Get Mystery Box with random crypto!

🗣 ወቅታዊ_መረጃ 🇪🇹

የቴሌግራም ቻናል አርማ wektawi1mereja — 🗣 ወቅታዊ_መረጃ 🇪🇹
የቴሌግራም ቻናል አርማ wektawi1mereja — 🗣 ወቅታዊ_መረጃ 🇪🇹
የሰርጥ አድራሻ: @wektawi1mereja
ምድቦች: ፖለቲካ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 12.46K
የሰርጥ መግለጫ

This is national and international News and advertising channel
🇪🇹🇪🇹🇪🇹"ስለኢትዮጲያ ሳትሰማ ያሳለፍከው ቀን እንደባከነ ይቆጠራል" 🇪🇹🇪🇹🇪🇹
⏭▶️➡️ ሀገራዊና አለም አቀፋዊ ዜናዎችን በፍጥነት ይደርሶታል።🔚

Ratings & Reviews

3.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

2

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 5

2023-04-24 17:22:43
በአዲስ አበባ በሚገኙ 153ቱም ነዳጅ ማደያዎች የነዳጅ ሽያጭ በዲጂታል ክፍያ ሥርዓት እየተከናወነ ነው

ኢትዮ ቴሌኮም

በአዲስ አበባ በሚገኙ 153ቱም ነዳጅ ማደያዎች የነዳጅ ሽያጭ በዲጂታል ክፍያ ሥርዓት እየተከናወነ መሆኑን ኢትዮ ቴሌኮም አስታወቀ።

በአዲስ አበባ በሚገኙ ሁሉም ነዳጅ ማደያዎች ባለሙያዎች እና የቴሌብር ወኪሎች ተሰማርተው አስፈላጊውን እገዛ በማድረግ ላይ እንደሚገኙ ኢትዮ ቴሌኮም ገልጿል።

በአዲስ አበባ ነዳጅ ማደያዎች ዛሬ ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ በሆነው የዲጂታል ክፍያ ሥርዓት ደንበኞች በቀላሉ ክፍያቸውን በቴሌብር እየፈጸሙ እንደሆነም ተገልጿል።

ደንበኞች ነዳጅ ለመቅዳት ሲሄዱ በቅድሚያ የቴሌብር አካውንት ከሌላቸው ቴሌብር ሱፐርአፕን http://xn--onelink-om4a.to/75zfa5 በማውረድ ወይም *127# በመደወል በቀላሉ ሂደቱን በመከተል እንዲመዘገቡ ከቴሌብር ጋር በተሳሰሩ 20 ባንኮች፣ በአገልግሎት ማዕከሎች ወይም በቴሌብር ወኪሎች በኩል በቂ ገንዘብ ወደ ቴሌብር አካውንት እንዲያስተለልፉ እና በየነዳጅ ማደያዎቹም በሚገኙ ወኪሎች በኩል ገንዘብ ገቢ በማድረግ የነዳጅ ክፍያን በቀላሉ በቴሌብር መፈጸምም እንደሚችሉ ኢትዮ ቴሌኮም በማኅበራዊ ሚዲያ ገጹ አስታውቋል።

ተጨማሪ መረጃዎችን ለማየት የቴሌግራም ገፃችንን ይመልከቱ!
https://t.me/wektawi1mereja
424 views14:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-23 19:48:48
ኦነግ ሸኔና የኢትዮጲያ መንግስት በታንዛኒያ ከማክሰኞ ጀምሮ ንግግር እንደሚጀምሩ ጠ/ሚ አብይ አህመድ ተናገሩ

ይህ የተነገረው በዛሬው እለት በተካሄደው "ጦርነት ይብቃ፣ ሰላምን እናጽና" የምስጋና እና የእውቅና መረሀ ግብር በወዳጅነት አደባባይ በተከነወነው መርሃ ግብር ነው።ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ(ዶ/ር) ከኦነግ ሸኔ ጋር የፊታችን ማክሰኞ በታንዛኒያ ንግግር እንደሚጀምር በመድረኩ ገልፀዋል።

