Get Mystery Box with random crypto!

Think Abyssinia

የቴሌግራም ቻናል አርማ thinkabyssinia — Think Abyssinia T
የቴሌግራም ቻናል አርማ thinkabyssinia — Think Abyssinia
የሰርጥ አድራሻ: @thinkabyssinia
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 157
የሰርጥ መግለጫ

➠ ፈጣን እና ተዐማኒ መረጃ፣
➠ የስፓርት እና መዝናኛ ዘገባዎች፣
➠ የምሁራን እይታዎችና መጽሐፈቶች፣
➠ የአለም ሙሉ መረጃና የታሪክ መዛግብቶች ።
ለማንኛውም መረጃ ➥ @Contact_Thinkabyssinia

🎬 "ተመራጭ የዜና ምንጭ"

Ratings & Reviews

3.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 87

2022-05-16 18:58:46 #ቲንክአቢሲኒያ_የመክሰስ_መረጃዎች

1፤የገንዘብ ሚኒስቴር እና የዓለም ባንክ የ300 ሚሊየን ዶላር የድጋፍ ስምምነት ተፈራረሙ።

የዓለም ባንክ በኢትዮጵያ በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን ለመልሶ ማቋቋሚያ የሚሆን የ300 ሚሊየን ዶላር ድጋፍ ለማድረግ ከገንዘብ ሚኒስቴር ጋር ስምምነት ተፈራርመዋል። ስምምነቱን የገንዘብ ሚኒስትሩ አህመድ ሽዴ በዓለም ባንክ የኢትዮጵያ፣ ሱዳን፣ ደቡብ ሱዳንና የኤርትራ ዳይሬክተር ኦስማን ዲዮን ጋር ተፈራርመዋል። የድጋፍ ስምምነቱ በአማራ፣ አፋር፣ ትግራይ፣ ኦሮሚያና ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልሎች በግጭት ለተጎዱ አካባቢዎች ለመልሶ ግንባታና መልሶ ማቋቋሚያ የሚውል ነው ተብሏል። ድጋፉ በተመረጡ የግጭት ተጎጂ ወረዳዎች የጤና፣ የትምህርትና የውሃ መሰረት ልማት መዘርጋት ብሎም ለፆታዊ ጥቃት የተጋለጡ ሴቶችን ለመደገፍና መልሶ ለማቋቋም እንደሚውልም ተመላክቷል፡፡

2፤1ሺህ 40 ኢትዮጵያውያን ከሳዑዲ ዓረቢያ ወደ አገራቸው ተመለሱ።

በዛሬው ዕለት በሶስት ዙር በተከናወነ ዜጎችን ከሳዑዲ ዓረቢያ የመመለስ ስራ 1 ሺህ 40 ኢትዮጵያውያንን ወደ አገራቸው ተመልሰዋል፡፡ ከተመላሾች ውስጥም 303 ሴቶች ሲሆኑ 90 የሚሆኑት ደግሞ ህጻናት መሆናቸው ተገልጿል፡፡ ለተመላሽ ዜጎች ተገቢውን ድጋፍ እና እንክብካቤ በማድረግ ወደ ተዘጋጁላቸው የማቆያ ማዕከላት እንዲሄዱ መደረጉን ከከሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመላክታል። እስካሁን ድረስ በተከናወነው ዜጎችን የመመለስ ስራ ቁጥራቸው ከ 23 ሺህ 640 በላይ ኢትዮጵያውያንን መመለስ መቻሉ ተመላክቷል፡፡

