Get Mystery Box with random crypto!

Think Abyssinia

የቴሌግራም ቻናል አርማ thinkabyssinia — Think Abyssinia T
የቴሌግራም ቻናል አርማ thinkabyssinia — Think Abyssinia
የሰርጥ አድራሻ: @thinkabyssinia
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 157
የሰርጥ መግለጫ

➠ ፈጣን እና ተዐማኒ መረጃ፣
➠ የስፓርት እና መዝናኛ ዘገባዎች፣
➠ የምሁራን እይታዎችና መጽሐፈቶች፣
➠ የአለም ሙሉ መረጃና የታሪክ መዛግብቶች ።
ለማንኛውም መረጃ ➥ @Contact_Thinkabyssinia

🎬 "ተመራጭ የዜና ምንጭ"

Ratings & Reviews

3.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 91

2022-05-13 14:48:44 #Update

ስለ ፕሬዝዳንት ሼኽ ኻሊፋ ቢን ዛይድ አል ናህያን አንዳንድ መረጃዎች:-

የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች ፕሬዝዳንት ሼኽ ኻሊፋ ቢን ዛይድ አል ናህያን በ73 ዓመታቸው ማረፋቸው ተሰምቷል ዛሬ ተሰምቷል።

የሃገሪቱ ፕሬዝዳንት ጉዳዮች ሚኒስትር እንዳስታወቀው ለቀጣዮቹ 40 ቀናት በተባበሩት አረብ ኤምሬቶች ብሔራዊ የሐዘን ቀናት ሆኖ ታውጇል።

ፕሬዝዳንት ሼኽ ኻሊፋ ቢን ዛይድ አል ናህያን የተባበሩት አረብ ኤምሬቶችን ከፈረንጆቹ 2004 ጀምሮ ለ18 ዓመታት በፕሬዝዳንትነት መርተዋታል።

ለረጅም አመታት በህመም የቆዩት ሼኽ ካሊፋ ከተለያዩ የአስተዳደር ጉዳዮች ራሳቸውን አግልለው የነበረ ሲሆን ወንድማቸው የአቡ ዳቢው ልኡል መሃመድ ቢን ዛይድ በህጋዊነት ስልጣኑን ባይዙም የመሪነት ሚና ሲጫወቱ ቆይቷል።

ሼኽ ከሊፋ የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች መስራች የሆኑትን አባታቸውን ሼኽ ዛይድ በመተካት ነበር በ 2004 እአአ ስልጣን የያዙት።

ፕሬዝዳቱን ስለሚተካው ሰው እስካሁን ምንም የተሰጠ ይፋዊ መግለጫ የለም።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድም በተባበሩት አረብ ኢሚሬቶች ፕሬዚዳንት ሼክ ካሊፋ ቢን ዛይድ አል ናህያን ህልፈት የተሰማቸውን ሐዘን ገልጸዋል።

• @ThinkAbyssinia •
4.8K viewsedited  11:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-13 13:58:32
ሕንዳዊያኑ ወላጆች የልጅ ልጅ አልወለዱልንም ሲሉ ብቸኛ ልጃቸውን እና ባለቤቱን ፍርድ ቤት አቆሙ

ሳንጄቭ እና ሳድሃና ፕራሳድ እንደሚሉት ልጃቸውን ለማሳደግ የነበራቸው አንጡራ ሃብት አፍስሰውበታል። የበረራ ትምህርቱን እንዲከታተል ከመርዳት ባለፈም ድል ባለ ድግስ እንደዳሩት አስታውቀዋል።

በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ የልጅ ልጅ ካላገኙ 650 ሺህ ዶላር ካሳ ከልጃቸው እንደሚፈልጉም አስታውቀዋል። ያልተለመደ ነው የተባለው ክስ "ስነ-ልቦናዊ ጉዳት" በማድረስ በሚል የቀረበ ነው።

