Get Mystery Box with random crypto!

የሕያ ኢብኑ ኑህ - Yahya Ibnu Nuhe

የቴሌግራም ቻናል አርማ yahyanuhe — የሕያ ኢብኑ ኑህ - Yahya Ibnu Nuhe
የቴሌግራም ቻናል አርማ yahyanuhe — የሕያ ኢብኑ ኑህ - Yahya Ibnu Nuhe
የሰርጥ አድራሻ: @yahyanuhe
ምድቦች: እንስሳት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 13.06K
የሰርጥ መግለጫ

﷽ | Muslim | Theology | Comparative Religion | Philosophy | Student | Teacher |

Ratings & Reviews

3.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 5

2023-03-31 17:03:26
በአሁኑ ፈንድሬይዚንግ ጅማሯችን ከጎናችን ከነበሩት መካከል የምንጊዜም የስራችን ደጋፊ ጋዜጠኛ አብዱረሒም ዋነኛው ነበር። ምንም ጉዳይ ሲገጥመን ለመጠየቅም ለማማከርም የማላፍረው ወንድም ነው። ሚዲያውን 24 ሰአት ለኛ ስራዎች ክፍት ካደረጉልን የሚዲያ ሰዎች መካከል ግንባር ቀደሙ ነው። በአሁኑ ፈንድሬይዚንግም በማስተባበርና በማማከር ከጅማሮው ይኸው አብሮን አለ፥ ሰውን ያላመሰገነ አላህን አያመሰግንም ነውና ምስጋናችን ከልብ ነው፥ ጀዛከሏሁ ኸይራ
...
በተመሳሳይ ከአመታት በፌስቡክና በቴሌግራም የንጽጽር ስራዎች አብሮን የነበረው ወንድማችን ማሜ ከሚሴም ከጅምሩ ጀምሮ ጉዳዩን እንደራሱ ጉዳይ ወስዶ ሲያስተባብርና እንቅልፍ አጥቶ ሲለፋ ነበር። ስራውን በቅርበት ታውቀዋለህና ቁጭቱ ይዞህ ለምታደርገው ትግል አሏህ መልካም ምንዳውን ይክፈልልን።
...
ድጋፍ ማድረግ የምትፈልጉ ወንድምና እህቶች በቀጥታ የተቋሙ አካውንት ቁጥር ገቢ አድርጋችሁ ደረሰኝ ከዚህ በታች ባለው ግሩፕ ሼር ልታደርጉን ትችላላችሁ።
..
1000499318212
Hidaya Islamic Center
አጭር ቁጥር - 8212
..
ወደ ግሩፑ ለመቀላቀል፦
https://t.me/+Dy1d7s3_31s4NmQ0
483 views14:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-31 16:17:39
በትላንትናው እለት ወንድማችን ኡስታዝ ሙዓዝ ነዚፍ በቲክቶክ በኩል ለሒዳያ ኢስላማዊ ማዕከል ፕሮጀክቶች ድጋፍ የሚሆን ፈንድሬይዝ ሲያደርግ አምሽቷል። ተቋሙ የሚሰራቸው ስራዎች ሊደገፉ ይገባሉ "ተቋሙ የኔም ነው" በሚል ስሜት ከመነሻው ጀምሮ በትጋት እያገዙን ካሉ ወንድሞች መካከል ነው። አሏህ መልካም ምንዳህን ይክፈልህ፥ ተቋሙ የተሻለ ደረጃ ደርሶ የምታየውም ያድርግህ..! በሒዳያ አባላትና አሚሮች ስም ከልብ አመሰግናለሁ፥ ጀዛከሏሁ ኸይራ
...
ድጋፍ ማድረግ የምትፈልጉ ወንድምና እህቶች በቀጥታ የተቋሙ አካውንት ቁጥር ገቢ አድርጋችሁ ደረሰኝ ከዚህ በታች ባለው ግሩፕ ሼር ልታደርጉን ትችላላችሁ።
..
1000499318212
Hidaya Islamic Center
አጭር ቁጥር - 8212
..
ወደ ግሩፑ ለመቀላቀል፦
https://t.me/+Dy1d7s3_31s4NmQ0
618 views13:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-31 04:07:14
በግፍ ከፍ ያለ የለም..! እያንዳንዱ ግፍ ዘግይቶም ቢሆን ግፈኛውን ሲያዋርድ በእድሜያችን አይተናል። የዛሬ ግፍ የነገን ውርደት እንደሚፈጥርም ፈጽሞ አንጠራጠርም።

