Get Mystery Box with random crypto!

🗣 ወቅታዊ_መረጃ 🇪🇹

የቴሌግራም ቻናል አርማ wektawi1mereja — 🗣 ወቅታዊ_መረጃ 🇪🇹
የቴሌግራም ቻናል አርማ wektawi1mereja — 🗣 ወቅታዊ_መረጃ 🇪🇹
የሰርጥ አድራሻ: @wektawi1mereja
ምድቦች: ፖለቲካ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 12.46K
የሰርጥ መግለጫ

This is national and international News and advertising channel
🇪🇹🇪🇹🇪🇹"ስለኢትዮጲያ ሳትሰማ ያሳለፍከው ቀን እንደባከነ ይቆጠራል" 🇪🇹🇪🇹🇪🇹
⏭▶️➡️ ሀገራዊና አለም አቀፋዊ ዜናዎችን በፍጥነት ይደርሶታል።🔚

Ratings & Reviews

3.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

2

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 8

2023-04-09 23:27:00 በወቅታዊ ጉዳይ ከአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) የተሰጠ መግለጫ

የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ ከአማራ ልዩ ኃይል ጋር በተያያዘ የገዥው ፓርቲ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ያሳለፈውን ውሳኔ እና ውሳኔውን ለማስፈጸም እየወሰዳቸው ያሉ እርምጃዎችን በሚመለከት በተከታታይ አቋሙን ግልጽ ሲያደርግ መቆየቱ ይታወቃል፡፡ እንዲሁም የአማራ ክልልን ለከፍተኛ አለመረጋጋት እና የጸጥታ መድፈረስ ያጋለጠው ፣ ፍጹም ኃላፊነት የጎደለው እና አደገኛ የሆነው የገዥው ፓርቲ ውሳኔ እስኪቀለበስ ድረስ እና ተገቢው መፍትሄ እስኪገኝ ድረስ ድርጅታችን አብን አስፈላጊውን ጥረት እና ትግል እንደሚያደረግ ማሳወቁ ይታወቃል፡፡ ድርጅታችን አብን ሁኔታውን በከፍተኛ ትኩረት እየተከታተለ ሲሆን ፣ ገዥው ፓርቲ እና የፌዴራሉ መንግስት ስህተቱን ከማረም እና መፍትሄ ከማፈላለግ ይልቅ ከጥፋት ላይ ጥፋት እየጨመረ ችግሩን እያወሳሳበ እና ክልሉን ለከፍተኛ አለመረጋጋት እና የጸጥታ መደፍረስ እየዳረገው ይገኛል፡፡ በዛሬው እለትም በበርካት የአማራ ክልል ከተሞች የተቃውሞ ሰልፎች የተካሄዱ ሲሆን ፣ በተለያዩ አካባቢዎች መደበኛ እንቅስቃሴዎች ተስተጓጉለው ውለዋል፡፡ በተለይም በራያ ቆቦ ከተማ ውስጥና በዙሪያው በከባድ መሳሪያ ጭምር የታገዘ ተኩስ ሲደረግ የዋለ ሲሆን ይህ በከተሞች ውስጥና አቅራቢያ የሚደረግ የከባድ መሳሪያ ተኩስ በአስቸኳይ እንዲቆም እናሳስባለን።

ዛሬ ሚያዚያ 1 ቀን 2015 ዓ.ም ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ (ዶ/ር) “ከጊዚያዊ መፍትሄ ዘላቂ ጥቅም አይገኝም” በሚል በስማቸው ባወጡት መግለጫ ፣ “ዘላቂ መፍትሄ” ብለው የሰየሙትን የአማራ ክልል ልዩ ኃይልን ትጥቅ የማስፈታት ውሳኔ “ዋጋ ተከፍሎም ቢሆን ተግባራዊ እንደሚደረግ እና የህግ ማስከበር እርምጃ እንደሚወሰድ” በመግለጽ ፓርቲያቸው ያሳለፈው ውሳኔ በአማራ ክልል ለፈጠረው አለመረጋጋት እና የጸጥታ መድፈረስ ኃላፊነት ሳይወስዱ ቀርተዋል፡፡ ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትሩ በመግለጫቸው የልዩ ኃይል አባላትን ወደ ሌሎች የጸጥታ መዋቅሮች እንዲገቡ ለማድረግ ተገቢው ዝግጅት እንደተደረገበት ፣ የልዩ ኃይል አመራሮች እና አባላት እንደ ተወያዩበት ፣ የልዩ ኃይል አባላት ወደ መረጡት ተቋም (የሀገር መከላከያ ሠራዊት ፣ የፌዴራል ፖሊስ  ወይም የክልል ፖሊስ) ለመቀላቀል ምርጫ እንደተሰጣቸው እና ውሳኔው በሁሉም ክልሎች የሚገኙ ሁሉንም የልዩ ኃይል ፖሊሶችን የሚመለከት መሆኑን ገልጸዋል፡፡