በሰሜኑ የኢትዮጵያ ክፍል የነበረው ግጭት በሰላም ስምምነቱ እልባት እንዲያገኝ ቁልፍ ሚና ለነበራቸው አካላት የማመስገንና የእውቅና መረሀ ግብር በወዳጅነት አደባባይ ተካሂዷል።

በመረሀ ግብሩ ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ እና ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸውን ጨምሮ አፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ሙሳ ፋኪ ማህመት፣ የሁሉም ክልል ርዕሰ መስተዳደሮች፣ የሀገር ሽማግሌዎች ፣ የሀይማኖት አባቶች፣ አንጋፋ የኪነ ጥበብ ባለሙያዎች እና ሌሎችም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።

https://t.me/wektawi1mereja
1.6K views16:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-23 17:35:09
#ሰበር ዜና..!

የቀድሞው የሱዳን መሪ #አል_በሽር ከእስር ማምለጠቸው እየተነገረ ነው።

ለትኩስ መረጃዎችን የቴሌግራም ገፃችንን ይመልከቱ!

https://t.me/wektawi1mereja
1.7K views14:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-22 18:06:30
#SUDAN

የሱዳን ተዋጊ ኃይሎች የተኩስ አቁም ቢያውጁም ውጊያው አሁንም መቀጠሉ ታውቋል ፤ ሀገራት ዜጎቻቸውን ከሱዳን ለማስወጣት ሩጫ ላይ ናቸው።

ትላንት የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ኃይል (RSF) የዒድ አልፈጥር በዓልን ምክንያት በማድረግ የ72 ሰዓታት የተኩስ አቁም ማወጁ፤ የሱዳን ጦርም ምሽት ላይ በተኩስ አቁሙ እንደተስማማ አሳውቀው እንደነበር ይታወሳል።

ነገር ግን ዛሬም በሱዳን የተለያዩ ቦታዎች ውጊያ መኖሩ ተሰምቷል። በካርቱም ካለፉት ቀናት ጋር ሲነፃፀር በተለየ መልኩ የተኩስ ድምፅ ቀንሶ ታይቷል።

በሌላ በኩል ፤ ሀገራት ዜጎቻቸውን ከሱዳን ለማስወጣት ሩጫ ላይ ናቸው። ተዋጊ ኃይሎቹም የውጭ ዜጎች እንዲወጡ ለማመቻቸት ቃል ገብተዋል ተብሏል።

የሱዳን ጦር ፤ የውጭ ዜጎች እና ዲፕሎማቶች ከአሜሪካ ፣ ዩናይትድ ኪንግደም፣ ፈረንሳይ እና ቻይና በጦር አውሮፕላኖች ከካርቱም ኤርፖርት የማስወጣት ስራ በሰዓታት ውስጥ ይጀምራል ብሏል።

ከዚህ ባለፈ በሀገሪቱ የሚገኙ የሳዑዲ አረቢያ ዲፕሎማቶች ከካርቱም ወደ ፖርት ሱዳን ከዚያም ወደ ሳዑዲ አረቢያ እንዲወጡ መደረጉን አስታውቋል። የጆርዳን ዲፕሎማቶችም ዛሬ ወደበኃላ ላይ በተመሳሳይ መንገድ ከአገሪቱ ይወጣሉ ሲል ገልጿል።

በሱዳን የተካሄደ ያለው ውጊያ እጅጉን የከፋው በትልልቅ ከተሞች፣ የዜጎች የመኖሪያ መንደሮች፣ የስራ ቦታዎች  ላይ እየተደረገ መሆኑ ሲሆን የሀገሬው ዜጋ እና የሌሎችም ሀገራት ዜጎች ያለ ውሃ ፣ ምግብ ፣ መብራት ቤታቸው ውስጥ ከሳምንት በላይ እንዲቀመጡ አድርጓል።

https://t.me/wektawi1mereja
588 views15:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-22 17:54:18
አብይ አህመድ ሰሞኑን ነቀምት ህዝብ ሰብስቦ ያደረገዉ ንግግር።

