Get Mystery Box with random crypto!

የሕያ ኢብኑ ኑህ - Yahya Ibnu Nuhe

የቴሌግራም ቻናል አርማ yahyanuhe — የሕያ ኢብኑ ኑህ - Yahya Ibnu Nuhe
የቴሌግራም ቻናል አርማ yahyanuhe — የሕያ ኢብኑ ኑህ - Yahya Ibnu Nuhe
የሰርጥ አድራሻ: @yahyanuhe
ምድቦች: እንስሳት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 13.06K
የሰርጥ መግለጫ

﷽ | Muslim | Theology | Comparative Religion | Philosophy | Student | Teacher |

Ratings & Reviews

3.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 7

2023-03-14 15:32:49
የነብዩ ሙሐመድ "ﷺ" ጋብቻዎች እና ተያይዘው የሚነሱ ጥያቄዎችን አስመልክቶ ከዚህ በፊት በተከታታይ እየተወያየን መቆየታችን ይታወሳል፤ በዛሬው የቲክቶክ ላይቭ ትምህርታችንም ከዚያ የቀጠለውን ክፍል የምንመለከት ሲሆን በውይይታችን ሁለት ጥያቄዎችን አንስተን ምላሽ የምንሰጥባቸው ይሆናል። ትምህርቱን ይከታተሉ፥ ሼር ያድርጉ።
...
ትምህርቱን ለመከታተል ከዚህ በታች ባሉ ሊንኮች የቲክቶክ መገኛዎችን ፎሎው ማድረግ ይችላሉ፦

