Get Mystery Box with random crypto!

Think Abyssinia

የቴሌግራም ቻናል አርማ thinkabyssinia — Think Abyssinia T
የቴሌግራም ቻናል አርማ thinkabyssinia — Think Abyssinia
የሰርጥ አድራሻ: @thinkabyssinia
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 157
የሰርጥ መግለጫ

➠ ፈጣን እና ተዐማኒ መረጃ፣
➠ የስፓርት እና መዝናኛ ዘገባዎች፣
➠ የምሁራን እይታዎችና መጽሐፈቶች፣
➠ የአለም ሙሉ መረጃና የታሪክ መዛግብቶች ።
ለማንኛውም መረጃ ➥ @Contact_Thinkabyssinia

🎬 "ተመራጭ የዜና ምንጭ"

Ratings & Reviews

3.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 88

2022-05-16 09:18:05
ፕሬዚዳንት ፋርማጆ ለአዲስ ተመራጩ ፕሬዚዳንት የእንኳን ደስ አለህ መልእክት አስተላለፉ

የቀድሞው የሶማሊያ ፕሬዚዳንት መሃመድ አብዱላሂ ፋርማጆ ለአዲስ ተመራጩ የሶማሊያ ፕሬዚዳንት ሀሰን ሼክ መሃመድ የእንኳን ደስ አለህ መልእክት አስተላልፈዋል።

መሃመድ አብዱላሂ ፋርማጆ በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ባስተላለፉት መልእክት “ወንድሜ ፕሬዚዳንት ሀሰን ሼክ መሃመድ 10ኛው የሶማሊያ ፕሬዝዳንት ሆነህ በመመረጥህ እንኳን ደስ አለህ” ብለዋል።

መላው የሶማሊያ ሕዝብም ለአዲሱ ተመራጭ ፕሬዚዳንት ድጋፋቸውን እንዲሰጡ እና ለስኬታቸውም እንዲፀልዩ መሃመድ አብዱላሂ ፋርማጆ ጥሪ አቅርበዋል። መሃመድ አብዱላሂ ፋርማጆ ምርጫው በሰላማዊ መንገድ እንዲጠናቀቅ አስተዋፅኦ ላበረከቱ ሁሉ ምስጋናቸውን ገልፀዋል።

• @ThinkAbyssinia •
8.1K views06:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-16 06:48:33
የቀድሞው የሶማሊያ ፕሬዜዳንት ሀሰን ሼክ ሞሐመድ የሶማሊያ ፕሬዜዳንት ሆነው ተመረጡ

ሀሰን ሼክ ሞሐመድ የአሁኑን የሶማሊያ ፕሬዜዳንት ሞሀመድ አብድላሂ ፈርማጆን እጅግ ፉክክር በተሞላበት ሶስት ዙር የምርጫ ሂደት አሸንፈዋቸዋል።

ቀደም ሲል በቲንክአቢሲኒያ የመክሰስ የመረጃ ጥንቅራችን በሶማሊያ ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ሰይድ አብዱላሂ ዴኒ የመጀመሪያ ዙር እየመሩ እንደሚገኙ መረጃ አድርሰናቹ ነበር።

ለማስታወስ ያህል በመጀመሪያ ዙር ሰይድ አብዱላሂ ዴኒ በ65 ደምጽ ቀዳሚ ሲሆኑ ፕሬዝዳንት መሃመድ አብዱላሂ ፋርማጆ በ61 ድምጽ በሁለተኝነት እየተከተሉ ነበር። ሀሰን ሼክ መሃመድ 52 ድምጽ እንዲሁም ሀሰን አሊ ካሂሬ 48 ድምጽ በማግኘት ወደ ሁለተኛ ዙር ምርጫ ማለፋቸው ጠቅሰን ነበር።