"እናንተ ወደኛ ኑ እንጂ ለሌላው በጭራሽ አታስቡ።ሌላው ያወራሉ ፤እኛ ግን ለኦሮሞ ነው የምንሰራው።እየሰራን ነው።ይሔ ብልጽግና የኦሮሞ መንግስት ነው።በዚህ ወቅት ስልጣኑ ከእጃችን ከወጣ በመቶ አመት ውስጥ አናገኘውም።

በሰሜን በኩል ያሉት እያንገራገሩ ነው። እኛ ተደራጅተን እነሱን ማንበርከክ ካልቻልን እኛ ስልጣን ላይ ያለነው ብቻ ሳይሆን የምንጎዳው ኦሮሞ የሆነው ሁሉ ነው።

በወለጋ በርካታ የተፈናቀሉ አሉ። እነዛ የተፈናቀሉት ለኛ የሚተኙልን ይመስላችኋል!?

ስለዚህ የብልጽግና መንግስት አትጠራጠሩ።የኦሮሞ ነው።የምንሰራውም ለኦሮሞ ነው። እናም እናንተ ወደኛ ኑ እንጂ ለሌላው በጭራሽ አታስቡ! ይስተካከላል።

ወደኛ መምጣት፣ እኛን ማዳመጥና መደማመጥ ካልቻልን፤ ስልጣናችንን ካጣን እኛ ብቻ ሳይሆን አጠቃላይ ኦሮሞ የሆነ ሁሉ ለከፉ ችግር ይጋለጣል።”

ለትኩስ መረጃዎችን የቴሌግራም ገፃችንን ይመልከቱ!
https://t.me/wektawi1mereja
637 views14:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-21 00:12:56 ዒድ ሙባረክ

የሸዋል ወር ጨረቃ  በሳኡዲ አረበያ በመታየቷ የኢድ አል ፊጥር በዓል በነገው ዕለት ጁምዓ ሚያዝያ 13/ April21/2023 መሆኑ ታውቋል።

እንኳን ለ1 ሺህ 444ኛው የዒድ አልፈጥር በዓል በሰላም አደረሳችሁ።

https://t.me/wektawi1mereja
568 views21:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-19 08:27:15
የግብፅ ወታደሮች በሱዳን የተገኙት ለወታደራዊ ስልጠና ነው ሲሉ ፕሬዝዳንት አል ሲሲ አስተባበሉ

በሱዳን የግብፅ ወታደሮች በፈጥሮ ደራሽ ኃይሉ ተይዘዋል


የግብፅ ፕሬዝዳንት አብዱል ፈታህ አል ሲሲ አንዳንድ የግብፅ ወታደሮች በጎረቤት ሀገር ሱዳን መኖራቸውን የገለፁ ሲሆን የግብፅ ወታደሮች ግን በቀጠለው ጦርነት ውስጥ እንደማይሳተፉ አረጋግጠዋል። በሱዳን ጦር ሠራዊቱ እና በፈጣን ድጋፍ ሰጪ ሃይሎች (አርኤስኤፍ) ወታደራዊ ቡድን መካከል በተፈጠረው ግጭት ወደ የትኛውም ወገን የማይሰለፉ ናቸው፤ በወታደራዊ ስልጠና ላይ እንደነበሩ ተናግረዋል ።

አርኤስኤፍ ቅዳሜ እለት በሰሜን ሱዳን በሚገኘው ሜሮዌ ወታደራዊ አየር ሰፈር የግብፅ ወታደሮች የሚያሳይ ቪዲዮ በትዊተር ገፁ ላይ ማጋራቱ ይታወሳል። አል ሲሲ "በሱዳን የሚገኙ የግብፅ ወታደሮችን በፍጥነት ወደ ሀገር ውስጥ እንደምናመጣቸው ተስፋ አደርጋለሁ" ሲሉ ተናግረዋል።

ፕሬዝዳንቱ ይህንን የገለፁት  ከመከላከያ ሰራዊት ጠቅላይ ምክር ቤት ጋር ባደረጉት ውይይት መሆኑን በከፊል በግል ባለሀብት በሚተዳደረው ኤክስትራ ኒውስ ቲቪ ላይ የተላለፈው መረጃ ያሳያል። ግብፅ በሱዳን "የውስጥ ጉዳይ" ውስጥ ጣልቃ እንደማትገባ ገልፀው ነገር ግን "ተኩስ እንዲያቆሙ ለማበረታታት" በቡድኖች መካከል ያለውን የሽምግልና ሚና መጫወት እንደምትችል ተናግረዋል።
https://t.me/wektawi1mereja
2.3K views05:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-18 09:05:09 #SUDAN