ነገር ግን የማስፈጸሚያ እቅድ ነው የተባለው ሰነድ እንኳ በፌዴራል መንግስት ባለስልጣናት ደረጃ ውይይት የተደረገበት ትናንት ቅዳሜ መጋቢት 30 ቀን 2015 ዓ.ም በአዲስ አበባ ከተማ በፌዴራል ፖሊስ ዋና መስሪያ ቤት መሆኑ ሲታይ ፣ ለአማራ ክልል ልዩ ኃይል አባላት “ትጥቃችሁን ፍቱ” ከሚል ትዕዛዝ በቀር እንኳን ምርጫ መረጃ እንኳን የሰጣቸው አካል እንደሌለ የሚታወቅ መሆኑ እና ከአማራ ክልል በስተቀር በየትኛውም ክልል ልዩ ኃይሎችን ትጥቅ የማስፈታትም ሆነ ወይም ጠቅላይ ሚኒስትሩ እንደሚሉት “ወደ ተለያዩ ተቋማት የማስገባት” እንቅስቃሴ የሌለ መሆኑ ሲታይ ፣ ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትሩ ያወጡት መግለጫ እውነትነት የሌለው መሆኑን እና በድርጅታች አብን የቀደመ ግምገማ መሰረት የክልል ልዩ ኃይሎችን ለማፍረስ የተላለፈው ውሳኔ በሁሉም ክልሎች ልዩ ኃይሎች ላይ በእኩል ደረጃ ተፈጻሚ የማይሆን እና የውሳኔው ዋነኛ የትኩረት አቅጣጫ የአማራ ልዩ ኃይልን ትጥቅ ማስፈታት እና መበተን መሆኑን አረጋግጧል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስተሩ በመግለጫቸው “የልዩ ሃይል አደረጃጀት አስፈላጊ አይደለም ማለት ፣ የልዩ ሃይል አባላት አያስፈልጉም ማለት አይደለም” ቢሉም ፣ በተግባር የአማራ ክልል ልዩ ኃይልን በሚመለከት ያሳለፉት ውሳኔ እና ውሳኔውን ለማስፈጸም እየሄዱበት ያለው መንገድ የአማራ ልዩ ኃይል ፖሊስ የሀገር አንድነትን እና ኅልውና ለማስከበር የከፈለውን መስዋዕትነት እና ግዙፍ አስተዋጽኦ የካደ ፣ በግዳጅ ላይ እና በካምፕ ውስጥ የሚገኙ የልዩ ኃይል አባላትን የዕለት ስንቅ ፣ ሎጂስቲክ እና ደሞዝ ነፍጎ ለርሃብ እና ለእንግልት እንዲዳረጉ ያደረገ ፍጹም ክብረ ነክ ተግባር ሲሆን ፣ እንኳንስ ለቀጣይ ሀገራዊ ተልዕኮ የማዘጋጀት ፍላጎት አይደለም ዝቅተኛውን የግበረ-ገብ እና ጨዋነት መመዘኛ የማያሟላ ፣ ልዩ ኃይሉን ተስፋ በማስቆረጥ እና በማበሳጨት ለመበተን እና ክልሉን የቀውስ እና የትርምስ ቀጠና የማድረግ ተልዕኮ ያለው ውሳኔ ሁኖ አግኝተንዋል፡፡