ማምሻውን በተካሄደው ሁለተኛ ዙር ፕሬዝዳንታዊ የምርጫ ፉክክር የቀድሞው ፕሬዝዳንት ሐሰን ሼክ ሞሐመድ 110 ድምጽ እና የወቅቱ የአገሪቱ ፕሬዝዳንት ሞሐመድ ፎርማጆ 83 ድምጽ በማግኘት አንደኛ እና ሁለተኛ ሆነው ለሦስተኛው ዙር ምርጫ አልፈው ነበር።

በሦስተኛው ዙር ምርጫ ሀሰን ሼክ ሞሐመድ የአሁኑን የሶማሊያ ፕሬዜዳንት ሞሀመድ አብድላሂ ፈርማጆን እጅግ ፉክክር በተሞላበት ሶስት ዙር የምርጫ ሂደት አሸንፈዋቸዋል

• @ThinkAbyssinia •
1.2K viewsedited  03:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-15 22:13:11
#Breaking

በሱማሊያ ማምሻውን በተካሄደው ሁለተኛ ዙር ፕሬዝዳንታዊ የምርጫ ፉክክር የቀድሞው ፕሬዝዳንት ሐሰን ሼክ ሞሐመድ 110 ድምጽ እና የወቅቱ የአገሪቱ ፕሬዝዳንት ሞሐመድ ፎርማጆ 83 ድምጽ በማግኘት በማግኘት አንደኛ እና ሁለተኛ ሆነው ለሦስተኛው ዙር ምርጫ አልፈዋል።

በመጀመሪያው ዙር በ65 ድምጽ በአንደኛ ደረጃ ሲመሩ የነበሩት የፑንትላንዱ ፕሬዝዳንት አብዱላሂ ደኒ እና የቀድሞው ጠቅላይ ሚንስትር ሐሰን ካይሬ ሦስተኛ እና አራተኛ ደረጃ በማግኘት ከፉክክሩ ውጭ ሆነዋል።


ሁለተኛውን ዙር ፉክክር በቀዳሚነት ያሸነፉት ሐሰን ሼክ ሞሐመድ ከአሁኑ ፕሬዝዳንት ፎርማጆ በፊት አገሪቱን የመሩ ናቸው።


Wazema

• @ThinkAbyssinia •
5.7K views19:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-15 20:16:16
በኮምቦልቻ ከተማ የሚገኙ 26 ኢንዱስትሪዎች ከደረሰባቸው ውድመት አገግመው ወደ ስራ መግባታቸው ተገለጸ

በኮምቦልቻ ከተማ አስተዳደር የሚገኙ 26 ኢንዱስትሪዎች ከደረሰባቸው ውድመት አገግመው ወደ ስራ መግባታቸውን የገለፀው የኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት መምሪያ ነው፡፡

ከእነዚህ መካከል 10 የሚሆኑት ኢንዱስትሪዎች ከክልል የኢንዱስትሪ እና ኢንቨስትመንት ቢሮ ምክክር ጉባኤ በኋላ ወደስራ የገቡ ናቸው ተብሏል፡፡

በአሁኑ ወቅት የአምራች ኢንዱስትሪዎችን ምርታቸውን ወደ ውጭ በመላክ የውጭ ምንዛሬን በጨርቃ ጨርቅ እና ቆዳ እንዲሁም በግብርና ማቀነባበሪያ ዘርፎች በዘጠኝ ወራት ውስጥ 19 ሚሊየን 806 ሺህ 957 ከ80 ዶላር ማግኘት መቻሉም ተገልጿል።

• @ThinkAbyssinia •
7.4K views17:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-15 19:30:55 #ቲንክአቢሲኒያ_የመክሰስ_መረጃዎች