አባት ፕራሳድ ያላቸውን ጥሪት በሙሉ ልጃቸው የአውሮፕላን አብራሪ እንዲሆን 65 ሺህ ዶላር ወጪ አድርገው አሜሪካ እንደላኩት ተናግረዋል ሲል አል አይን ቢቢሲን ጠቅሶ ዘግቧል ።


• @ThinkAbyssinia •
1.6K views10:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-13 13:38:01
#united_Arab_emirate

የተባበሩት አረብ ኤሜሬቶች ፕሬዝዳንት ሼክ ካሊፋ ቢን ዛይድ አል ነህያን በ73 አመታቸው ከዚህ አለም በሞት ተለዩ ሲሊ የሀገሪቱ የመንግስት መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል።


RT News

• @ThinkAbyssinia •
2.4K views10:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-13 13:16:39
የ11 ልጆች አባትና የ69 ዓመቱ አዛውንት የዘንድሮ የጅማ ዩኒቨርሲቲ አዲስ ገቢ ተማሪ ሆነዋል

የ11 ልጆች አባት እና የ69 ዓመቱ አዛውንት ታደሰ ጊችሌ የጅማ ዩኒቨርሲቲ እየተቀበላቸው ካሉ አዲስ ገቢ ተማሪዎች መካከል አንዱ ሆነዋል።

የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና ወስደው 502 የመግቢያ ነጥብ ያመጡት እና በጅማ ዩኒቨርሲቲ የተመደቡት ተማሪ ታደሰ ጊችሌ ፥ ከምዕራብ ወለጋ ገንጅ ወረዳ መነሻቸውን አድርገው ለትምህርት ጅማ ዩኒቨርሲቲ በዕድሜ ከልጆቻቸው በትምህርት ደግሞ ከእኩዮቻቸው ጋር ተቀላቅለዋል።

በ1945 ዓ.ም የተወለዱት አቶ ታደሰ የ11 ልጆች አባት ሲሆኑ ፥ ባለቤታቸው ወይዘሮ ቢዲጡ ቶላ እና ልጆቻቸው ‘’ትምህርቴን ጨርሼ ትልቅ ደረጃ እንድደርስ ትናንትም ዛሬም አስተዋፅኦ አድርገዋል’’ ብለዋል።

እንደ እኩዮቻቸው ፊደል ቆጥረው ሳይንሱን አርቅቀው የሚፈልጉበት የልጅነት ራዕያቸዉ ላይ ለመድረስ በቤተሰብ ሃላፊነትና በዝቅተኛ የኑሮ ሁኔታ ቢፈተኑም ፥ ካሰቡበት ለመድረስ ባላቸው ጠንካራ የመማር ፍላጎት ዩኒቨርሲቲ መግባታቸውን ይናገራሉ፡፡

በጅማ ዩኒቨርሲቲ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት አዲስ ገቢ የሆኑት ተማሪ ታደሰ ፥ ‘’አንዳንዶች በዚህ እድሜህ ትምህርቱን አቋርጠህ ለምን ወደ እርሻህ አትመለስም ይሉኛል ፤ እኔ ግን የልጅነት ህልሜን ማሳካት ስላለብኝ ከትምህርቴ ጎን ለጎን የእርሻና የቡና ችግኝ እያስፋፋሁ ቆይቻለሁ’’ ብለዋል።

ተማሪ ታደሰ ጊችሌ ወደ ፊት በዩኒቨርሲቲ ቆይታ በጤና ዶክትሬት ማጥናት እና በሕክምናው ዘርፍ የሚታዩ ክፍተቶችን በማስተካከል ኢትዮጵያን እና ወገኔን ማገልገል እፈልጋለሁ ማለታቸውን ከጅማ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

FBC

• @ThinkAbyssinia •
3.1K viewsedited  10:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-13 13:14:09
የዘኢኮኖሚስት ዘጋቢው ቶም ጋርድነር የስራ ፈቃድ ተሰረዘ

የዘ ኢኮኖሚስት መጽሔት ዘጋቢው ቶም ጋርድነር በኢትዮጵያ የነበረው የሥራ ፈቃድ መሰረዙን የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለስልጣን አስታውቋል።