3፤የአሜሪካው ፕሬዚዳንት በኒው ዮርክ የ10 ሰዎች ሕይወት የጠፋበትን የዘር ተኮር ጥቃት አወገዙ።

የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ጆ ባይደን በኒው ዮርክ ከተማ የ10 ሰዎች ሕይወት የጠፋበትን ዘር ተኮር የጥላቻ ጥቃትን አውግዘዋል። በትላንትናው ዕለት በፋሎ በተባለ አካባቢ በሚገኝ የንግድ ማዕከል ውስጥ በአንድ የነጭ የበላይነት አቀንቃኝ መሆኑ በተነገረለት የ18 ዓመት ወጣት በተተኮሰ ጥይት የሞቱ ሰዎች ዝርዝር ይፋ ሆኗል። ወጣቱ ጥቃት ያደረሰባቸው ሰዎች ቁጥር 13 ሲሆን ከእነዚህ መካከል የ10 ሰዎች ሕይወት ወዲያው ማለፉ ተገልጿል። የወንጀል ድርጊቱን ያወገዙት የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ጆ ባይደን፣ የዘር ጥላቻ ችግርን ለመፍታት በጋራ መሥራት ይገባል ብለዋል። በአሜሪካ የትላንቱ የጅምላ ግድያ የፈረንጆቹ አዲስ ዓመት ከገባ ወዲህ ከፍተኛው ነው ተብሏል።

4፤በህንድ ዋና ኒዉ ዴሊህ 49 ዲግሪ ሴንቲግሬድ ከባድ ሙቀት ተመዘገበ።

በሰሜናዊ ህንድ ከፍተኛ የሆነ የሙቀት ማዕበል መኖሩ የተነገረ ሲሆን በዋና ከተማዋ ኒዉ ዴሊህ አንዳንድ አካባቢዎች የሙቀት መጠኑ 49.2 ዲግሪ ሴንቲግሬድ መድረሱ ተመላክቷል፡፡በዋና ከተማው ከመጋቢት ወር ጀምሮ እንዲህ ዓይነት ሙቀት የሙቀት ሞገድ ሲመዘገብ የአሁኑ ለአምስተኛ ጊዜ ነዉ፡፡ የሙቀት መጠኑ ከፍተኛ ሆኖ በመቀጠሉ በበርካታ የአገሪቱ ክፍሎች የሚገኙ የመንግስት ባለስልጣናት ህዝቡ ጥንቃቄ እንዲያደርግ ጠይቀዋል። ሙቀቱ ጨቅላ ሕፃናትን፣ አዛውንቶችን እና ሥር የሰደደ በሽታ ያለባቸውን ሰዎች ጨምሮ ለአደጋ ተጋላጭ በሆኑ ሰዎች ላይ የጤና ስጋት ሊፈጥር እንደሚችል አስጠንቅቀዋል። በህንድ በተለይ በግንቦት እና ሰኔ ወር ከፍተኛ ሙቅት የተለመደ ቢሆንም በተያዘዉ አመት ከመጋቢት ወር ጀምሮ የሙቀት መጠኑ ከፍተኛ ሆኖ ተመዝግቧል፡፡

5፤የኢትጵያ ሴቶች ብሄራዊ ቡድን በሴካፋ ዋንጫ ለሚሳተፉ 23 ተጨዋቾች ጥሪ አቀረበ።

የኢትጵያ ሴቶች ብሄራዊ ቡድን በአሰልጣኝ ፍሬው ሀይለገብርኤል በኩል በዩጋንዳ አስተናጋጅነት ለሚካሄደው የሴካፋ ሴቶች ዋንጫ ለሚሳተፉ 23 ተጨዋቾች ጥሪ አቅርቧል፡፡ ተጫዋቾቹ ነገ በጁፒተር ሆቴል ተገኝተው ሪፖርት እንደሚያደርጉ መደረጉን ከኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡ ሉሱዎቹ በምድብ ሁለት መደልደላቸው የሚታወስ ሲሆን የምድባቸውን የመጀመሪያ ጨዋታ ግንቦት 25 ከ ዛንዚባር አቻቸው ጋር የሚያካሂዱ ይሆናል ። ውድድሩ ግንቦት 24 ጀምሮ ከአስር ቀናት ቆይታ በኋላ ሰኔ 4 ፍፃሜውን እንደሚያገኝ የወጣው መርሐ ግብር ያመላክታል ።

• @ThinkAbyssinia •
6.5K views15:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-16 16:57:02
ለሰርግ ወደ አዲስ አበባ የመጣችው ሀናን