ይህም የክልሉ መንግስት የሚቆጣጠረውን እና የሚመራውን ኃይል በመበተን ፣ በእዝ የማይመራ እና መንግስት የማይቆጣጠረውን ኃይል ለመፍጠር እና ክልሉን ወደ ቀውስ እና ትርምስ ለመውሰድ የሚደረግ ጥረት ሆኖ የሚቆጠር ነው፡፡ ስለሆነም የገዥው ፓርቲ ሥራ አስፈጻሚ እና ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትሩ ያሳለፉትን ፍጹም ኃላፊነት የጎደለው ውሳኔ እና ውሳኔውን ለማስፈጸም እየሄዱበት ያለ ፍጹም አደገኛ ከሆነ መንገድ እንዲቆጠቡ እና ቆም ብለው እንዲያስቡ እያሳሰብን ፣ ፓርቲያችን የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ አብን የሚከተሉትን ጥሪዎች በድጋሜ ያስተላልፋል:-

1. ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትሩ ውሳኔያቸውን በይፋ እንዲሰርዙ ፣ ውሳኔው ስለመሰረዙ በአደባባይ እንዲገልጹ እና የአማራ ልዩ ኃይል አባላት እና የሀገር መከላከያ ሠራዊት አባላት ወደ ካምፓቻቸው እና ወደ ግዳጅ ቦታቸው እንዲመለሱ በይፋ ጥሪ እንዲያደርጉ፤

2. በፌዴራል መንግስቱ ውሳኔ እና ትዕዛዝ ከስራ ውጭ የሆኑት የአማራ ልዩ ኃይል ከፍተኛ አመራሮች ፣ የብርጌድ እና የክፍለ ጦር አዛዦች ወደ ኃላፊነታቸው እና ምድብ ቦታቸው እንዲመለሱ እንዲደረግ፤

3. የክልሉ መንግስት ለልዩ ኃይሉ  አስፈላጊ የሆኑ የስንቅ እና ሎጂስቲክ እንዲያቀርብ እና ደሞዝ እንዲከፍል፤

4. በካምፕ እና በግዳጅ ቦታችሁ ላይ የምትገኙ ውድ የአማራ ክልል የልዩ ኃይል ፖሊስ አመራሮች እና አባላት ሠራዊቱ እንዲበተን የሚደረጉ ጥረቶችን እና የፕሮፖጋንዳ ጥቃቶችን በመቋቋም በተለመደው ሥነ-ምግባር ፣ ዲስፕሊን እና ጨዋነት የሠራዊቱን የእዝ ሰንሰለት አክብራችሁ እና ጠብቃችሁ ከህዝባችሁ ጎን እንድትቆሙ፤

5. ለሀገር መከላከያ ሠራዊት አባላት እና አመራሮች በሙሉ በግፍ እየተጠቃ ካለው የአማራ ክልል ልዩ ኃይል እና ከአማራ ሕዝብ ጎን እንድትቆሙ እና ለግጭት ከሚጋብዙ ማናቸውም ሁኔታዎች እንድትቆጠቡ፤

6. የአማራ ክልል ከፍተኛ አመራሮች እንዲሁም የዞን እና የወረዳ አመራሮች በሙሉ በዚህ ፈታኝ ወቅት ከልዩ ኃይል ፖሊስ ሰራዊት እና ከሕዝባችሁ ጎን እንድትቆሙ፤ 

7. የአማራ ሕዝብ በየአካባቢው ላሉት የልዩ ኃይል አባላት አስፈላጊውን ስንቅ እና ድጋፍ እንዲያደርግላቸው ድርጅታችን አብን ጥሪውን ያቀርባል።

አብን ጉዳዩን በቅርበትና በንቃት እየተከታተለው መሆኑን እየገለፀ መንግስት ውሳኔውን እስኪቀለብስ እና ሁኔታዎች እስኪስተካከሉ ድረስ ተከታታይ ሰላማዊ ትግል የሚያደርግ መሆኑን ያሳውቃል። ድርጅታችን አብን መላው የአማራ ሕዝብ እና ሀገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን በሙሉ ከሀገር ወዳዱ የአማራ ልዩ ኃይል ጎን እንድትቆሙ የከበረ ጥሪውን ያቀርብላችኋል።

የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን)
አዲስ አበባ ፣ ሸዋ ፣ ኢትዮጵያ
ሚያዚያ 1 ቀን 2015 ዓ.ም

ቻናላችንን በመቀላቀል
ዓለም-አቀፋዊ  እና አገር-አቀፍ መረጃዎችን በቴሌግራም ገፃችን ይከታተሉ።
https://t.me/wektawi1mereja
2.2K views20:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-09 23:24:28
1.9K views20:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-09 23:05:58
መምህርት እና የፖለቲካ ተንታኝ መስከረም አበራ ታሰረች!