ባለስልጣኑ ለጋዜጠኛው በጻፈው ደብዳቤ ላይ እንዳስታወቀው፤ ጋዜጠኛው ከሙያ ስነ ምግባር ውጭ በተደጋጋሚ ሲሰራ በመገኘቱ ተደጋጋሚ የቃል እና የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ ተሰጥቶታል። በተጨማሪም ከጋዜጠኛው ጋር ውይይት በማድረግ ከስህተቱ እንዲታቀብ ለማድረግ ጥረት መደረጉን ባላስልጣኑ ገልጿል።

ይሁን እንጂ ቶም ጋርድነር የሙያውን ስነ ምግባር በማክበር ለመስራት ባለመቻሉ ከዛሬ ግንቦት 5 ቀን 2014 ዓም ጀምሮ በኢትዮጵያ የነበረው የጋዜጠኝነት የስራ ፈቃድ መሰረዙንና ከዚህ በኋላ በጋዜጠኝነት ስራ በኢትዮጵያ ውስጥ መስራት እንደማይችል ባለስልጣኑ አስታውቋል።

ዘ ኪኮኖሚስት በዚህ ጋዜጠኛ ምትክ ሌላ የሙያውን ሥነ ምግባር አክብሮና ገለልተኛ ሆኖ መስራት የሚችል ሰው መድቦ ማሰራት እንደሚችልም ባለስልጣኑ በዚሁ ደብዳቤ ላይ ገልጿል።


የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለስልጣን

• @ThinkAbyssinia •
2.8K views10:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-13 12:53:23
ህጻን አግቶ ህይወቱ እንዲያልፍ ያደረገው ግለሰብ በ25 ዓመት ፅኑ እስራት ተቀጣ።

በማዕከላዊ ጎንደር ዞን ጭልጋ ወረዳ የአይከል ከተማ ነዋሪ የሆነውን 15 ዓመት ታዳጊ ህጻን ጥር 2 ቀን 2013 ዓ.ም. ከመኖሪያ ቤቱ አፍኖ በመውሰድ ህይወቱ እንዲያልፍ በማድረግ ወንጀል የተከሰሰው ግለሰብ በእስራት ተቀጥቷል።

ግለሰቡ ለህጻኑ ወላጆች ስልክ በመደወል 100 ሺህ ብር ከፍለው ልጃቸውን እንዲወስዱ ብሩን ካልከፈሉ ግን ህጻኑን እንደሚገድለው ሲዝት እንደነበር የፍርድ ቤቱ የህዝብ ግንኙነት ባለሙያ ወይዘሮ ማስተዋል ወርቁ ተናግረዋል።

በዛተውም መሰረት ህጻኑን በወረዳው ፋይና ገብ ተብሎ በሚጠራው ገደል ውስጥ በመክተት ህይወቱ እንዲያልፍ ማድረጉን በሰውና በህክምና ማስረጃ መረጋገጡን ባለሙያዋ ተናግረዋል፡፡

ከፍተኛ ፍርድ ቤቱ ግራ ቀኙን አስቀርቦ ክስ ከሰማ በኋላ ተከሳሹ የእምነት ክህደት ቃሉን ሲጠይቅ ወንጀሉን አልፈጸምኩም በማለት ክዶ ተከራክሯል፡፡

ተከሳሽ በአቃቢ ህግ የቀረበበትን ማስረጃ ማስተባበል ባለመቻሉ በወንጀለኛ መቅጫ ሥነ- ሥርዓት የህግ ቁጥር 149/1/ መሰረት ጥፋተኛ ሆኖ መገኘቱን አስታውቀዋል፡፡

ግለሰቡ የቤተሰብ አስተዳዳሪና ከዚህ በፊት የወንጀል ሪከርድ የሌለበት መሆኑን በቅጣት ማቅለያነት የተመለከተው ፍርድ ቤቱ በ25 ዓመት ፅኑ እስራት እንዲቀጣ ፈርዶበታል። (ENA)


