Get Mystery Box with random crypto!

የሕያ ኢብኑ ኑህ - Yahya Ibnu Nuhe

የቴሌግራም ቻናል አርማ yahyanuhe — የሕያ ኢብኑ ኑህ - Yahya Ibnu Nuhe
የቴሌግራም ቻናል አርማ yahyanuhe — የሕያ ኢብኑ ኑህ - Yahya Ibnu Nuhe
የሰርጥ አድራሻ: @yahyanuhe
ምድቦች: እንስሳት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 13.06K
የሰርጥ መግለጫ

﷽ | Muslim | Theology | Comparative Religion | Philosophy | Student | Teacher |

Ratings & Reviews

3.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 6

2023-03-26 22:53:31
754 views19:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-25 14:45:27
የረመዷን ማስታወሻ ❶

ما أغلق الله على عبد بابات بحكمته إلا فتح له بين برحمته!!

"ከጥበቡ አሏህ በባሪያው ላይ አንድ በር አይዘጋበትም፣ ሁለት ከእዝነት የሆነ በሩን የከፈተለት ቢሆን እንጅ"

አሏህ ﷻ የተቆለፉትን በሮች ይከፍትልናል ብቻ ሳይሆን ያልነበሩበትንም በሮች ሳይቀር ይፈጥርልናል!! ከበሮች ጀርባ ከተደበቁ ጉዳቶች ሊከላከልልን ደግሞ የተወሰኑ በሮችን ዘግቶብናል።

አንድ እድል ሲያልፈን ከልክ በላይ ሊያስጨንቀን አይገባም፥ ምክንያቱም ያጣነው ነገር በማጣታችን ብቻ ሊጎዳን አልያም ስላጣነው ሊያጎድለን ብቻ አይደለም፥ የፍላጎታችንን ገለል ያደረገልን ለእኛ ጥሩ ስላልሆነም ሊሆን ይችላልና።

والله يعلم وأنتم لا تعلمون
_______________
የሕያ ኢብኑ ኑህ
https://t.me/Yahyanuhe
97 views11:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-22 17:35:15 እንኳን ለተከበረው የረመዷን ወር አሏህ በሰላም አደረሳችሁ! አሏህ ﷻ ወሩን የዒባዳ ወር ያድርግልን! አሚን
1.1K views14:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-20 16:30:57 https://vm.tiktok.com/ZMYxhD2dx/
956 views13:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-20 14:53:04
ከሰሞኑ በሀላባ የምትገኝ አንድ የፕሮቴስታንት እምነት ተከታይ እስር ጋር ተያይዞ በርካታ ሀሳቦች ሲንሸራሸሩ ቆይተዋል። ከክስተቱ በተለየ በብዛት ከገጠሙኝ ፍርጃዎች መካከል "የሚፈውሰው ኢየሱስ ነው፥ በእስልምና ፈውስ የለም" የሚለው የአንበሳውን ድርሻ ይወስዳል። ይህንን አጀንዳ የተወሰነ ሜካፕ ቀብተው ስለ እስልምና አብዘተው ሲያወሩ የነበሩ የእምነቱ ሰዎችም ጥቂት የሚባሉ አልነበሩም።
...
በዛሬው የውይይት ርዕሳችን ይህንን አስመልክተው የሚነሱ ጥያቄዎችን በሚዛን እያስቀመጥን እንወያይባቸዋለን። "ስለ ክርስትናው የተነገረንስ ክሌም ምን ያክል እውነት ነው?" የሚለውንም እንፈትሻለን። እንደተለመደው ይከታተሉ፥ ለሌላውም ሼር ያድርጉ።
.
.
.
ትምህርቱን ለመከታተል ከዚህ በታች ባሉ ሊንኮች የቲክቶክ መገኛዎችን ፎሎው ማድረግ ይችላሉ፦