የአማራ ሕዝብን ማሳደድ እና ማሰር መገለጫው የሆነው ኦህዴድ መራሹ የብልጽግና መንግሥት መምህርት እና የፖለቲካ ተንታኝ መስከረም አበራን ማሰሩን ሚዲያችን አረጋግጧል።

ኦህዴድ መራሹ የብልጽግና መንግሥት የአማራ ምሁራንን፣ ጋዜጠኞችን፣ ፖለቲከኞችን እና አክቲቪስቶችን እያሳደደ እያሰረ እንደሚገኝ ይታወቃል። በዚህ ወር ብቻ ከ10 ሺ በላይ የአማራ ተወላጆች በአዲስ አበባ መታሰራቸውን ማረጋገጥ ችለናል።

ለትኩስ መረጃዎችን የቴሌግራም ገፃችንን ይመልከቱ!
https://t.me/wektawi1mereja
2.0K views20:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-09 13:37:04
#ተቀበል
193 views10:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-09 12:09:16
#በጎንደር_እየተካሄደ_ያለው_ሰላማዊ_ሰልፍ::
ቻናላችንን በመቀላቀል
ዓለም-አቀፋዊ  እና አገር-አቀፍ መረጃዎችን በቴሌግራም ገፃችን ይከታተሉ።
https://t.me/wektawi1mereja
768 views09:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-09 09:00:01
የሰብዓዊ መብት ተሟጋች የሆኑት ያሬድ ሀይለማርያም ስለጠቅላይ ሚኒስትሩና ስለፓርቲያቸው የተናገሩት!

“የዛሬዋን ኢትዮጵያን ሳስብ፤ ጠቅላዬ ጭልጥ ባለ ቁልቁለት ላይ ፍሬን የበጠሰ ሲኖትራክ መኪና የሚነዳ ወጣት፣ በቂ ልምድ የሌለው ሹፌር መስለው ነው የሚታዩኝ። ፍሬን በጥሶ ቁልቁል የሚምዘገዘገውም ሲኖትራክ የሚባለው መኪና ስሪቱ እራሱ ችግር ያለበት፣ ኢትዮጵያ ውስጥ ደግሞ በግጭትና በአደጋ የሚታወቅ፣ ወጣቶች የሚጋልቡት ግዙፍ መኪና ብልጽግና ፓርቲን ተመስሎ ነው የሚታየኝ። መኪናው እንኳን ቁልቁለት ላይ ፍሬን በጥሶ አይደለም በየሜዳውም ካገኘው ነገር ጋር በመጋጨት ለብዙ ሰውች ሞት ምክንያት እንደሆነ ይታወቃል። የሚገርመው በብዛት ይሄን መኪና የሚሾፍሩት በቂ እና የረዥም ጊዜ የሹፈራ ልምድ የሌላቸው ችኩል ወጣቶች ናቸው። አንዳንዶቹም እየቃሙ ነው አሉ የሚነዱት። ብልጽግና ፖርቲም ልክ በጎረምሶች እጅ የገባ ሲኖተትራክ መኪና ነው። ዛሬ ግን ቁልቁለትና ፍሬን መበጠስ አንድ ላይ የተገጣጠሙበት ይመስላል። እግዚአብሔር ኢትዮጵያን ይጠብቃት እንጂ አሁን ያለንበት ሁኔታ ያስፈራል።”
         
ተጨማሪ መረጃ ለማየት የቴሌግራም ገፃችንን ይመልከቱ!
https://t.me/wektawi1mereja
1.0K views06:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-09 08:53:21 #ማርከህ ታጠቅ ያለኝ->
የጨነቀው ለታ ፣
ስልጣን አደላድሎ በደሜ ጠብታ፣
ዛሬ ጠላት አርጎኝ ይላል ትጥቅ ፍታ፣#
992 views05:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-01 04:46:30 በሸገር ከተማ እየተካሄደ ያለው ቤቶችን የማፍረስ እና በግዳጅ ማስነሳት እርምጃ ጋር በተያያዘ የአንድ ሰው ህይወት ህልፈት ሪፓርት እንደደረሰው ኢሰመኮ አስታወቀ።