ሒዳያ ኢስላማዊ ማዕከል
https://bit.ly/3BZerNy

አቡ ዩስራ
https://bit.ly/3kkoaYU

ኢልያህ ማሕሙድ
https://bit.ly/3VlI6HQ

የሕያ ኢብኑ ኑህ
https://bit.ly/3Vs5O4V
1.5K views12:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-11 22:53:11 https://vm.tiktok.com/ZMYaKPePp/
787 views19:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-11 21:47:06 ከሰሞኑ በሀላባ ትምህርት ቤት ውስጥ አንዲት ተማሪ በእምነቷ ምክንያት ታስራለች የሚል በተለይም በወንጌላውያን ዘንድ በሰፊው እየተራገበ ይገኛል። እውነታውን የማያቁ ሰዎችም መለስተኛ ውዥንብሮች ውስጥ ወድቀዋል። ያለውን ሁኔታ ከአካባቢው ለማጣራት እንደሞከርኩት ዝርዝር ጉዳዩን ከዚህ በታች ለማስቀመጥ እሞክራለሁ፦
..
1/ ልጅቷ የታሰረችበት ምክንያት በምትማርበት ትምህርት ቤት በርካታ ተማሪዎች ለህመም መዳረጋቸውን ተከትሎ ከህመማቸው ጀርባ መመረዝ እንዲሁም ድግምት እንዳለ በመታመኑ ሳቢያ ነው። በዚህ ተግባርም ቀጥተኛ ተሳታፊ ናት የሚሉ ጥርጣሬዎች በተማሪዎችም በህግ አካላትም በመኖሩ ሳቢያ ታስራለች። በወቅቱም "ገና ምን አይታችሁ?" የሚል ስሜታዊ ንግግር መናገሯን በቦታው ከነበሩ ሰዎች ለመስማት ችያለሁ።
...
2/ በእምነቷ ምክንያት ታሰረች የሚባለው ፈጽሞ ሀሰትና ጉዳዩን ለማጦዝ የተፈጠረ አስቂኝ ክስ ነው። በዋናነት ጉዳዩን አስመልክቶ ቀድሞ የታሰረውና እነዚያን ባዕድ ነገሮች እያዘጋጀ ይሰጣታል ተብሎ በቀዳሚነት የተከሰሰው ሰው ሙስሊም ሰው ነው። ተግባሩ እምነትን ያማከለ ቢሆን በአካባቢው የባህል ሀኪም ነኝ የሚለው አቶ ናሲር ቀድሞ አይታሰርም ነበር። ጉዳዩ ከእምነት ጋር የሚያያዝ አይደለምና ተጠርጣሪዎቹ ሙስሊምም ይሁኑ ፕሮቴስታንት የእምነት ልዩነት ሳይደረግ በተግባሩ ተጠርጥረው በህግ ቁጥጥር ስር ሊውሉ ችለዋል።
...
3/ አብዛኛው ሰው በዘመቻ መልክ ሳይቀር ስለታሰረችው ሴት ሲጮህ ተመልክተናል። በሚገርም ሁኔታ ግን እሷ በሰጠቻቸው ባዕድ ነገሮች ሳቢያ ታመው በህክምና ቦታዎች ስለሚገኙ ሴቶች ማናቸውም መናገር አይፈልጉም። የነሱ ጉዳይ ከህመም አልፎ ሞት እራሱ ቢመጣ ለነዚህ ሰዎች ግዳቸው አይደለም። በዚህ መልኩ ጉዳዩን በህግ አግባብ እንዲፈታ ከመጠየቅ ይልቅ በዘመቻ ጫና ለመፍጠር መፍጨርጨርን መርጠዋል።
...
4/ የዞኑ የጸጥታ ቢሮ ይህንን በተመለከተ የወሰደው እርምጃ እንደ አንድ ኃላፊነት እንደሚሰማው የመንግስት አካል ተገቢ ነው። በርካታ ሰዎች ታመዋል፥ የዚህ መነሻ ተደርጎ የተጠቀሰም ተጠርጣሪ አለ። በዚህ ሒደት ውስጥ ተጠርጣሪውን በህግ ከለላ ውስጥ አድርጎ ምርመራ ማካሔዱ በምን መልኩ እንደ ውግዝ እንዳስቆጠረው ሊገባኝ አልቻለም። ተጎጂዎች ጉዳዩ እንዲጣራላቸውና አጥፊው ተገቢውን ህጋዊ እርምጃ እንዲወሰድበት ይጠብቃሉ። ይህንን ጉዳይ ኃላፊነት ወስዶ የሚያጣራው ደግሞ የሚመለከተው የጸጥታ አካል ነው። ይህ ደግሞ ስራው ነውና የሚጠበቅ እንጅ የሚያስወግዝ አይደለም።
...
❐ ሲጠቃለል
...
በግሌ ከተለያዩ አካላት ለማጣራት እንደሞከርኩት ያገኘሁት መረጃ ይህ ነው። ከዚህ በዘለለ ሀላባን ሆን ተብሎ በሀይማኖት ስም በጅምላ ለማጠልሸት እየተሄደበት ያለው ርቀት እጅግ አሳፋሪ ነው። በጉያዋ በርካታ የተለያየ እምነት አማኞች ትላንትም ኑረዋል፥ ዛሬም በሰላም እየኖሩ ነው። ነጠላ ክስተቶችን ሰንጥቆ ሀገር ምድሩ የተናወጠ እያስመሰሉ በማኅበራዊ ሚዲያው ለማስተጋባት የሚሞከረው አካሔድ አይጠቅምም። መሬት ላይ ያለውንም እውነታ የካደ ነውና ቢታረም መልካም ነው።
___
የሕያ ኢብኑ ኑህ
https://t.me/Yahyanuhe
1.2K viewsedited  18:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-11 21:47:02
1.1K views18:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-11 13:16:46 ኢየሱስ አምስት እንጀራና ሁለት አሳ ባርኮ በተአምር ከአምስት ሺህ ሰው በላይ እንዳበላ የሚሰብኩን የዘመኑ ነባያት አሁን ላይ ለተራቡ ወገኖቻችን ግን እንደ ተራው ምዕመን የእርዳታ ገንዘብ እያሰባሰቡ ነው።
347 views10:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-03 16:33:08
የቲክቶክ ላይቭ ትምህርታችን በዛሬው እለትም በአሏህ ﷻ ፍቃድ የሚቀጥል ይሆናል። በዛሬው ውይይታችን ከረሱል "ﷺ" ጋብቻዎች ጋር ተያይዞ የሚነሱ አጸፋዊ መከራከሪያዎችን /Counter Arguments/ በተመለከተ በሰፊው ለመወያየት እንሞክራለን። በአጀንዳው ዙሪያ ጥያቄ ያላችሁ ሙስሊሞችም ሆነ ሙስሊም ያልሆናችሁ ወገኖቻችን ጥያቄያችሁን ለማቅረብ መድረኩ ክፍት ነው። እንደተለመደው በየግሩፖች ሼር ማድረግዎን አይዘንጉ..!
..

