ ትራፊክ
እስኪመጣ ውስጥ ያለው ሰው ደሙ ፈሶ ይሙት ነው እምትይው?
ጥፋተኛው እንደሆነ ከውኻላ መጥቶ የገጨው እራሱ እንደሆነ
ይታወቃል! ደሞ ባይታወቅስ አንድ አደጋ ሲደርስ ትራፊክ
እስኪመጣ ፖሊስ እስኪመጣ እያልን ባደጋ የተጎዳው ሰው
እስኪሞት መጠበቁ ተገቢ ነው? ፈጣሪ ምናልባት በኛ ምክንያት
ዳን ብሎት ቢሆንስ የኛ እንቢተኝነት ምን እሚሉት ነው?
ተጠያቂነትን ለመሸሽ በሰው ስቃይና ነብስ መፍረድ ሰው ከሆነ
ፍጡር አይጠበቅም። " እሱስ ልክ ነው አለች ሴትዮዋ የሰውየው
ብስጭት አስደንግጧት።
ብሩክን ከመኪኖው ውስጥ ተጋግዘው አወጡት። ግንባሩ አከባቢ
በፍንጥርጣሪ ከመፈንከቱና ከጉልበቱ በታች መጠነኛ ጉዳት
ከመድረሱ ውጪ ብዙ የሚያሰጋ ጉዳት አልደረሰበትም።
"ፈጣሪ ይመስገን ኧረ ምንም አልተጎዳም ቀበቶ ማሰሩ በጀው!"
አለ ከመሀላቸው አንደኛው። ማን እንደደወለ ባይታወቅም
ከደቂቃዎች ቡኻላ አንድ አንፑላንስ እያቃንጨለች ቦታው ደረሰች
አፋፍሰው አስገቡት አንድ የብሩክን ሞባይል እና የኪስ ዋሌት የያዘ
ግለሰብ አብሮት ወደ ሆስፒታል ሄደ።
ብሩኬ ከሌላ መኪና ጋር በተላተመበት ተመሰሳይ ሰአት ላይ
በሀዋሳ ሁለት ወይን እስከወገባቸው የያዙ ብርጭቆዎች እርስ
በርስ ተላተሙ።
ምኛት እና መሳይ ሀዋሳ ከደረሱ ቡሀላ ስለምንም ጉዳይ ሳያወሩ
መዝናናትና መዝናናት ላይ ብቻ በማተኮር ታስራ እንደተለቀቀች
ጥጃ በሀዋሳ ምድር ሲቦርቁ ሲሽከረከሩ ሲስቁ ሲበሻሸቁ ዋሉ።
ከምሽቱ ሁለት ሰአት አከባቢ አልጋ ወደያዙበት ሄቴል አምርተው
እራት በልተው ከጨረሱ ቡሀላ የብሩኬ መኪና ስትጋጭ እነሱ
ለፍቅራቸው ወይን የተቀዳበት ብርጭቋቸውን አጋጩ።
መሳይ ጎንጨት አለና ውስጡ ሲከነክነው የነበረውን ነገር አነሳ
"የፍቅር ታሪክሽን እንጂ ፍቅረኛሽ ስለነበረው ሰው ማንነት እኮ
አልነገርሽኝም አላት ።
እሄን ርእስ እንደጦር በፍርሀት ስትጠብቀው ነበርና ደነገጠች
ፍርሀቱን የጫሩባት ሁለት ምክንያቶች ነበሯት ።
አንደኛው የርእሱ መነሳት ወደ ነበሩበት ጥሩ ያልሆነ ስሜት
እንዳይከታቸው መፍራቷ ሲሆን ሁለተኛው ስጓቷ ደግሞ ሚኪ
በመጀመሪያው አዲስ አበባ በመጣችበት ቀን በቤቱ መታደስ
ሰበብ ወደዛ ኮንዶሚንየም ሲያመጣት ኮንዶሚንየሙን የተከራዩት
እሱና ሌሎች ጓደኛቹ በጋራ ሆነው እንደነበር ነግሯታል ። መሳይን
ወደዛ ኮንደሚንየም ያመጣው ደሞ አባቱ ነው። አባትየው
ከተከራዮቹ አንድ ከሆነ ደሞ ከሚኪ ጋር ይተዋወቃሉ ማለት ነው ።
የመሳይ አባትና ሚኪ ከተዋወቁ ደግሞ መሳይ ሚኪን ሊያውቀው
ይችላል እኼንን ስታስብ ለምን እንደሆነ ለራሳም ባይገባትም እዛ
ኮንደሚንየም ውስጥ አምጥቶ የጣላት ፍቅረኛዋ ሚኪ መሆኑን
ለመሳይ መናገሩ አስፈራት። ግን እስከመቼ?