ሃናን ትባላለች የ25 አመት ወጣት የዩኒቨርሲቲ ተማሪ ነች፣ ከእጮኛዋ ጋር ኒካ ለማሰር ስላሰቡ አዲስ አበባ በመምጣት ለሰርጋቸው የሚያስፈልጋቸው እቃዎች ለመግዛት በአንድ ሆቴል 8ኛ ፎቅ ማረፊያቸውን አደረጉ ሲል የአዲስ አበባ ፖሊስ ከታዲያስ አዲስ ጋር በነበረው ቆይታ ገልጿል።

በሆቴሉ እንዳሉ በመካከላቸው አለመግባባት ተፈጥሮ ይጨቃጨቃሉ እሱ ክፍሉን ጥሎ ወጣ ከቆይታ በኋላ የሆቴሉን ባልደረባ "እስቲ ሂድና ቼክ አድርጋት ቅድም ተበሳጭታ ነበር" ብሎ ይልከዋል፣ እሱም ሄዶ ሲመለከት ከ8ኛ ፎቅ ራሷን ወደ 3ኛ ፎቅ ወርውራ ህይወቷ እንዳለፈ ታውቋል ሲል ፖሊስ ተናግሯል።

• @ThinkAbyssinia •
8.1K viewsedited  13:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-16 16:27:19
#Breaking

የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሜር ፑቲን ስዊድን እና ፊንላንድ ኔቶን መቀላቀላቸው ሩስያ ላይ ስጋት እንደማይፈጥር ተናገሩ

የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሜር ፑቲን ስዊድን እና ፊንላንድ ኔቶን መቀላቀላቸው እኛ ላይ ስጋት አይፈጥርም ነገር ግን ምላሽ ሊያሰጥ ይችላል ሲሉ አስጠንቅቀዋል።

በተያያዘ የሩሲያ መከላከያ ሚኒስቴር በማሪፑል በሚገኘው አዞቭታል ፋብሪካ ወስጥ ከመሸገው የዩክሬን ጦር ጋር ስምምነት ላይ መድረሱን ተናግሯል፡ የተጎዱት በዶኔትስክ ህዝባዊ ሪፐብሊክ ኖቮአዞቭስክ ወደሚገኝ ሆስፒታል ይወሰዳሉ ማለቱን ስፑቶኒክ ዘግቧል።


• @ThinkAbyssinia •
8.4K views13:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-16 15:50:56
በአሜሪካ ቡፋሎ መገበያያ ስፍራ ጥቃት ያደረሰው ግለሰብ የቀረፀው ቪዲዮ

በኒው ዮርክ ግዛት ቡፋሎ መገበያያ ስፍራ የነጮችን የበላይነት የሚደግፈው ፔይተን ጄንድሮን የተባለ ግለሰብ ጥቁሮች የሚበረክቱበት መገበያያ ሥፍራ ገብቶ ዘርን መሰረት ያደረገ ጥቃት መፈፀሙ ትናንት መዘገባች ይታወሳል።

በጥቃቱም 10 ሰዎች የተገደሉ ሲሆን በጥይት ከተመቱ 13 ግለሰቦች መካከል አስራ አንዱ ጥቁሮች ናቸው። የ18 ዓመቱ ፔይተን ጌንድሮን 320 ኪሎ ሜትር ተጉዞ መጥቶ ጥቃት የመፈፀሙ ምክንያትም ጥቁሮች በብዛት የሚገኙበት ስፍራ በመሆኑ ነው ተብሏል።

ግለሰቡ ፋሺስትና በነጭ የላይነት አማኝ መሆኑን የሚጠቁም 180 ገፅ ያለው "ማኒፌስቶ" እንዳለው ተሰምቷል። ይህም ማኒፌስቶ በዘረኛና ፀረ-ጥቁሮች ቃላት የታጨቀ ሲሆን ከአሜሪካ ምድር ጥቁሮችና ስደተኞችን ማጥፋት ላይ የተመሠረተ ነው።