በሱዳን የEU አምባሳደር ጥቃት ተፈፀመባቸው።

በሱዳን ካርቱም ሚገኙት የአውሮፓ ህብረት (EU) አምባሳደር በመኖሪያ ቤታቸው ጥቃት እንደተፈፀመባቸው ተሰማ።

አምባሳደሩ ጥቃት እንደተፈፀመባቸው ያሳወቁት የአውሮፓ ህብረት ከፍተኛ ዲፕሎማት ጆሴፕ ቦሬል ናቸው (በትዊተር ገፃቸው)።

ቦሬል ስለ ጥቃቱ ምንም አይነት ዝርዝር ነገር ባይገልጹም አምባሳደሩ ግን " ደህና ናቸው " ብለዋል።

የዲፕሎማቲክ ቦታዎችን እና ሰራተኞችን ደህንነት ማስጠበቅ የሱዳን ባለስልጣናት ቀዳሚ ኃላፊነት ነውም ሲሉ ገልጸዋል።

ምንም እንኳን ቦሬል ፤ በሱዳን የአውሮፓ ህብረት አምባሳደርን ስም ባይፅፉም ስማቸው አይዳን ኦሃራ የሚባሉ ሲሆን የ #አየርላንድ ዲፕሎማት ናቸው።

ቦሬል ካርቱም ውስጥ የተፈፀመው ጥቃት ፤ በሌሎች ሀገራት የሚሰሩ ዲፕሎማቶች ጥበቃን የሚደነግገውን  የተመድ ስምምነት የ " ቪይና ኮንቬንሽን " በእጅጉ የጣሰ ነው ብለዋል።

በሌላ በኩል ፥ የአውሮፓ ህብረት ቃል አቀባይ ናቢላ ማስራሊ ለAFP በሰጡት ቃል " የሰራተኞች ደህንነት ቅድሚያ የምንሰጠው ጉዳይ ነው " ብለዋል፤ የተፈፀመውን ጥቃት ተከትሎ የአውሮፓ ህብረት ልዑካን ቡድን ከካርቱም እንዲወጣ እንዳልተደረገ ተናግረዋል።

ቃል አቀባይዋ ፤ በሱዳን ያለው የፀጥታ እና ደህንነት ሁኔታ እየተገመገመ ነው ብለዋል።
https://t.me/wektawi1mereja
827 views06:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-18 08:56:53
በሱዳን…!

"…በሱዳን የፕሬዝዳንት ኢሳይያስ አፈወርቂ ወዳጅ እንደሆኑ የሚነገርላቸው የሱዳን ልዩ ኃይል ፈጥኖ ደራሽ ጦር መሪ የጄነራል ሄሜንቲ የሚመራው ቡድን ዋነኛውን የሱዳን ፕሮፓጋንዳ ማሽን የሆነውንና በእምዱሩማን የሚገኘውን የሱዳን ብሮድካድካስቲንግ ኮርፖሬሽን የሬዲዮና ቴሌቪዥን ማሰራጫው ሕንፃ በቁጥጥር ስር ማዋላቸው ተሰምቷል።

በተያያዘ ዜና ሄማቲ “ማርከን የለቀቅናቸው የግብፅ አየር ሀይሎች አሁን እየደበደቡን ነው። 31 ጊዜም አየሮቹ የተነሱት ከግብፅ ነው። ሂሳብ እናወራርዳለን። ረመዳን ነው እያሉ እያለቀሱ ስንቸገር ነበር የለቀቅናቸው። ነገ ግን ብንማርካቸው አንለቃቸውም። አሁን እየተደራጀን ነው። እየተከላከልን እንጅ የምንጠራበትን የጃንጃዊ ጥቃታችንን አልጀመርንም። ቡረሀን ደውሎ ውጊያ እናቁምና አብይ አህመድና መሀመድ ቢን ዛይድ ያደራድሩን ብሎ ለፀሀፊየ ነግሯታል። እጅህ ላይ የፍትህ ገመድ ሳላጠልቅ አልደራደርም ብየዋለሁ። ግብፅ ግን እድሉን ተጠቅማ የሱዳንን ተቋሞች  በአየር ጥቃት እያወደመች ነው።” ሲል ተናግረዋል።