أَن لَّعْنَةُ اللَّهِ عَلَى الظَّالِمِينَ
1.3K views01:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-29 19:54:00
ወንድማችን አንዋር 51,930 ብር ለሒዳያ ኢስላማዊ ማዕከል ድጋፍ አድርጓል፥ በተመሳሳይ ወንድማችን አሚርም 3,000 ብር ገቢ አድርጓል። አሏህ አክበር። ወንድሞቻችንን በዱአችሁ አስታውሷቸው..!
...
ድጋፍ ማድረግ የምትፈልጉ ወንድምና እህቶች በቀጥታ የተቋሙ አካውንት ቁጥር ገቢ አድርጋችሁ ደረሰኝ ከዚህ በታች ባለው ግሩፕ ሼር ልታደርጉን ትችላላችሁ።
..
1000499318212
Hidaya Islamic Center
አጭር ቁጥር - 8212
..
ወደ ግሩፑ ለመቀላቀል፦
https://t.me/+Dy1d7s3_31s4NmQ0
1.8K views16:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-29 17:05:42
ትኩረቱን በሚሽነሪው እንቅስቃሴና እሱን በመመከት ላይ በማድረግ ላለፉት ሰባት አመታት ስራ ሲሰራ የቆየው ሒዳያ ኢስላማዊ ማዕከል ለወደፊቱ ደግሞ በርካታ ስራዎችን ለመስራት ፕሮጀክቶችን ቀርጾ እየተንቀሳቀሰ ይገኛል። ለነዚህ ስራዎቹ ደግሞ የናንተ ድጋፍ ወሳኝ ነው። ይህንን በተመለከተ ሀሙስ ማለትም መጋቢት 21/ MARCH 30 ከተራዊህ በኃላ ከምሽቱ 5 ጀምሮ በቲክቶክ ቀጥታ ስርጭት ተጋባዥ እንግዶችና ኡስታዞች በተገኙበት ፈንድሬይዚንግ ያደርጋል። በዚህ ፈንድሬይዚንግ ተሳታፊ በመሆን በአቅምዎት የዚህ መልካም ስራ ባለ አሻራ እንዲሆኑ ጥሪ አቅርበንለዎታል። የፈንድሬይዚንጉ ፕሮግራም በወንድማችን ኡስታዝ ሙዓዝ ነዚፍ የቲክቶክ አድራሻ ላይ የሚከናወን ይሆናል።

በፕሮግራሙ ላይ ላለፉት አመታት ሒዳያ የሰራቸው ስራዎችና የወደፊት እቅዶቹ በማዕከሉ አመራሮች የሚቀርብ ይሆናል። በዚህ ወሳኝ ታሪካዊ ስራ ላይ አሻራዎን ያሳርፉ..!

