Get Mystery Box with random crypto!

🗣 ወቅታዊ_መረጃ 🇪🇹

የቴሌግራም ቻናል አርማ wektawi1mereja — 🗣 ወቅታዊ_መረጃ 🇪🇹
የቴሌግራም ቻናል አርማ wektawi1mereja — 🗣 ወቅታዊ_መረጃ 🇪🇹
የሰርጥ አድራሻ: @wektawi1mereja
ምድቦች: ፖለቲካ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 12.46K
የሰርጥ መግለጫ

This is national and international News and advertising channel
🇪🇹🇪🇹🇪🇹"ስለኢትዮጲያ ሳትሰማ ያሳለፍከው ቀን እንደባከነ ይቆጠራል" 🇪🇹🇪🇹🇪🇹
⏭▶️➡️ ሀገራዊና አለም አቀፋዊ ዜናዎችን በፍጥነት ይደርሶታል።🔚

Ratings & Reviews

3.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

2

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 16

2022-12-07 08:35:30
አንጋፋው የወንጌል አገልጋይ ቄስ በሊና ሳርካ ከዚህ አለም ድካም አረፉ

ከ60 አመታት በላይ በወንጌል አማኞች ዘንድ በማገልገል የወንጌል አርበኛ የሚል ስያሜ ያላቸው ቄስ በሊና ሰርካ ባጋጠማቸው ህመም በኮሪያ ሆስፒታል በህክምና ሲረዱ ቆይተው ትናንት አመሻሽ ላይ ከዚህ ዓለም በሞት መለየታቸው ተሰምቷል።

#የወቅታዊ_መረጃ  ለቤተሰቦቻቸው፣ለወዳጅ ዘመድ መፅናናት እንዲሆን ይመኛል።

#ሼር በማድረግ ትክክለኛዉን  መረጃ ለሌሎች ተደራሽ ያድርጉ። ለበለጠ መረጃ ቴሌግራም 
@wektawi_Merej
4.2K views05:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-06 12:22:25 https://www.hulusport.com/?referal=212465
4.4K views09:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-06 12:21:24 https://www.hulusport.com/?referal=212465
4.2K views09:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-06 05:28:56
2 ህፃናት በአሰቃቂ ሁኔታ የገደለችው የቤት ሰራተኛ በሞት እንድትቀጣ  ተወሰነ

2 ህጻናትን በአሰቃቂ ሁኔታ ህይወታቸው እንዲያልፍ አድርጋለች ተብላ የተከሰሰችው የጥፋተኝነት ፍርድ የተሰጠባት ህይወት መኮንን የተባለችው የቤት ሰራተኛ በሞት ቅጣት እንድትቀጣ ተወስኗል።

የቅጣት ውሳኔውን የሰጠው የፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ 1ኛ የከባድ ግድያና የውንብድና ጉዳዮች ወንጀል ችሎት ነው።

ተከሳሽ ህይወት መኮንን ሀይሉ በነሃሴ 26 ቀን 2014 ዓ/ም ከጠኋቱ 3:30 ላይ በለሚኩራ ክ/ከ አራብሳ ኮንዶሚኒዬም  በቤት ሰራተኛነት ተቀጥራ በምትሰራበት መኖሪያ ቤት ውስጥ ምክንያቱ ባልታወቀ ሁኔታ የህጻን ግዮናዊት መላኩ አፏን በማፈን በቢላ በማረድ ህይወቷ እንዲያልፍ ማድረጓን እና ህጻን ክርስቲና መላኩን አፏን በማፈን በማነቅ በአጠቃላይ ህፃናቶቹን በአሰቃቂ ሁኔታ ህይወታቸው እንዲያልፍ  አድርጋለች ሲል በግድያ ወንጀል እና በወቅቱ የሟች ቤተሰቦችን የሰነድ ማስረጃዎች ቀዳዳ በማጥፋት በአጠቃላይ በተደራራቢ ክስ በጥቅምት 15 ቀን 2015 ዓ/ም የወንጀል  ክስ ተመስርቶባት እንደነበር ይታወሳል።