ትንሽ ተቁነጠነጠችና እሄውልህ መስዬ•••
አሁን ለግዜው አንተም ከናርዶስ አለም እኔም የኔ ከነበረው ሰው
አለም ወጥተን በራሳችን አለም ውስጥ የምናሳልፍበት ግዜ ቢሆን
አይሻልም መስዬ እስከመጨረሻው ባንድ ግዜ አውጥተን መጣል
ባንችልም እስቲ ትንሽ ግዜ አንተን ለአመት እኔን ለወራት
ሲያስጨንቁን የነበሩትን ሀሳቦች ፊት እንንሳቸው!? አለችው
" ግድ የለሽም ምኛትዬ በሙሉ ልብ ወደራሳችን አለም ለመግባት
መመለስ ያለባቸው ጥያቄዎች ስላሉ ነው ቀለል አርጊው እና
ንገሪኝ እባክሽ ?"አላት።
አቦ ያበጠው ይፈንዳ ምን አስጨነቀኝሳ አለች በውስጧ ወድያው
ሚኪ •••ማለት ሚክያስ ይባላል ።ለብዙ አመት ከሀገር ውጪ
ቆይቶ በቅርብ ግዜ ነው ወደ የመጣው ስትለው •••
መሳይ አፉን ተሻግሮ ጉሮሮው ላይ ደርሶ የነበረው ወይን ትን
ብሎት ሊወጣ ሲል እንደምንም አከሸፈው ።
ደነገጠ ሚኪን በደንብ ያውቀዋል ከአባቱ ጋር በእድሜ
የማይደራረሱ ሚኪ ገና በጎልማሳዎቹ እድሜ ውስጥ ያለ ሰው
ቢሆንም ከአባትየው ጋር ጓደኛ ነው እቤታቸው ብዙ ግዜ ይመጣል
ከሱም ጋር በጣም ይግባባሉ ።
ምን እንዳስደነገጠው አሰበ እቺን ልጅ እየወደድኳት ነው መሰለኝ
ፈጣሪዬ ባክህ ዳግም ለጉዳት አታጋልጠኝ አለ በውስጡ።
ዝምታው ያስፈራት ምኛት ምነው ዝም አልክ መስ ታውቀዋለህ
እንዴ? አለችው
"ኧረ በጭራሽ አላውቀውም ያስጨነኩሽ መሎኝ ነው ዝም ያልኩት
ብሎ መልሶ ፀጥ አለ።
ዝምታ በመሀላቸው ሰፈነ ተያዩ መሳይ ከዝምታው መሀል ድንገት
ያልታሰበ እና ቦንብ የሆነ ጥያቄ አስወነጨፈ።
"ምኛትዬ" ወዬ መስ ምነው ?
" ሚኪ እንደው ምናልባት ባንቺ ላይ ያደረገው ነገር ስተት
እንደነበር ተረድቶ ይቅርታ ቢጠይቅሽ ይቅርታውን ተቀብለሽ
ታርቀሽው አብረሽው ትኖሪያለሽ...

.............ይቀጥላል............

150 ከገባ#ክፍል 50 ዛሬ ይለቀቃል