ሒዳያ ኢስላማዊ ማዕከል
1.3K views13:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-28 21:04:23 https://vm.tiktok.com/ZMYUp6xbw/
817 views18:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-26 21:47:52
ከዚህ በታች ያለውን ጹሁፍ ከዛሬ 7 ወር በፊት ቦረናን በተመለከተ እዚህው ፌስቡኬ ጽፌው የነበረው ነው። ምንም ሳልጨማምር ከታች አስቀምጥላችኃለው፦
...
የመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን ዋና ቢሮ በፌስቡክ ገፁ 120 ሙስሊም በቦረና ማክፈሩን ነግሮናል። ቦረና ማለት በባለፈው አንድ ፖስት ላይ ስለሚከፍሩ ሰዎች ምስል ለጥፌ ከኦሮሚያ ነው በሚል በደፈናው ገልጨላችሁ የነበረው ቦታ ነው። ቦታው ድርቅና ረሀብ የሚፈራረቅበት ቦታ ከመሆኑ አንፃር ማኅበረሰቡ ለብዙ ችግር መጋለጡ አይቀሬ ነው። ይህ መከራ ደግሞ ሰርግና ምላሽ የሚሆንላቸው አካላት አሉ። እነዚሁ ሰዎች 120 ሰው አክፍረናል እያሉን ነው..! ወገኖቻችን ዲናቸውን እንዳያጡ ከገጠማቸው ችግርም እንዲላቀቁ ርብርብ የሚያስፈልግበት ጊዜ ላይ ነን..!
..
CC - Majlisa oromiyaa - የኦሮሚያ መጅሊስ
___
የሕያ ኢብኑ ኑህ
https://t.me/+A9f1rDgYDRYzYTY0
502 viewsedited  18:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-21 14:56:18
በሒዳያ ኢስላማዊ ማዕከል አማካኝነት በቋሚነት የሚተላለፈው የቲክቶክ ላይቭ ትምህርት ዛሬ ማክሰኞና የሚቀጥለው ጁሙዓ ከአቅም በላይ በሆነ ምክንያት አይኖርም። ለተፈጠረው ችግር ይቅርታ እየጠየቅን ፕሮግራሙ ከሚቀጥለው ሳምንት ጀምሮ በመደበኛ ሰአቱ በአሏህ ﷻ ፍቃድ የሚቀጥል ይሆናል።

ሒዳያ ኢስላማዊ ማዕከል
1.2K views11:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-20 14:59:41
ሰዎች ተሰባስበው ምግብ እየበሉ ሳለ አንድ በደዊን (ገጠሬ ሰው) ሰላምታ አቅርቦላቸው ከምግባቸው መብላት ጀመረ። ሰዎች አያውቁትምና ግራ ተጋብተው "ታውቀናለህ?" ብለው ጠየቁት። በደዊኑም ወደ ምግቡ እየጠቆመ "እሱን ነው የማቀው" አላቸው።
.
.
.
.
.
አንዳንዴ የማያውቁን ሁሉ ምግባችንን ሊበሉ ሲመጡ መለየት ካልቻልንማ አዕራቢዮቹ እኛ ነን።
1.0K views11:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