ሼር በማድረግ ትክክለኛዉን  መረጃ ለሌሎች ተደራሽ ያድርጉ። ለበለጠ መረጃ ቴሌግራም 
@wektawi_Merej
4.6K views02:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-05 07:00:15 ከሕወሃት ታጣቂዎች 65 በመቶዎቹ ከውጊያ ግንባሮች ወጥተዋል ሲሉ የሕወሃት ኃይሎች ዋና አዛዥ ጀኔራል ታደሠ ወረደ ለትግራይ ቴሌቪዥን በሰጡት መግለጫ ተናግረዋል። ጀኔራል ታደሠ "ሰላም አዋኪዎች" አሁንም በክልላችን ስላሉ፣ የተወሰኑ ኃይሎቻችን በግንባር እንዲቆዩ አድርገናል ብለዋል። ፌደራል መንግሥት የኤርትራ ወታደሮችንና የአማራ ክልል ታጣቂዎችን ከክልሉ እንዲያስወጣ ጀኔራል ታደሠ  ጠይቀዋል። የስምምነቱን አፈጻጸም ለመከታተል የተቋቋመው አካል ገና ወደ ክልሉ እንዳልገባ የጠቀሱት ጀኔራል ታደሠ፣ የሕወሃት ኃይሎች ግን ስምምነቱን ተግባራዊ እያደረጉ ነው ብለዋል። የሕወሃት ኃይሎችን ትጥቅ የማስፈታት ሂደቱ "የትግራይ ሕዝብን ደኅንነት ግምት ውስጥ ያስገባ" እንደሚሆንም ጀኔራሉ ገልጸዋል።//

በምዕራብ አባያ ከተማ አቅራቢያ 83 የትግራይ ተወላጅ የሆኑ ወታደር እስረኞች አምና ኅዳር 13 ላይ እንደተገደሉ ከግድያው ከተረፉ ስድስት እስረኞች ሰምቻለሁ በማለት ዋሽንግተን ፖስት ዘግቧል። አንዳንዶቹ እስረኞች 18 ያህል በሚሆኑ "ጠባቂዎቻቸውና ሌሎቹ ደም "በአካባቢው መንደርተኞች" ተገድለው አስክሬናቸው በጅምላ መቀበሩን አይተናል ሲሉ እማኞቹ መናገራቸውን ዜና ምንጩ ጠቅሷል። እማኞቹ የግድያው ምክንያት "ቂም በቀል ሳይሆን አይቀርም" ብለው እንደሚገምቱም ዘገባው አመልክቷል። የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ክስተቱን እንደሚያውቅ ገልጾ፣ ምርመራ እያደረገ እንደነበር ተናግሯል ተብሏል።//

ምንጭ ዋዜማ
ሼር በማድረግ ትክክለኛዉን  መረጃ ለሌሎች ተደራሽ ያድርጉ። ለበለጠ መረጃ ቴሌግራም 
@wektawi_Merej
4.9K views04:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-04 21:17:23 " እዛ እየሆነ ያለው ድርጊት ይሄ ነው ተብሎ የሚነገር አይደለም። " - ተፈናቃይ

በምስራቅ ወለጋ ኪረሙ ወረዳ ባለው የፀጥታ ሁኔታ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች ከቄያቸው ተፈናቅለዋል ፤ ህይወታቸውን ለማትረፍ ሸሽተዋል።

እንደ ዶቼ ቨለ ሬድዮ ጣቢያ ዘገባ ተፈናቃይ ወገኖች / ህይወታቸውን ለማትረፍ የሸሹ ወገኖች ሰላምን ፍለጋ 40 ኪሎ ሜትር ድረስ በእግር ታጉዘው ጊዳአያና ወረዳ መግባት ችለዋል።

በወረዳው በ19 ቀበሌዎች ውስጥ የተፈናቀሉ ዜጎች ወደ ነቀምቴ እና ጊዳ አያና ወደሚገኙ አካባቢዎች ለመሸሽ ተገደዋል።

ባለፈው ሀሙስ ኪረሙ ላይ ከፍተኛ ውድመት የደረሰ መሆኑ ተመላክቷል።

ይህንን ጉዳይ በተመለከተ አንድ የአካባቢው ነዋሪ ፥ " እዛ እየሆነ ያለው ድርጊት ይሄ ነው ተብሎ የሚነገር አይደለም። " ያሉ ሲሆን ብዙ ህዝብ መፈናቀሉን ፣ ተፈናቃዮች ሰላምን ፍለጋ በሸሹበት ወቅት እየራባቸው ፤ እየደከማቸው በእግር ለመጓዝ መገደዳቸውን ገልፀዋል።