• @ThinkAbyssinia •
3.3K viewsedited  09:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-13 12:19:35
ኬንያዊቷ ነርስ የ250 ሺህ ዶላር ሽልማት አሸነፈች

ነርስ አና ካባሌ ዱባ ኬንያዊት ስትሆን በመርሳቢት ሪፈራል ሆስፒታል ነርስ ናት። በምትኖርባቸው አካባዎች የሴት ልጅ ግርዛትን ጨምሮ ሌሎች ጎጂ ባህላዊ ድርጊቶች እንዲቆሙ ማህበረሰቡን ማስተማር ላይ ትኩረቱን ያደረገ ካባሊ ዱባ ፋውንዴሽን የተሰኘ ተቋም በመመስረት የሰዎች አመለካከታቸውን መቀየር የሚያስችሉ ስራዎችን ስትሰራም ነበር፡፡

ዓለም አቀፉ የነርሶች ቀን በትናንትናው እለት በአረብ ኢምሬትስ በተከበረበት ወቅት ይህቺ ነርስ የሴት ልጅ ግርዛትን ጨምሮ ሴቶችን እና ህጻናትን የሚጎዱ ድርጊቶችን ለመከላከል ላደረገችው ጥረት እውቅና ተሰጥቷታል፡፡ ነርስ አና ካባሌ ለጥረቷ የ250 ሺህ ዶላር ሽልማት እንደተበረከተላትም ቢቢሲ ዘግቧል፡


bbc, al ain Amharic

• @ThinkAbyssinia •
3.9K views09:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-13 11:45:55
የዓለም የምግብ ፕሮግራም ከ3ሺህ ቶን በላይ የሰብዓዊ ድጋፍ ማከፋፈሉን አሰታወቀ

ባሳለፍነው ሳምንት የሰብዓዊ እርዳታ አቅርቦት የጫኑ 165 ተሽከርካሪዎች ትግራይ ክልል ደርሰው 3ሺህ ቶን ምግብና አልሚ ምግቦችን ማከፋፈሉን የዓለም የምግብ ፕሮግራም አሰታወቀ።

የሰብዓዊ እርዳታ አቅርቦቱም በክልሉ ለሚገኙ ለ120 ሺህ ዜጎች ተደራሽ ተደርጎልም ብሏል።

የዓለም የምግብ ፕሮግራም በማህበራዊ የትስስር ገፁ እንዳስታወቀው አሁን ላይም እርዳታ የጫኑ 94 ተሽከርካሪዎች ወደ ትግራይ እያቀኑ ነው። የምግብ እርዳታ ስርጭቱ በአፋር እና በአማራ ክልልም በሂደት ላይ ነውም ብሏል።


WFP

• @ThinkAbyssinia •
4.2K views08:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-13 11:43:18
በ60 ሚሊዮን ዩሮ የተገነባው ሱፍሌት ማልት ኢትዮጵያ የተሰኘ ብቅል አምራች ፋብሪካ ተመረቀ

በቦሌ ለሚ ኢንዱስትሪ ፓርክ ውስጥ በ60 ሚሊየን ዩሮ ወጪ የተገነባው ሱፍሌት ማልት ኢትዮጵያ የተሰኘው የብቅል ማምረቻ ፋብሪካ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ (ዶ/ር) በተገኙበት የምረቃ መርሐግብር እየተካሄደ ይገኛል።

ፋብሪካው በዓመት 60 ሺህ ቶን ብቅል የማምረት አቅም እንዳለው ከኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ኮርፖሬሽንያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

በግብርና ላይ የሚሰራ ኢንቪቮ ግሩፕ በተባለ የፈረንሳይ ኩባንያ ስር የሚገኘው ሱፍሌት ማልት በ38 ሀገራት የተለያዩ የግብርና ምርቶች ማቀነባበሪያ ፋብሪካዎች አሉት።



• @ThinkAbyssinia •
4.1K views08:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-13 10:05:54 #ቲንክአቢሲኒያ_የቡናቁርስ_መረጃዎች