ግለሰቡ ባለፈው ሰኔ አንድ ትምህርት ቤት ውስጥ ጥቃት እፈፅማለሁ ሲል ዛቻ መሰንዘሩን አንድ ፖሊስ ለአሶሺዬትድ ፕሬስ ተናግረዋል። ከዚህ ዛቻ በኋላ የአእምሮ ጤናው ምርመራ እንዲደረግለት መደረጉ ተሰምቷል።


• @ThinkAbyssinia •
8.7K viewsedited  12:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-16 13:44:28 የነዳጅ ዋጋ ንረቱ ያልተጠበቀ ማህበራዊ ቀውስ ሊያስከትል እንደሚችል ምሁራን ገለፁ

ታህሳስ 20 ቀን 2014 ዓ.ም በተካሄደው ሶስተኛው የሚኒስትሮች ምክር ቤት ስብሰባ የፀደቀውና የነዳጅ ድጎማን በሂደት የሚቀንስና የሚያስቀር ውሳኔን ተከትሎ፣ በነዳጅ ዋጋ ላይ እየተደረገ ያለው ጭማሪ ያልተጠበቀ ማህበራዊ ቀውስ ሊያስከትል እንደሚችል የምጣኔ ሃብት ምሁራን ተናገሩ፡፡

የነዳጅ ድጎማው ሲነሳ የአንድ ሊትር ቤንዚን ዋጋ 66 ብር ከ78 ሳንቲም፤ የአንድ ሊትር ናፍጣ ዋጋ 73 ብር ይደርሳል ተብሏል። ተጨማሪውን ያንብቡ https://telegra.ph/ቤቤንዚን-05-16
9.8K views10:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-16 12:20:39
በአባቷ የቀብር ስነስርዓት ላይ ለጓደኛዉ የታገቢኛለሽ ወይ? ጥያቄ ያቀረበዉ ግለሰብ አነጋጋሪ ሆኗል

የጉድ ሀገር እንዲሉ በአባቷ ቀብር ላይ ለጓደኛዉ ቀለበት ያሰረዉ ደቡብአፍሪካዊ ከሀገሩ እንዲሁም ከሌሎች የዓለማችን ክፍል ነዋሪዎች ዘንድ ከባድ ትችትን እያስተናገደ ይገኛል፡፡

በአባቷ የቀብር ስነስርዓት ላይ ተንበርክኮ ታገቢኛለሽ ብሎ ሲጠይቃት የሚያሳየዉን አስደንጋጭ ቪድዮ የቀብር ስነስርዓቱ ላይ የተገኘች አንዲት ሴት ቀርጻ ወዲያዉ በቲክቶክ የማህበራዊ መገናኛ ላይ ከለቀቀች በኋላ፤ እጅግ በርካታ ሰዎች እንደተቀባበሉት እና ብዙ ተጠቃሚዎችም ትችቶችን እንደሰነዘሩበት ኦዲቲ ሴንትራል ነዉ የዘገበዉ፡፡

ቪድዮዉ ላይ የሚታየዉ የአባቷ አስከሬን ሳጥን ፊት ቁጭ ብላ በማልቀስ ላይ የምትገኘዉ ጓደኛዉን ተንበርክኮ የታገቢኛለሽ ጥያቄ ሲያቀርብ ነዉ። ማይክራፎን በመጠቀምም ንግግር ያደርግ እና የሌሎች ሹክሹክታ እና ተቃዉሞ አንዳች ሳያግደዉ ቀለበት አዉጥቶ በጣቷ ላይ ሲያጠልቅ ያሳያል፡፡

ጓደኛዉ በፍጹም ድንጋጤ ዉስጥ ሆና የምትታይ ሲሆን ምንም ዓይነት ምላሽ ባለመስጠቷም የጋብቻ ጥያቄዉን ትቀበል አትቀበል ምንም ግልጽ የሆነ ነገር የለም፡፡ በቦታዉ እየሆነ ያለዉን ነገር በስርዓቱ ለማጣጣም በትክክለኛዉ የስሜት ሁኔታ ላይ እንዳልነበረችም በግልጽ ይታይ ነበር፡፡

oddity central

• @ThinkAbyssinia •
9.6K views09:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-16 10:45:50 #ቲንክአቢሲኒያ_የቡናቁርስ_መረጃዎች