1፥ወልድያ ከተማ የ"መቀመጭት ተራራን" በአቡነ ኤርምስ ስም መሰየሙን አስታወቀ።

የተራራውን ስያሜ የሰጠው ከተማ አስተዳደሩ አቡነ ኤርምያስ ያደረጉትን ውለታ በማሰብ እና ለአቡኑ ተያያዥ የልማት የቤት ሥራዎች ለመስጠት መሆኑን ገልጿል። የዕፅዋት ሳይንስ መድኃኒት ቅመማ ጋር ተያይዞ ለምርምር የሚሆኑ ሀገር በቀል ዕፅዋቶች በስፋት የሚገኙበት ተራራ በመሆኑ የጥንት መጻሕፍትን በመተርጎም የሚመራመሩ ሊቃውንትን በተራራው በማሰማራት የምርምር ማዕከል እንደሚያደርጉት ታላቅ ተስፋ ስለተጣለባቸው ስያሜው የተሰጠበት አንደኛው ምክንያት እንደሆነ ተገልጿል። ተራራው ከፍ ያለ ዕይታ ባላቸው አባት ስም መሰየሙ ክብሩ ለተሰየመለት ሰው ብቻ ሳይሆን የብፁዕነታቸውን አገልግሎት ለቀመሰው እና ላጣጣመው ለመላው የወልድያና አካባቢው ሕዝብ እና ከተማ አስተዳደሩ ጭምር ነው ሲል ወልድያ ከተማ ኮሙኒኬሽን አስታውቋል።

2፤በኢትዮጵያ በየዓመቱ ከ20ሺህ በላይ ሰዎች በቲቢ በሽታ ሕይወታቸው ያልፋል ተባለ።


በአለም ለ40ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ25ኛ ጊዜ እየተከበረ የሚገኘው የአለም የቲቢ ቀን በድሬዳዋም በከተማ ደረጃ ቀኑ የተከበረ ሲሆን በመድረኩ የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ጤና ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ዩሱፍ ሰኢድ የበሽታው በትንፋሽ የሚተላለፍ መሆን ከአኗኗሯችን ሁኔታ ጋር ተዳምሮ የቁጥጥር ስራውን አስቸጋሪ አድርጎታል ብለዋል። በድሬዳዋ አስተዳደር ከ2005 ዓ/ም ጀምሮ በ31 የህክምና መስጫ ማእከላት የቲቪ ህክምና አገልግሎት እየተሰጠ ይገኛል ያሉት ሃላፊው፤ "አገልግሎቱን ካገኙት ተማሚዎች ውስጥ ሰባ ከመቶ ያህሉ ህክምናቸውን በስኬት ያጠናቀቁ ናቸው” ሲሉ አምልክተዋል። በመድረኩ በቀረበ ጽሑፍ በኢትዮጵያ በአመት 20 ሺህ ሰዎች በቲቪ በሽታ ህይወታቸው እንደሚያልፍ ተገልጿል። ቲቢ በኢትዮጵያ በገዳይነቱ በአንደኛ ደረጃ ላይ ይገኛል ነው ያሉት።

3፤የቻይናው ባሉን የዓለም በከፍታ የመብረር ክብረ ወሰንን ሰበረ።

የቻይናው ተንሳፋፊ ባሉን ከምድር 9 ሺህ 32 ሜትር ከፍታ ላይ መንሳፈፍ በመቻሉ ነው የዓለም የከፍታ ክብረ ወሰንን የሰበረው። በጉዙፍነቱ ምክንያት “ተንሳፋፊው መርከብ” ተብሎ የሚጠራው እና‹‹ጂሙ ቁጥር 1›› በሚል ስያሜ የተሰጠው ይህ ባሉን 2.625 ቶን የሚመዝን ሲሆን ሂሊየም በተሰኘ ጋዝ ተሞልቶ በአየር ላይ በሰከንድ 30 ሜትር የሚቀዝፍ እንደሆነ ተነግሯል። ከ8 ሺህ 840 ሜትር በላይ ከሚረዝመው እና በቻይና እና በኔፓል ድንበር አካባቢ ከሚገኘው ኮሞላግማ ተራራ ጫፍ ከሚገኘው የምርምር ጣቢያ የተለቀቀው ባሉኑ ከ9 ሺህ ሜትር በላይ በመንሳፈፍ ነው ክብረ ወሰኑን ለመስበር የቻለው።