ለትኩስ መረጃዎችን የቴሌግራም ገፃችንን ይመልከቱ!
https://t.me/wektawi1mereja
841 views05:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-17 22:08:09 አጫጭር መረጃዎች በሱዳን ወቅታዊ ሁኔታ ዙሪያ

በካርቱም የሚገኘው የአል-ሻባብ ሆስፒታል ረዳት ዳይሬክተር አል-ታይብ አብደልራህማን በጦር ሠራዊቱ ማዘዣ ሕንጻ አቅራቢያ ያለው ሆስፒታሉ የጥቃት ሰለባ መሆኑን ተናግረዋል። “ሆስፒታሉ በዛሬው እለት ብቻ አራት ጊዜ በቦምብ ተመቷል በዚህም ሰራተኞችና ህሙማን ቆስለዋል" ሲሉ ተናግረዋል።

በሱዳን መከላከያ እና የፈጣን ድጋፍ ኃይሎች (RSF) በሚል ከተሰየመው ቡድን መካከል ለሶስት ቀናት በቀጠለው ውጊያ የሱዳን ቲቪ (SRTC) እና የሱዳን ራዲዮ ከትላንትና ጀምሮ ከአየር ላይ የወረዱ ሲሆን መንግስታዊው የቴሌቪዥን ጣቢያ የሀገር ፍቅር ይዘት ያላቸውን ሙዚቃዎች በማጫወት ላይ ይገኛል።

የሱዳን ጦር ቃል አቀባይ ናቢል አብዱላህ የጦሩ ሰራዊት በአርኤስኤፍ ቦታዎች ላይ የአየር ጥቃት መጀመሩን ተናግረዋል።ነገር ግን ጥቃቱ ምን ተጽዕኖ እንዳሳደረ እስካሁን አልታወቀም። "ግጭቱን በአጭር ጊዜ ውስጥ ለማስቆም እየሰራን ነው ምክንያቱም ዜጎችን ለአደጋ እንዳይጋለጹ ከፍተኛ ፍላጎት አለን" ብለዋል።

የሱዳን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የሀገሪቱ ጦር አዛዥ አል-ቡርሃን የፈጣን ድጋፍ ሰጪ ሀይሎች(RSF) በመባል የሚታወቀውና በጄኔራል ዳጋሎ የሚመራው ኃይል እንዲፈርስ ትእዛዝ መስጠታቸውን እና በመላው ሀገሪቱ በሚካሄደው ጦርነት አማፂ ቡድን ተብሎ መፈረጁን ይፋ አድርገዋል።

የሱዳን ጦር መሪ ጄኔራል አብደል ፋታህ አል ቡርሃን ለስካይ ኒውስ እንደተናገሩት ወታደሮቻቸው የፈጣን ድጋፍ ሰጪ ልዩ ሀይሉ እንደሚያሸንፉ የተናገሩ ሲሆን ለውይይት ግን ክፍት መሆናቸውን ተናግረዋል። በካርቱም የሚገኙ ነዋሪዎች እንቅልፍ ማጣታቸውንና ምግብና ውሃ እጥረት መኖሩን ገልፀዋል።

ዋይት ሀውስ በሱዳን የሚደረገው ውጊያ አፋጣኝ የተኩስ አቁም ጥሪ ያቀረበ ሲሆን የዩናይትድ ስቴትስ ባለስልጣናት ከወታደራዊ መሪዎች ጋር ግንኙነት እንዳላቸው ገልጿል።

በሱዳን ቁልፍ ከተማ የሆነችውን ሜሮዌ ለመያዝ ከአውሮፕላን ማረፊያው በስተምዕራብ በኩል የከተማ ውጊያ እየተካሄደ መሆኑ ተሰምቷል።

https://t.me/wektawi1mereja
254 views19:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