በቤት ማፍረስና በግዳጅ ማንሳት እርምጃ ለተጎዱ ሰዎች በሕጋዊ መንገድ የመኖሪያ ቤት የሚያገኙበትና ለደረሰባቸው የንብረት ውድመት ሊካሱ የሚችሉበት መንገድ በአፋጣኝ ሊመቻች እንደሚገባ አሳስቧል፡፡ 

የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን በኦሮሚያ ክልል በሸገር ከተማ እየተካሄደ ያለው ቤቶችን የማፍረስ እና በግዳጅ ማስነሳት እርምጃ የመኖሪያ ቤት አልባነትን አባብሷል ብሏል።

ኢሰመኮ በጉዳዩ ዙሪያ በለገጣፎ ለገዳዲ፣ በሰበታ  አካባቢ ፉሪ እና ለቡ ተክለሃይማኖት እንዲሁም በቡራዩ ገፈርሳ ኖኖ አካባቢዎች በመዘዋወር ቀደም ሲል የፈረሱ እና የማፍረስ ተግባሩ እየተከናወነ የነበረባቸውን አካባቢዎች ተመልክቻለሁ ነው ያልው፡፡

ኮሚሽኑ በለገጣፎ ለገዳዲ ክፍለ ከተማ በመገኘት
እየፈረሱ የነበሩ ቤቶችንም ለመመልከት ችሏል።
በምልከታው የቤት ማፍረሱ እና በግዳጅ ማስነሳቱ በግብረ ኃይል እየተከናወነ እንደነበረ እና በቦታው ከፖሊስ፣ ልዩ ኃይል እና ሚሊሻ አባላት በተጨማሪ ሌሎች ዱላ የያዙ ሲቪል ሰዎች እንደነበሩም መመልከቱን ነው ያሳወቀው።

በዘመቻ ቤት የማፍረሱ ሂደት ተገቢ ልየታ ያልተደረገበት ስለመሆኑ  ፣ አድሏዊ አሰራሮች መኖራቸውና ይህም ከብሔር ማንነት ጋር የተገናኘ መሆኑን፣ እና በቂ ቅድመ ማስጠንቀቂያ ሳይሰጥ ቤቶች እንደሚፈርሱ መረዳቱን ገልጿል።

እስር፣ የአካል እና የስነልቦና ጉዳት መድረሱንም በሪፓርቱ ኢሰመኮ አትቷል። ፊሊዶሮ በተባለ ቦታ ላይ በተደረገው የቤት ፈረሳ የሰው ሕይወት ማለፉን ኢሰመኮ መረጃ የደረሰው ሲሆን ይህን በተመለከተ ክትትል እያደረገ እንደሚገኝም አስታውቋል። 

ኢሰመኮ ከአቤቱታ አቅራቢዎች እና ተገቢነት ካላቸው የመንግሥት አካላት ባሰባሰበው መረጃ እና ማስረጃ መሠረት የማፍረስና በግዳጅ የማንሳት እርምጃው በርካታ ቤተሰቦችን ለከፍተኛ የኢኮኖሚ እና የማኅበራዊ ቀውስ ዳርጓል፤ ተማሪዎች ከትምህርታቸው ለማቋረጥ ተገደዋል፤ በርካታ ቤተሰቦች የእለት ተእለት ተግባራቸውን ማከናወን የማይችሉበት ሁኔታ ተፈጥሯል፤ በርካታ ቤተሰቦች ተፈናቅለው ወደ ሌሎች ቦታዎች ለመሄድ ተገደዋል፤ ከፊሎቹም መንገድ ላይ ወድቀዋል ወይም በተለያዩ የሀገር ውስጥ መጠለያ ጣቢያ በመሰብሰብ የመንግሥት እርዳታ ለመጠባበቅ ተገደዋል" ነው ያለው፡፡ 