4፤የፊንላንድ መሪዎች ሀገራቸው ኔቶን መቀላቀል እንደምትፈልግ በይፋ አሳወቁ።

የፊንላንድ ፕሬዚዳንት ሳውሊ ኒኒስቶ ከካቢኔያቸው ጋር ባደረጉት ስበስባ ላይ ፊንላንድ የኔቶ አባል ለመሆን በምታቀርበው የአባልነት ጥያቄ ላይ ስምምነት ላይ ደርሰዋል። ይህን የካቤኒ ስምምነት ተከትሎም የአባልነት ጥያቄው ለመጽደቅ የፓርላማ ይሁንታ ማግኘት ይኖርበታል ተብሏል። የፊንላንድ ጠ/ሚ ሳና ማሪን ውሳኔውን " ታሪካዊ ነው " ያሉ ሲሆን " ዋናው ነገር የፊንላንድና የህዝቦቿ ደህንነት ነው " ሲሉ ገልጸዋል። ውሳኔው የኖርዲክ አካባቢ ሃገራትን ፀጥታና ትብብር ያጠናክራልም ብለዋል። ሩስያ ሰሞኑን የፊንላንድ የኔቶ አባል የመሆን ፅኑ ፍላጎትን ተከትሎ ማስጠንቀቂያ መስጠትዋም አይዘነጋም። ሩስያ በአሁን ሰዓት ከዩክሬን ጋር በጦርነት ውስጥ የምትገኘው ሀገሪቱ የNATO አባል የመሆን ፍላጎት ማሳየቷን ተከትሎ እንደሆነ ይታወቃል።

5፤በሶማሊያ ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ሰይድ አብዱላሂ ዴኒ እየመሩ ይገኛሉ።

የሀገሪቱ ፓርላማ በፀጥታ ስጋት በሀጋር አውሮፕላን ማረፊያ ውስጥ እያካሄደ ባለው ምርጫ እስካሁን የመጀመሪያ ዙር ውጤት ታውቋል። በዚህም ሰይድ አብዱላሂ ዴኒ በ65 ደምጽ እየመሩ ሲሆን፤ ፕሬዝዳንት መሃመድ አብዱላሂ ፋርማጆ በ61 ድምጽ በሁለተኝነት እየተከተሉ መሆኑን ሲ.ጂ.ቲ.ኤን ዘግቧል። ሀሰን ሼክ መሃመድ 52 ድምጽ እንዲሁም ሀሰን አሊ ካሂሬ 48 ድምጽ በማግኘት ለሁለተኛ ዙር ምርጫ ማለፋቸው ተነግሯል። እየተካሄደ ባለው ምርጫ ላይ ለመወዳደር በስልጣን ላይ ያሉትን መሃመድ አብዱላሂ መሃመድ ፋርማጆን ጨምሮ 39 ሰዎች ለፕሬዝዳንትነት ለመወዳደር በእጩነት ቀርበዋል። በተጨማሪም የቀድሞዋ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ፋውዚያ የሱፍ ሀጂ አደም ብቸኛዋ ሴት እጩ ሆነው ቀርበዋል።

6፤ማንችስተር ሲቲ ነጥብ ተጋርቷል።

የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የሰላሳ ሰባተኛው ሳምንት ጨዋታ በለንደን ስታዲየም ቀጥሎ ሲካሄድ ማንችስተር ሲቲ ከ ዌስትሀም ያደረገውን ጨዋታ 2 - 2 በሆነ ውጤት አጠናቋል ። የማንችስተር ሲቲን ግቦች ጃክ ግሪሊሽ እና ሶፊያን ኩፋል በራሱ መረብ ላይ ሲያስቆጥሩ የዌስትሀምን ሁለት ግቦች ጃሮድ ቦውን ማስቆጠር ችሏል ። ጃሮድቦውን በዘንድሮ የውድድር አመት 18 ግቦችን በሁሉም ውድድሮች ላይ አስቆጥሯል ። ሪያድ ማህሬዝ ማንችስተር ሲቲ ያገኘውን የፍፁም ቅጣት ምት አባክኗል ። የዛሬውን ውጤት ተከትሎ ማንችስተር ሲቲ ሊጉን በ 90 ነጥብ ሊጉን መምራቱን ሲቀጥል ዌስትሀም በ 56 ነጥብ ሰባተኛ ደረጃ ላይ ይገኛል ።