ድጋፍ ማድረግ የምትፈልጉ ወንድምና እህቶች በቀጥታ የተቋሙ አካውንት ቁጥር ገቢ አድርጋችሁ ደረሰኝ ከዚህ በታች ባለው ግሩፕ ሼር ልታደርጉን ትችላላችሁ።
..
1000499318212
Hidaya Islamic Center
አጭር ቁጥር - 8212
..
ወደ ግሩፑ ለመቀላቀል፦
https://t.me/+Dy1d7s3_31s4NmQ0
2.1K views14:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-28 15:07:47
ትላንት ቲክቶክ ላይ በኔትዎርክ ምክንያት እንዳሰብነው ባለመሄዱ ይቅርታ እንጠይቃለን። ተቋማችንን ለመደገፍ ወንድምና እህቶች የቻሉትን ድጋፍ እያደረጉ ሲሆን ጋዜጠኛ አብዱረሒም አህመድ የኒያውን 5,000 ገቢ አድርጎ ደረሰኝ ልኮልናል። በተመሳሳይ በቲክቶክ የምናውቀው ወንድማችን ማሜ ከሚሴም የኒያውን 5,000 ብር ገቢ አድርጓል። አሏሁ አክበር..! ድጋፍ ማድረግ የምትፈልጉ ወንድምና እህቶች በቀጥታ የተቋሙ አካውንት ቁጥር ገቢ አድርጋችሁ ደረሰኝ ከዚህ በታች ባለው ግሩፕ ሼር ልታደርጉን ትችላላችሁ።
..
1000499318212
Hidaya Islamic Center
አጭር ቁጥር - 8212
..
ወደ ግሩፑ ለመቀላቀል፦
https://t.me/+Dy1d7s3_31s4NmQ0
837 views12:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-28 00:22:49 www.tiktok.com/@hidaya_islamic_center/live?source=h5_m&_r=1&user_id=6808799369015067653&sec_user_id=MS4wLjABAAAAcx-4PtBeP3ifqCuGRERHAX4dk9PrgqWvCS1ABOBE_q_Y32JJDigtu9MeOOJHZKTO&utm_source=more&utm_campaign=client_share&utm_medium=android&share_iid=7214923339118708485&share_link_id=87b04878-3a81-4152-a52b-e1aa3646e488&share_app_id=1233&ugbiz_name=Live&ug_btm=b9081%2Cb4180
191 views21:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-27 16:13:10 አስገራሚ ታሪክ
...
በንጽጽራዊ ስራዎቻቸው የሚታወቁት ዶ/ር አሊ በአንድ ወቅት ሙስሊም ነበርኩ ካለ ፓስተር ጋር የነበራቸውን ገጠመኝ በንግግራቸው ይተርካሉ። ንግግራቸውን ቃል በቃል ባይሆንም ፍሬ ሀሳቡን ከታች ላስቀምጠው።
.
.
.
ግለሰቡን ሲያገኙት በንግግራቸው መሀል ለምን ውይይት አናደርግም የሚል ጥያቄ ያቀርቡለታል። ሰውየውን ፍቃደኛ ይሆንና ስለ ዝርዝር ጉዳይ እንዲወያዩ አንድ ሬስቶራንት ውስጥ ይቀጥራቸዋል። በጨዋታቸው መሀልም ፓስተሩ "እንድትገነዘበው የምፈልገው ነገር እኔ ነጋዴ ነኝ" ሲል መግቢያ ይሰጠውና ከክርክራቸው እንዴት በርካታ ገንዘብ ማግኘት እንደሚቻል በዝርዝር ያብራራለታል። ይህም የመጀመሪያ ቀን በአንድ ርዕስ ጉዳይ መጠነኛ ክርክር እንዲያደርጉና ሰው ፕሮግራሙን ሰምቶ ጉዳዩ ሞቅ ማለት ሲጀምር ደግሞ የመግቢያ ክፍያ አድርገውለት እያሟሟቁ በተከታታይ እንዲቀጥሉበት በዚህም በርካታ ገንዘብ እንደሚያገኙበት ሀሳብ አቀረበለት።
...
ዶ/ር አሊ ያልጠበቀው ነገር ስለነበር ግርምት ዋጠው። ይህ ሰው ምን ያክል ሀብታም እንደሆነ ከሚነዳው መኪናና ከአኗኗር ሁኔታው በቀላሉ ማስተዋል ቻለ። እውነትም ነጋዴ እንደሆነ ተረዳ፥ ግለሰቡ አሁን ድረስ ቁርአን እንደሚቀራ ወዘተም አስከትሎ ነገረው። በዚህ መሀል ዶ/ር አሊ ሰውየው በልቡ በእስልምና እውነተኝነት እንደሚያምንና ለገንዘብ ሲል ወደ ኩፍሩ እንደሄደ ገባው። ደፍሮም ጠየቀው "ሙስሊም ነህ እንዴ?" አለው፥ ሰውየውም በፈገግታ ብቻ አለፈው።
...
ከዚህ በፊት እንደጻፍኩት ሀገር ቤትም አንድ ቸርች የከፈተና የሙስሊም ስም ያለው ግለሰብ ለኡስታዝ አቡ ሐይደር "አምላክ እውነቱን ገልጦልሀል ክርክር ላንተ ምን ያደርግልሀል?" ሲል እንደነገረው ኡስታዝ ተገርሞ አጫውቶኛል። አሁን ላይ በዚህ ዘርፍ ያለው ቢዝነስ የደራ ነው። የሙሉ ጊዜ ስራ ተደርጎ ከፍተኛ ገቢ የሚያስገኝም ነው። በኛ ሀገርም ከላይ የጠቀስኩት አይነት አንዳንድ የቢዝነስ ሰዎች የዛን ቤተ እምነት አማኝ ስስ ልብ አጥንተው አዋጭ ቢዝነሳቸውን አጧጡፈውታል። አኼራ ቀልድ መስሏቸዋል፥ ሞት መዘጋጃ የሚሰጥም አድርገው አስበው ይሆናል። ከንቱ መታለል..!