1፤አቀፍ ተቋሟት በዲጂታል ዘርፉ መዋዕለ ንዋያቸውን እንዲያፈሱ ጥሪ ቀረበ።

ኢትዮጵያ ምቹ የዲጂታል ስነ ምህዳር እየፈጠረች በመሆኑ አለም አቀፍ ተቋሟት በዘርፉ መዋዕለ ንዋያቸውን እንዲያፈሱ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዶ/ር በለጠ ሞላ ጥሪ አቀረቡ። በኢትዮጵያ አስተናጋጅነት ለሁለት ቀናት በአዲስ አበባ ሲካሄድ የነበረው 19ኛው የኢኖቬሽን አፍሪካ ዲጂታል ጉባኤ ተጠናቋል። የዲጂታል ይዘትና አገልግሎት ላይ ትኩረቱን አድርጎ በተካሄደው በዚህ ጉባኤ ላይ ከ 26 በላይ ድርጅቶችና ከ390 በላይ ከተለያዩ ሀገራት የተውጣጡ ተሳታፊዎች ታድመዋል። የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዶ/ር በለጠ ሞላ ኢትዮጵያ ምቹ የዲጂታል ስነ ምህዳር እየፈጠረች በመሆኑ አለም አቀፍ ተቋሟት በዘርፉ መዋዕለ ንዋያቸውን እንዲያፈሱ ጥሪ አቅርበዋል። በቴሌኮም ዘርፍ የተጀመረው ማሻሻያ ለዲጂታል ቴክኖሎጂ ትግበራ ትልቅ አቅም ይፈጥራል ያሉ ሲሆን መንግስትም አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ ገልጸዋል።

2፤የጉሙዝ ሕዝብ ዲሞክራሲያዊ ንቅናቄ መንግሥት ፍትህ ላላገኙት እስረኞች አስቸኳይ መፍትሄ እንዲሰጥ ጠየቀ።

የጉሙዝ ሕዝብ ዲሞክራሲያዊ ንቅናቄ በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ካማሺ እና አሶሳ ዞኖች ከ2011 ዓ.ም ጀምሮ የታሰሩ 47 ሰዎች እስካሁን ለፍርድ አልቀረቡም ሲል ቅሬታውን ማሰማቱን ዶይቸቨለ ዘግቧል። ንቅናቄው መንግሥት ፍትህ ላላገኙት እስረኞች አስቸኳይ መፍትሄ እንዲሰጥ ጠይቋል። የክልሉ ጠቅላይ ዓቃቤ ሕግ ግን ፍርድ ቤት ያልቀረበ
ተጠርጣሪ እስረኛ የለም ሲል አስተባብሏል። የዞኑ ፖሊስ በበኩሉ፣ ፍርድ ቤት ሳይቀርቡ ለአራት ዓመታት የታሰሩ ሰዎች መኖራቸውን አምኖ፣ ጉዳዩን ለሚመለከተው አካል ማሳወቁን
ተናግሯል።

3፤በታላቁ ህዳሴ ግድብ ላይ ዓሳ የማርባት ሥራ ተፈቀደ።

በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ላይ የዓሳ ማርባት ሥራ መፈቀዱን የግብርና ሚኒስቴር አስታወቀ። ግብርና ሚንስቴር በሕዳሴ ግድብ ላይ አሳ ማርባት እንዲጀመር መፍቀዱን የዘገበው ሪፖርተር ነው። በኢትዮጵያ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት ጥናት መሠረት፣ ኢትዮጵያ በዓመት ከ94 ሺህ 500 ቶን በላይ አሳ የማምረት አቅም ያላት ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት እየተመረተ የሚገኘው ግን ከ60 ሺህ ቶን በታች ነው። ሰው ሰራሽ ሐይቆች ከዓመታዊ ምርቱ የ27 በመቶ ድርሻ አላቸው። የአንድ ኢትዮጵያዊ ዓመታዊ የአሳ ፍጆታ ከግማሽ ኪሎ ግራም በታች ሲሆን፣ በሌሎች የአፍሪካ አገራት ግን ፍጆታው ወደ 12 ኪሎ ግራም አድጓል።