7፤ቼልሲ የሴቶች ኤፍ ኤ ካፕ አሸናፊ መሆኑ ተረጋግጧል።

የእንግሊዝ የሴቶች የኤፍ ኤ ካፕ የፍፃሜ ጨዋታ በዌምብሌ ስታዲየም ሲካሄድ ቼልሲ ከ ማንችስተር ሲቲ ጋር ያደረገውን ጨዋታ 3 - 2 በሆነ ውጤት አሸንፏል ። ቼልሲ በሳማንታ ከር ሁለት ግቦች እና ኤሪክ ኩተበርት ሶስት ግቦች ማንችስተር ሲቲን በማሸነፍ ለአራተኛ ጊዜ የእንግሊዝ የሴቶች ኤፍ ኤ ካፕን ማሸነፋቸውን አረጋግጠዋል ። የቼልሲ የሴቶች ቡድን በባለፈው ሳምንት የእንግሊዝ የሴቶች ሱፐር ሊግን ማሸነፉ ይታወሳል ።

• @ThinkAbyssinia •
7.4K views16:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-15 13:30:59
የሶማሊያ ፖሊስ ምርጫው እስኪጠናቀቅ ናዋሪዎች ከቤት እዳይወጡ አገደ


ሶማሊያ በተለያዩ ምክንያች ለሁለት ዓመት የተራዘመውን የሀገሪቱ ፕሬዝዳንት ምርጫ በዛሬው እለት እንደምታካሂድ ይጠበቃል። ዛሬ በሚካሄደው ምርጫ ላይ ለመወዳደር በስልጣን ላይ ያሉትን መሃመድ አብዱላሂ መሃመድ ፋርማጆን ጨምሮ 39 ሰዎች ለፕሬዝዳንትነት ለመወዳደር በእጩነት ቀርበዋል።

የሶማሊያ ፖሊስ ቃል አቀባይ አብዲፈታህ አደን በትናትናው እለት በሰጡት መግለጫ፤ ሞቃዲሾ ከተማ ለ33 ሰዓታት ማለትም ከትናንት ምሽት 3 ሰዓት እስከ ነገ ጠዋት 12 ሰዓት ድረስ የትራፊክ እና ሰዎች እንቅስቃሴ ላይ ክልከላ መጣሉን አስታውቀዋል።

ፕሬዝዳናታዊ ምርጫውም በሀጋር አውሮፕላን ማረፊያ ውስጥ ሲሆን፤ ይህም ሊፈፀም የሚችል የሽበር ጥቃትን ለመከላል በሚያስችል ስፍራ ነው ተብሏል።

ሶማሊያዊያን ፕሬዝዳንታቸውን በቀጥታ ባይመርጡም በተወካዮቻቸው አማካኝነት የሚመርጡ ሲሆን 300 የሚሆኑት የሶማሊያ የጎሳ ተወካዮች ቀጣዩን የሀገሪቱ ፕሬዝዳንት እንደሚመርጡ ይጠበቃል፡፡


አልአይን

• @ThinkAbyssinia •
4.2K views10:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-15 12:32:42
ዛሬ ምሽት ሙሉ የጨረቃ ግርዶሽ እንደሚታይ ተገለፀ