የክልሉ መንግሥትና የከተማ አስተዳደሩ የማፍረስና በግዳጅ የማንሳት እርምጃውን ተግባራዊ ከማድረግ በፊት ቤቶቹ እንደተገነቡበት የይዞታ ዓይነትና ሁኔታ፣ ለብዙ ዓመታት የመብራት እና የውሃ እንዲሁም ሌሎች ማኅበራዊ አገልግሎቶችን እየሰጠ እና ነዋሪዎቹ የማኅበራዊ ሕይወት እንዲመሠርቱ ሲያደርግ የቆየ መሆኑን ከግምት ውስጥ በማስገባት አማራጭ መፍትሔዎችን በማመቻቸት የሰብአዊ መብቶች መከበራቸውንና መጠበቃቸውን ሊያረጋግጥ ይገባ እንደነበር አስገንዝቧል፡፡ 

በቤት ማፍረስና በግዳጅ ማንሳት እርምጃ ለተጎዱ ሰዎች በሕጋዊ መንገድ የመኖሪያ ቤት ሊያገኙ የሚችሉበት መንገድና ለደረሰባቸው የንብረት ውድመት ሊካሱ የሚችሉበት መንገድ በአፋጣኝ ሊመቻች እንደሚገባ አሳስቧል፡፡ 

የኢሰመኮ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ መብቶች ሥራ ክፍል ዳይሬክተር ዶ/ር ብራይትማን ገብረሚካኤል “ኢመደበኛ ይዞታዎቸን መከላከል የመንግሥት ኃላፊነት ቢሆንም የማፍረስና በግዳጅ የማንሳት እርምጃዎች ሰዎች ሕይወታቸው እንዲናጋ እና ቤተሰብ እንዲበተን የሚያደርግ መሆን የለበትም፤ ይልቁንም ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ መብቶች የተከበሩበት አሠራር መሆኑን ማረጋገጥ ይገባል” ብለዋል፡፡
1.4K views01:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-31 07:51:03 በኢትዮጵያ ውስጥ የሚገኙ የክልል ልዩ ሃይል አባላት ፈርሰው ወደ መደበኛ ፖሊስና ወደ ማረሚያ ቤት ፖሊስነት እንዲገቡ መመሪያ ተላልፏል::

የክልል ልዩ ሃይል አባላት የሚሸፍኑትን ስራዎች የመከላክያ ሰራዊትና የፌደራል ፖሊስ እንደሚወጡትም ተገልጿል::

ወደ መደበኛ ፖሊስና ማረሚያ ቤት ፖሊስ መጠቃለል የማይፈልጉ የክልል ልዩ ሃይል አባላት መቋቋሚያ ተሰቷቸው ወደሌላ የስራ መስክ እንደሚሰማሩ ተነግሯል::

ቻናላችንን በመቀላቀል
ዓለም-አቀፋዊ  እና አገር-አቀፍ መረጃዎችን በቴሌግራም ገፃችን ይከታተሉ።
https://t.me/wektawi1mereja
808 views04:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-30 17:59:10
#Nekemte

" ግድያው የተፈፀመው የቤታቸው ደጃፍ ላይ ነው "

ዛሬ የነቀምቴ ከተማ የብልጽግና ፓርቲ ጽህፈት ቤት ኃላፊ የሆኑት የ33 ዓመቱ ጎልማሳ አቶ ደሳለኝ ቦኮንጃ በታጣቂዎች በተፈጸመባቸው ጥቃት ተገድለዋል።

ግድያውን በተመለከተ የከተማ አስተዳዳሩ ምን አለ ?

- ለሥራ ከቤታቸው ሲወጡ በቤታቸው ደጃፍ ነው ባልታወቁ ሰዎች ነው የተገደሉት ብሏል።

- አቶ ደሳለኝ የሕዝብን ጥቅም ለማስከበር በቁርጠኝነት እና በተቆርቋሪነት. . . ያለምንም ፍርሐት ሕዝቡን ሲያገለግሉ ነበሩ ሲልም ገልጿል።

በብልጽግና ፓርቲ የኦሮሚያ ብልጽግና ፓርቲ ቅርጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ፍቃዱ ተሰማ ምን አሉ ?

- ግድያው የተፈፀመው በታጠቀ አካል ነው ብለዋል።

- ምንም እንኳን ግድያውን የፈፀሙ አካላትን ማንነት በስም ባይገልፁም ግድያውን የተፈፀሙት ከአገሪቱ የለውጥ መንገድ በተጻራሪ የቆሙ አካላት ናቸው ብለዋል።
804 views14:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