وَمَا هَـٰذِهِ الْحَيَاةُ الدُّنْيَا إِلَّا لَهْوٌ وَلَعِبٌ ۚ وَإِنَّ الدَّارَ الْآخِرَةَ لَهِيَ الْحَيَوَانُ ۚ لَوْ كَانُوا يَعْلَمُونَ

ይህችም የቅርቢቱ ሕይወት መታለያና ጨዋታ እንጂ ሌላ አይደለችም፡፡ የመጨረሻይቱም አገር እርሷ በእርግጥ የዘላለም ሕይወት አገር ናት፡፡ የሚያውቁ ቢኾኑ ኖሮ፤ (ጠፊይቱን ሕይወት አይመርጡም ነበር)፡፡

[ ሱረቱ አል-ዐንከቡት - 64 ]
938 views13:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-27 16:13:08
870 views13:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-26 22:53:36 የሚሽነሪው እንቅስቃሴ መልኩን እየቀያየረ አሁንም ድረስ ቀጥሏል። ህዝባችን በተለይም በገጠር አካባቢ የሚገኘው ለዚህ የኩፍር እንቅስቃሴ በከፍተኛ ደረጃ ተጋላጭ ለመኾኑ አያጠያይቅም።

ሒዳያ ኢስላማዊ ማዕከል ይህንን እንቅስቃሴ ከመመከት አንጻር የራሱን አስተዋጽኦ ለማበርከት በንጽጽር ሃይማኖት ዘርፍ እንቅስቃሴ በሚያደርጉ ወንድምና እህቶች ትብብር የተቋቋመ ህጋዊ ተቋም ነው።

ተቋሙ በገጠሪቱ አካባቢዎች በተለይም ለአክፍሮቱ ኀይላት ተጋላጭ በኹኑ ስፍራዎች ላይ ለዱዓቶች የተለያዩ ጠቃሚ ስልጠናዎችን በመስጠትና በዚህ መስክ ትኩረት ያደረጉ ዳኢዎችን በመላክ ማኅበረሰቡን የማስተማር ስራዎችን ሰርቷል፥ ወደፊትም በኢትዮጵያ 16 ቦታዎች ላይ መሰል ስራዎችን ለመስራት አቅዷል።

የንጽጽር ሃይማኖት ስርአተ-ትምህርት ተቀርጾለት በቅጡ እንዲሰጥና ፍላጎት ያላቸው በአግባቡ የሰለጠኑ ተተኪዎች እንዲኖሩት ሰፊ እቅዶችን አዘጋጅቷል፤

ተቋሙ በንጽጽር የሀይማኖት ላይ መሠረታዊ ስራዎችን በመስራት በመጽሀፍት፣ በኦዲዮቪዥዋልና በድረ ገጽ በኩል ወቅቱን የጠበቀና አስፈላጊ ትምህርቶችን እየሰጠ ይገኛል፥ ለወደፊትም በሰፊው ለመስራት አቅዷል።

.
.
.
ተቋሙ እነዚህንና ሌሎችንም በርካታ ተያያዥነት ያላቸውን ተግባራት ከመሬት ለማውረድ ዕቅድ ነድፎ በመንቀሳቀስ ላይ ይገኛል። ይሕንን ስራ ከመሬት ለማውረድ ደግሞ የናንተ ድጋፍ ወሳኝነት አለው። ከዚህም አኳያ ሰኞ ማለትም መጋቢት 18/ March 28 በቲክቶክ ቀጥታ ስርጭት ተጋባዥ እንግዶችና ኡስታዞች በተገኙበት ፈንድሬይዚንግ ይደርጋል። በዚህ ፈንድሬይዚንግ መሰናዶ ተሳታፊ በመሆን የአቅምዎትን በማድረግ የዚህ መልካም ስራ ባለ አሻራ እንዲሆኑ ጥሪ አቅርበንልዎታል። መሰናዶው በሒዳያ ኢስላማዊ ማዕከል ኦፊሺያል የቲክቶክ አድራሻ በኢትዮጵያ ሰአት አቆጣጠር 4:30 ጀምሮ ከተራዊህ በኃላ የሚካሔድ ይሆናል።

ቲክቶክ ለሌላችሁ በቴሌግራም ሊንክ ጆይን ማለት ትችላላችሁ፦

https://t.me/+Dy1d7s3_31s4NmQ0

ቲክቶክ ሊንክ፦ https://bit.ly/3BZerNy

ሒዳያ ኢስላማዊ ማዕከል
779 viewsedited  19:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