በተለያዩ የዓለማችን አካባቢዎች ዛሬ ምሽት እና ነገ ማለዳ ሙሉ የጨረቃ ግርዶሽ እንደሚታይ ቢቢሲ ዘግቧል። ከግርዶሹ ደቂቃዎች በፊት ጨረቃ ብርቱካናማ ቀይ መልክ ይዛ ወይንም “ደም ለብሳ” የምትታይ ሲሆን ክስተቱ ከፕላኔታችን አስደናቂ እይታዎች አንዱ የሆነው የጨረቃ ግርዶሽ በሰማይ ላይ ይሆናልም ተብሏል።

ሙሉ የጨረቃ ግርዶሽ የሚፈጠረው ምድር በፀሐይ እና በጨረቃ መካከል በምትሆንበት ጊዜ የሚከሰት ነው። ክስተቱ በአብዛኛዎቹ የአውሮፓ አገራት ሰኞ ማለዳ እንደሚታይ የሚጠበቅ ሲሆን በአሜሪካ ደግሞ በአንፃሩ ዛሬ እሁድ ምሽት ላይ ያያሉ ነው የተባለው።

ጨረቃ ከምህዋሯ በጣም ቅርብ በሆነ ቦታ ላይ እንደምትሆንና ከወትሮው በበለጠ ተልቃና ገዝፋ እንደምትታይም ይጠበቃል ተብሏል።

በመሆኑም ማንኛውም ሰው የጨረቃ ግርዶሹን ክስተት በዓይን ማየት የሚችል ሲሆን አቅርቦ ማሳያ (ባይኔኩላር) ወይም አነስተኛ ቴሌስኮፕ በመጠቀምም የሚፈጠረውን የቀይ ቀለም የበለጠ ለማየት ይችላል ነው የተባለው።

bbc

• @ThinkAbyssinia •
5.3K views09:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-15 12:28:07
በኒውዮርክ የመገበያያ አዳራሽ በተከፈተ ተኩስ የአስር ሰዎች ህይወት አለፈ

በኒውዮርክ የመገበያያ አዳራሽ በተከፈተ ተኩስ የአስር ሰዎች ህይወት ያለፈ ሲሆን ጥቃቱ ዘርን መሰረት ያደረገ የጥላቻ ወንጀልም ነው በሚል ፖሊስ ምርመራ ከፍቷል።

ጥቃቱን ፈጽሟል የተባለ የ18 አመት ወጣት በቡፋሎ ከተማ በቁጥጥር ስር ውሏል። ፖሊስ የግለሰቡን ማንነት ይፋ አላደረገም። ተጠርጣሪው ቅዳሜ ከሰአት በኋላ በተጨናነቀ የመገበያያ አዳራሽ ከገባ በኋላ ነው ተኩስ የከፈተው።

ተጠርጣሪው በከተማዋ ጥቁሮች በብዛት ወደሚገኙበት አካባቢ ለመድረስ ለበርካታ ሰዓታት መኪና ማሽከርከሩ ተሰምቷል። የቡፋሎ ፖሊስ ኮሚሽነር ጆሴፍ ግራማሊያ እንዳሉት 13 ሰዎች በጥይት የተመቱ ሲሆን አብዛኞቹ ጥቁሮች ናቸው።

በመገበያያ አዳራሹ በጥበቃ ስራ ላይ የነበረ አንድ ጡረታ የወጡ ፖሊስ ተጠርጣሪው ላይ በጥይት ለመተኮስ ቢሞክሩም በዚህ ጥቃት ከተገደሉት መካከል አንዱ ሆነዋል። ተጠርጣሪው ከፍተኛ ሃይል ያለው ሽጉጥ፣ የሰውነት መከላከያ ትጥቅ እንዲሁም የጭንቅላት መከላከያ ሄልሜት አድርጎ እንደነበር ፖሊስ ተናግሯል።


bbc

• @ThinkAbyssinia •
5.0K views09:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-15 10:47:21 #ቲንክአቢሲኒያ_የቡናቁርስ_መረጃዎች