4፤ ሩስያ ፊንላድ ኔቶን ከተቀላቀለች የአፀፋ እርምጃ እንደምትወስድ አሳወቀች።

ፊንላንድ ያለምንም መዘግየት ኔቶን ለመቀላቀል ለማመልከት እንደምትፈልግ ገልፃለች። ስውዲንም ፊንላንድ ትከተላለች እየተባለ ነው። ይህ ደግሞ ሞስኮን ክፉኛ ያስቆጣ ሲሆን ፊንላንድ ኔቶን ለመቀለቀል ያሳየችውን ፅኑ ፍላጎት እና ዝግጁነት " ቀጥተኛ ስጋት " ስትል በመጥራት " ወታደራዊ-ቴክኒካል " እርምጃዎችን ጨምሮ አፀፋዊ ምላሽ እንደምትሰጥ አስፈራርታለች። ይህም በኢኮኖሚው ላይ የሚያሳድረው ጫና ለታዳጊ ሀገራትና ለመላው ዓለም የሚተርፍ ነው ተብሏል። ከዩክሬን ጦርነት በኃላ ሩስያ ፥ ፊንላንድ እና ስውዲን ኔቶን ለመቀላቀን ብታስቡ እጅግ " ጎጂ " የሆኑ ውጤቶች [ኢኮኖሚያዊና ወታደራዊ] ይኖራል ስትል አስጠንቅቃቸው ነበር።

5፤ዛሬ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አንድ የአሜሪካን ዶላር በ51 ብር ከ4676 ሳንቲም እየተገዛ ይገኛል።


እንዲሁም መሸጫ ዋጋው 52 ብር ከ4970 ሳንቲም መሆኑን ከድረገጹ ተመልክተናል። የአንድ የእንግሊዝ ፓውንድ መግዣ ዋጋው 59 ብር ከ9796 ሳንቲም እንዲሁም መሸጫው 61 ብር ከ1792 ሳንቲም ሆኗል። በተመሳሳይ አንድ ዩሮ በ53 ብር ከ6859 ሳንቲም እየገዛ በ54 ብር ከ7596 ሳንቲም እየተሸጠ ሲሆን፣ አንድ የቻይና ዩዋን ደግሞ በ6 ብር ከ8611 ሳንቲም ተገዝቶ በ6 ብር ከ9983 ሳንቲም እየተሸጠ እንደሚገኝ ቲንክአቢሲኒያ ተመልክቷል።

6፤ተጠባቂው ጨዋታ በቶተንሀም አሸናፊነት ተጠናቋል።

የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ተስተካካይ ጨዋታ በቶተንሀም ሆትስፐር ስታዲየም ቀጥሎ ሲካሄድ ቶተንሀም ከ አርሰናል ጋር ያደረገውን ጨዋታ 3 - 0 በሆነ ውጤት አሸንፏል ። የቶተንሀምን የማሸነፊያ ግቦች ሰን ሁንግ ሚን እና ሀሪ ኬን ሁለት ግቦችን አስቆጥረዋል ። ሀሪ ኬን በሰሜን ለንደን ደርቢ ላይ አስራ ሶስተኛ ግቡን ማስቆጠር ችሏል ። በአርሰናል በኩል ሮብ ሆልዲንግ በ 33ተኛው ደቂቃ በቀይ ካርድ ከሜዳ ተሰናብቷል ። ሚኬል አርቴታ አርሰናልን ከተረከበ በኋላ በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መድፈኞቹ 13 ቀይ ካርዶችን ተመልክተዋል ። ሰን ሁንግ ሚን በዘንድሮ የውድድር አመት ሀያ አንደኛ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ግቡን አስቆጥሯል ። ውጤቱን ተከትሎ አርሰናል በ 66 ነጥብ አራተኛ ደረጃ ላይ ሲቀመጥ ቶተንሀም በ 65 ነጥብ አምስተኛ ደረጃ ላይ ይገኛል ።


• @ThinkAbyssinia •
1.4K views07:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