ከተፈናቃዮች መካከል ፤ አንድ አዛውንትም በመንገድ ላይ ደክሟቸው ህይወታቸው እንዳለፈ ያጠቆሙት እኚሁ ነዋሪ " ባለፉት ሳምንታት በነበረው ግጭት ኪረሙ ላይ በአንድ ጉድጓድ ሃያ (20) እና አርባ (40) ሰው ስንቀብር ነበር " ሲሉ የሁኔታውን አስከፊነት ተናግረዋል።

የቲክቫህ ቤተሰብ አባላት እንዳሳወቁት ፤ ከሰሞኑን በነበረው ሁኔታ የሰዎች ህይወት ያለፈ ሲሆን እናቶች ልጆቻቸውን ተሸክመው ጫካ ለጫካ እንዲንከራረቱ፣ እንዲሰቃዩ ሆነዋል።

በኦሮሚያ ክልል መንግስት በተለያዩ ዞኖች አካባቢዎች በተለይም ደግሞ በወለጋ ላለፉት ዓመታት የነበረው የፀጥታ ችግር፣ ጥቃት፣ መፈናቀል፣ ሞት ፣ መፍትሄ ሳያገኝ ዛሬም ድረስ የቀጠለ ሲሆን ችግሩ እልባት ከማግኘት ይልቅ ይበልጥ እየተባባሰ እና እየተወሳሰበ መጥቷል።

የአካባቢው ህዝብ ዘርቶ ማጨድ ፣ ሰርቶ መብላት ፣ እንደልቡ ወጥቶ መግባት፣ ልጆቹን በሰላም ያለስጋት ማሳደግ አልቻለም።

- በተደጋጋሚ ጊዜ ፤ የፀጥታ ችግር ያለባቸው ቦታዎች በግልፅ ተለይተው እየታወቁ ችግርም ሲኖር የድረሱልን ጥሪ እየቀረበ በፍጥነት መፍትሄ መስጠት ለምን አልተቻለም ?

ሁሌም ክቡር የሆነው የሰዎች ህይወት ከረገፈ በኃላ የአንድ ሰሞን ትኩረት ተሰጥቶ ፤ ሰሞነኛ ጩኸት ተጩሆ ከዛ ችግሩ ለምን ይቀጥላል ?

- ስንት ሰው ሲያልቅ ነው ዘላቂ መፍትሄ የሚበጀው ? አሁን እየሆነ ላለው እና ለነበረው ነገር ሁሉ ማነው ተጠያቂ ?

- ኃላፊነታቸውን ያልተወጡ ፤ እንመራዋለን የሚሉትን ህዝብ ሰላሙንና ደህንነቱን ማስጠበቅ ያልቻሉ የመንግስት አካላት መቼ ነው በህግ ፊት ተጠያቂ የሚሆኑት ?

- የተሰቃዩ ፣ የተበደሉ ፣ የሚወዱትን የተነጠቁ እንዴት ነው ፍትህ የሚያገኙ ? የሚሉ ጥያቄዎች መልስ ሊሰጣቸው ይገባል።

ሼር በማድረግ ትክክለኛዉን  መረጃ ለሌሎች ተደራሽ ያድርጉ። ለበለጠ መረጃ ቴሌግራም 
@wektawi_Merej
4.8K views18:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-03 21:34:27 የ12ኛ ክፍል ውጤት
የ12ኛ ክፍል ፈተና ውጤት እስከ ታህሳስ 25 ድረስ ይፋ  ይደረጋል የሚል መረጃ ደርሶኛል።
የ 2014 የ 12ኛ ክፍል ፈተና ውጤት ከ  2ተኛው ዙር ተፈታኞች ውጤት ጋር በአንድ ላይ ይለቀቃል።
የ 2ኛ ዙር ፈተና ከ ታህሳስ 11-14 እንደሚሰጥ እቅድ እንደተያዘ የአዩ ዘሀበሻ ምንጮች ገልጸዋል። የ 2ኛ ዙር ፈተና እርማት አንድ ሳምንት ባልሞለ ውስጥ ታርሞ ተማሪዎች ውጤታቸውን ያውቃሉ።
በአጠቃላይ የ 2014 የ 12ኛ ክፍል ተማሪዎች  ከጥር ወር ጀምሮ ወደ ዩኒቨርስቲ እንዲገቡ ይደረጋል።

ሼር በማድረግ ትክክለኛዉን  መረጃ ለሌሎች ተደራሽ ያድርጉ። ለበለጠ መረጃ ቴሌግራም 
@wektawi_Merej
5.4K views18:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