1፤በደንዲ ሀይቅ ላይ ዘመናዊ ሎጅ ለመገንባት የመሰረት ድንጋይ ተቀመጠ።

በኦሮሚያ ብሔራዊ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን ከአዲስ አበባ 127 ኪ.ሜ ርቀት ላይ በሚገኘው ደንዲ ሐይቅ የገበታ ለሀገር ፕሮጀክት አካል በሆነው የደንዲ ሃይቅ ላይ ዘመናዊ ኢኮ-ቱሪዝም ሎጅ ለመገንባት የመሰረት ድንጋይ ተቀምጧል። የኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ ሽመልስ አብዲሳ እና የጣልያኑ "ዊ ቢውልድ" ኮንስትራክሽን ድርጅት ዋና ስራ አስፈፃሚ ፔትሮ ሳሊኒ የመሰረት ድንጋዩን አስቀምጠዋል። በመርሀ ግብሩ ላይ የወንጪ ደንዲ ኢኮ-ቱሪዝም ፕሮጀክት አስተባባሪና የመከላከያ ሚኒስትር
ዶክተር አብርሃም በላይን ጨምሮ የተለያዩ የስራ ኃላፊዎችና የአካባቢው ነዋሪዎች ተገኝተዋል።
የገበታ ለሃገር ፕሮጀክት ዋና ዓላማ በቅድሚያ የአካባቢውን ማህበረሰብ ተጠቀሚነት ማረጋግጥ ስመሆኑ በዚሁ እለት ተጠቁሟል።

2፤በአዲስ አበባ ከተማ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች የአካል ብቃት እንቅስቃሴ አካሄዱ።

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በ11ዱም ክፍለ ከተሞች የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች የአካል ብቃት እንቅስቃሴ አካሄዱ። ዛሬ ማለዳ ከ12 ሰዓት ጀምሮ በተካሄደው የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች፣ ወጣቶች፣ ስፖርተኞች በየአካባቢያቸው በነቂስ ወጥተው ተሳትፎ አድርገዋል። በዚህም አዲስ አበባ የሰላም፣ የፍቅር፣ የመቻቻልና የአብሮነት ከተማ መሆኗን በተግባር አስመስክረዋል በማለት የአዲስ አበባ ከተማ ወጣቶች እና ስፖርት ቢሮ መረጃ ገልጿል።

3፤መንግሥት ለውጭ አገር ዜጎች ዲጂታል መታወቂያ ሊሰጥ እንደሆነ ተገለፀ።

መንግሥት ለውጭ አገር ዜጎች ዲጂታል መታወቂያ ሊሰጥ እንደሆነ ሪፖርተር ዘግቧል። የውጭ ዜጎች ዲጂታል መታወቂያ መያዛቸው ግን ዜጎች የሚያገኟቸውን አገልግሎቶች ሁሉ እንዲያገኙ እንደማያስችላቸው የብሄራዊ ዲጂታል መታወቂያ ፕሮጀክት ጽሕፈት ቤት ተናግሯል። መንግሥት ዲጂታል መታወቂያ ለመስጠት የሚያስችለውን ሕግ ያረቀቀ ሲሆን፣ ሕጉ አገልግሎት ሰጭ ተቋማት አገልግሎት ሲሰጡ ተገልጋዮች ዲጂታል መታወቂያ ያላቸው መሆኑን እንዲያረጋግጡ ያስገድዳል።