ሒዳያ ኢስላማዊ ማዕከል
https://bit.ly/3BZerNy

አቡ ዩስራ
https://bit.ly/3kkoaYU

ኢልያህ ማሕሙድ
https://bit.ly/3VlI6HQ

የሕያ ኢብኑ ኑህ
https://bit.ly/3Vs5O4V
1.2K views11:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-19 15:13:51 አንዳንድ ሰዎች አሉ፦
...
ሲሰሩ ድምጻቸውን አትሰማውም፣ በልፋታቸው ውጤት ውዳሴ አያጓጓቸውም ትችትም አያስጨንቃቸውም። ከአሏህ ውጭ ማንም እንዲያውቃቸውም አይፈልጉም። የገቡበት ስራ ሁሉ በረካ አለው። ብትቀርባቸው ከመልካም ነገራቸው ውጭ ምንም ክፉ አያገኘህም። ዘንበል ስትል ቀና ያደርጉሀል፤ በእገዛቸው ሁሉ የአንተን ምስጋናም ሆነ ውለታ አይፈልጉም። አሏህ ባሮች አሉት፥ ዱንያን ያሳመሩ መልካም ባሮች..!
999 views12:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-19 10:46:47
ይህ የፕሮቴስታንት እምነት ተከታይ የሆነ ሰው ኮልፌ የሙስሊም መካነ መቃብር ውስጥ ገብቶ ካልሰበኳችሁ ሲል ጠብ ተፈጥሮ እንደነበር ሰማሁ። በዛ እምነት አካባቢ ቅርብ ጊዜ እየተፈጠረ ያለውን አደገኛ የትምክህት አካሔድ ለተመለከተ ሰው ነገ መስጅድ ውስጥ ሚንበር ላይ ካልቆምንና በግድ ካልሰበክናችሁ ለማለታቸው ምንም ዋስትና የለንም..!
1 view07:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-16 10:51:37
ለረመዷን አቅመ ደካሞችን የወር አስቤዛ በመስጠት የማስፈጠር ስራችን ዘንድሮም በአሏህ ﷻ ፍቃድ እናካሒዳለን። በዚህ መልካም ተግባር ላይ ተሳታፊ ለመሆን ለአንድ ቤተሰብ ወርሐዊ ወጭ 3,000 ብር ሲሆን የአቅምዎን በመደገፍ ማስፈጠር ይችላሉ።

ድጋፍዎን ለማድረግ በሒዳያ ኢስላማዊ ማዕከል አካውንት ገቢ በማድረግ ደረሰኙን በሒዳያ የቴሌግራም ቁጥር መላክ ይችላሉ፦

1000499318212
Hidaya Islamic Center
አጭር ቁጥር - 8212

ደረሰኙን ለመላክ በቴሌግራም፦
t.me/Hidayaislamiccenter
1.4K views07:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-15 19:38:40 ገሀዱን በጩኸት ለመሸፈን የሚደረግ ጥረት
...
ከሰሞኑ በሀላባ ሊዲያ ተብላ በምትጠራው ተማሪ እስር ጉዳይ በባለፈው ያገኘሁትን መረጃ ከሰጠሁ በኃላ በተለይ በቲክቶክ በኩል በርካታ የተንጋደዱ መረጃዎች የሰራሁት ቪዲዮ ኮሜንት ላይ ሲጻፉ አይቻለሁ። ኮሜንቶቹ ከስድብ ጋር ተቀላቅለው በርካታ በመሆናቸው ሁሉንም ማየት ባልችልም የተወሰኑት ላይ ግን ከዚህ በታች እርምት ለመስጠት እሞክራለሁ፥ መጨረሻ ላይም በሒደቱ የታዘብኩትን አስቀምጣለሁ፦