4፤ ሩሲያ ለፊንላንድ የምታቀርበውን የኤሌክትሪክ ኃይል ልታቋርጥ ነው።

አርኤኦ ኖርዲክ የተሰኘው የሩሲያ የኤሌክትሪክ ኃይል አቅራቢ ተቋም ከክፍያ ጋር በተያያዘ ችግር እንደገጠመው በመግለጽ ለፊንላንድ የሚያቀርበውን የኤሌክትሪክ ኃይል ከትላንት ቅዳሜ ጀምሮ እንደሚያቋርጥ አስታወቀ። ተቋሙ ከዚህ በፊት ላቀረብኩት አገልገሎት ክፍያ አላገኘሁም ብሏል። ሆኖም የፊንላንድ የኤሌክትሪክ ኃይል አስተዳዳሪ ተቋም አገሪቱ ከሩሲያ የምታገኘው የኃይል መጠን ድርሻ ዝቅተኛ እና በሌላ አማራጭ ሊተካ የሚችል ነው የሚል ምላሽ ሰጥቷል። ከቀናት በፊት ፊንላንድ ኔቶን የመቀላቀል ዕቅድ እንዳላት ከገለጸች በኋላ ጎረቤቷ የምዕራባውያኑ የጦር ማኅበር አባል የምትሆን ከሆነ ሩሲያ የበቀል እርምጃ እንደምትወስድ ዝታ ነበር።

5፤በድሬዳዋ ”ለፍቅር እሮጣለሁ” በሚል መሪ ሃሳብ የጎዳና ላይ ሩጫ ውድድር ተካሄደ።

በድሬዳዋ ከተማ ”ለፍቅር እሮጣለሁ” በሚል የ5 እና የ10 ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ ሩጫ ውድድር ተካሄደ። በውድድሩ ላይ ከአንድ መቶ በላይ ታዋቂ ወንድና ሴት አትሌቶች እና በሺዎች የሚቆጠሩ የከተማዉ ነዋሪዎች ተሳትፈውበታል። መነሻና መድረሻውን ድሬዳዋ ምድር ባቡር አደባባይ ያደረገና የከተማዋን ዋና ዋና ጎዳናዎችን ያካተተውን ውድድር የድሬዳዋ ስፖርት ኮሚሽን ከሔማ ሬስ ኢንተርናሽናል ጋር በመተባበር አዘጋጅተዋል። የዉድድሩ ዓላማ ድሬዳዋ የምትታወቅበት የፍቅርና የአብሮነት ዕሴቶች በይበልጥ ለማጠናከር ያለመ ስለመሆኑ በአዘጋጆቹ ተገልጿል። በተካሄደው የ10 ኪሎሜትር ወድድር በሴቶች እመቤት ንጉሴ 1ኛ ስትወጣ፣ ያለም ጌጥ ያረጋል እና አዳኔ አንማው ከውሃ ስራዎች ስፖርት ክለብ 2ኛ እና 3ኛ ወጥተዋል። በወንዶች ገመቹ ጊሼ ከፌደራል ፖሊስ 1ኛ፣ ደበበ ተካ ከፌደራል ማረሚያ 2ኛ እንዲሁም ሙሉጌታ አሰፋ ከመከላከያ 3ኛ በመሆን ወድድራቸውን አጠናቀዋል።


• @ThinkAbyssinia •
2.0K views07:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-15 10:45:59
#ቲንክአቢሲኒያ_እለታዊ_የአየር_ትንበያ_መረጃ

ለውሎዎ ጠቃሚ የሆኑ እለታዊ የአየር ትንበያ መረጃዎችን እናድርስዎ


ዛሬ በአንዳንድ የሀገራችን ከተሞች ያለውን ያየር ሁኔታ ስንመለከት መዲናችን አዲስ አበባ ዝቅተኛው 13 ከፍተኛው 29 ድግሪ ሲልሽየስ ፀሀያማ ሆና ትውላለች።

ባህርዳር ዝቅተኛው 13 ከፍተኛው 33 ፀሀያማ ሀዋሳ ዝቅተኛው 14 ከፍተኛው 31 ከፊል ደመናማ እንዲሁም መቀሌ ዝቅተኛው 16 ከፍተኛው 29 ፀሀያማ ሆነው እንደሚውሉ ቲንክአቢሲንያ ከቤሄራዊ ሜትሮዎሎጂ ኤጀንሲ ድረገፅ ተመልክቷል።


• @ThinkAbyssinia •
2.0K views07:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