1/ የወደቀችው መስሊም ልጅ "ኢየሱስ ጌታ ነው" ብላለች በሚል የተገለጸው ስህተት ነው። ልጆቹ ከወደቁ በኃላ ይህንን የተናገረችው ሊዲያ እንጅ ሙስሊም ተማሪዎች አይደሉም። በዚህ በኩል የተሰራጨው መረጃ አሳሳችና ሙስሊሙ ስለ ኢየሱስ እንዲመሰክር አድርጋለች የሚል አግናኝ ትርክት ለመፍጠር የተሰራጨ ቅጥፈት ነው። ለነገሩ በዚ በኩል የራሳቸው ሰዎችም ስህተት መሆኑንና ይህንን የተናገረችው ሊዲያ እንደነበረች ሲገልጹ ነበር።
...
2/ በማረሚያ ቤት ተገኝተው እሷን የጠየቁ ሰዎች በምን አግባብ ስልክ ይዘው ገብተው ፎቶ እንዳነሱ በግሌ ግርምትን ፈጥሮብኛል? የሀላባ ማረሚያ ቤት መሠል ህገወጥ ስራ ሲሰራ መረጃው አልነበረውም? ስለ ህግ ሲሟገቱ የነበሩ ሰዎችስ መሠል ህገወጥ ስራ ላይ ሲሰማሩ ማየት አያስተዛዝብም? እውነት ውግንናቸው ለህግ ቢሆን ህግን የመጣስ እብሪት ውስጥ መግባታቸው ስለማንነታቸው የሚጠቁመን ነገር የለም?
...
3/ እርቃኗን ተደርጋ ተመርምራለች የሚለውን በተመለከተም ጋዜጠኛ ታሪክ አዱኛ የዞኑን ፖሊስ አዛዥ ዋና ኢንስፔክተር ታረቀኝ ጉራቻ ባነጋገረችበት ወቅት "ፍጹም ሀሰት" መሆኑን ገልጸውላታል። ሆን ተብሎ የሀላባን ስም ለማጥፋት የተፈጠረ ትርክት መሆኑንም ነግረዋታል።
...
4/ ልጅቷ እድሜዋ ለእስር አይበቃም በሚል የሚደረገውን ክርክር በተመለከተም የህግ ባለሙያዎችን ሲያከራክር የቆየ ጉዳይ ስለሆነ በሱ ጉዳይ ዝርዝር ማብራሪያ አልሰጥም። ልጅቷ 10ኛ ክፍል ከመሆኗ አንጻር በትንሹ እድሜዋ 15 እና ከዚያ በላይ መሆኑ ግልጽ ነው። ይህ ሲሆን ደግሞ ህጉ ምን ይላል? ብለን ከጠየቅን 18 አመት ባይሞላትም ከ15 አመት በላይ ከሆነች በመደበኛው የህግ ሂደት ጉዳዮ እንደሚታይ የሀገሪቱ የወንጀለኛ መቅጫ ህግ ይገልጻል (አንቀጹ ከታች ተያይዟል)

5/ እነዚህ ሰዎች ካለ እድሜዋ ታሰረች በሚል እውነት በሰብአዊነት ከነበረ ትግላቸው ከወራት በፊት መሠል ተማሪዎች ጉራጌ ዞን ጉንችሬ ላይ በሒጃብ ምክንያት ተማሪዎቹ ለበርካታ ቀናት ሲታሰሩ የት ነበሩ? በእርግጥ የጥያቄያቸው ሞቲቭ ሰብአዊነት ስላልሆነ ጥያቄየ ቀሽም ሊሆን ይችላል። ግን እውነታው መታወቅ አለበት።

❐ የግል አስተያየቴ

በዚህ ዙሪያ የታዘብኩትን እውነታ ያለምንም ማሽሞንሞን ማስቀመጥ እፈልጋለሁ። ይኸውም አብዛኛው ሰው ሀላባን እየሰደበና እየወቀሰ ያለው እንዲሁ በዚህ ክስተት ብቻ አይደለም። የተጠና ተግባር ነው እየተፈጸመ ያለው። ሀላባ የሙስሊም ሀገር ናት ተብሎ ስለሚታሰብ ማንነታቸውን ያማከለ ውግዘት ነው እየተሰነዘረ ያለው። የአንዳንዶቹ ግልብ ፍርጃ ቆርቁሮን የምንናገረው ሀላባ ሁነን አልያም ስለ ጉዳዩ ከሚታወቀው እውነታ የዘለለ የተለየ እውቀትና መገንዘብ ኑሮን አይደለም። መጨነቁ ስለ ህግ ሳይሆን የሀላባ ህዝብ እሴት አድርገው እስልምና ላይ ዘመቻ የመክፈት ሴረኝነት እንደሆነ ስለገባን ነው። ጉዳዩን ከህግ አንፃር እንዲፈታ ነጻ ሁነው ቢጠይቁ ማንም ተቃውሞም ትችትም ባላቀረበ ነበር። የአብዛኛው ፍርጃ ግን "ሀላባ የሸሪዓ ዞን ናት" የሚል ሆንተብሎ እስልምናን የማጠየም ስትራቴጂ ስለሆነ ነው። ይህንን ደግሞ ሀላባም ላይ ሆነ ሌላ የትም ቦታ ስተገብሩት ሽታው ስለሚታወቀን ያለምንም ማመንታት ስለዲኑ ስንል ቆሻሻውን ነጥሎ ለመለየት አብረናቸው እንቆማለን።
...
___
የሕያ ኢብኑ ኑህ
https://t.me/Yahyanuhe
925 views16:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-15 19:38:37
896 views16:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