1፤የሰብዓዊ እርዳታ የጫኑ ተሽከርካሪዎች ወደ መቀሌ በመግባት ላይ መሆናቸውን ተመድ ገለፀ።

የዓለም ምግብ ፕሮግራም በኢትዮጵያ በማህበራዊ ትስስር ገጹ እንዳስታወቀው በትግራይ እና አፋር ክልሎች ችግር ውስጥ ለሚገኙ ዜጎች የሚሰራጨው የሰብዓዊ እርዳታ ተጠናክሮ ቀጥሏል፡፡ በዚህ መሰረትም በትናንትናው ዕለት የሰብዓዊ እርዳታ የያዙ ተጨማሪ 85 የጭነት ተሽከርካሪዎች መቀሌ መድረሳቸውን ነው የገለጸው፡፡ ከዚህ ባለፈም የሰብዓዊ እርዳታ የጫኑ ተጨማሪ 130 ተሽከርካሪዎች ወደ ትግራይ ክልል እያቀኑ መሆኑን አስታውቋል፡፡ ይህም በተያዘነው የፈረንጆቹ ዓመት ወደ መቀሌ ከተጓጓዘው የሰብዓዊ እርዳታ በመጠን ትልቁ መሆኑ ተመላክቷል፡፡ በተመሳሳይ በሰሜን አፋር አካባቢዎች ችግር ውስጥ ለሚገኙ ዜጎች በሚቀጥሉት ቀናት በዓለም የምግብ ፕሮግም የተዘጋጀው የሰብዓዊ እርዳታ እንደሚሰራጭ ተጠቁሟል፡፡

2፤ሱማሌ እና አፋር ክልሎች ከሚወዛገቡባቸው አዋሳኝ ቀበሌዎች የሁለቱ ክልሎች ልዩ ኃይሎች እና ሚሊሻዎች እንዲወጡ ስምምነት ላይ ደረሱ።

ሱማሌ እና አፋር ክልሎች በሚወዛገቡባቸው አዋሳኝ ቀበሌዎች ላይ በመካከላቸው የሚፈጠሩ ተደጋጋሚ ግጭቶችን በዘላቂነት ለመፍታት እንደተስማሙ ዶይቸቨለ ዘግቧል። የሁለቱ ክልሎች ልዩ ኃይሎች እና ሚሊሻዎች ከአወዛጋቢ አካባቢዎች እንዲወጡ እና የፌደራል ጸጥታ ኃይሎች ለጊዜው እንዲሰማሩባቸው ስምምነት ላይ እንደተደረሰ የሱማሌ ክልል ም/ርዕሰ መስተዳድር ተናግረዋል። ክልሎቹ እዚህ ስምምነት ላይ የደረሱት፣ ሰሞኑን በጅግጅጋ ከተማ ባካሄዱት እና የሰላም ሚንስትር ብናልፍ አንዷለም ጭምር በተገኙበት ውይይት ላይ ነው።

3፤በደቡብ ወሎ ዞን በደረሰ የትራፊክ አደጋ የ6 ሰዎች ህይወት አለፈ።

አደጋው የደረሰው ከመካነ-ሠላም ወደ መርጦለማሪያም 26 ሰዎችን አሳፍሮ ሲጓዝ የነበረው አነስተኛ የህዝብ ማመላለሻ መኪና በመገልበጡ መሆኑን የቦረና ወረዳ ፖሊስ ጽህፈት ቤት አስታውቋል፡፡ በዚህም አሽከርካሪውን ጨምሮ የ6 ሠዎች ህይወት ሲያልፍ 9 ተሳፋሪዎች ላይ ከባድ እንዲሁም 11 ተሳፋሪዎች ላይ ቀላል የአካል ጉዳት መድረሱ ታውቋል፡፡ የወረዳው ፖሊስ ጽህፈት ቤት ንዑስ ክፍል ቁጥጥርና ክትትል የስራ ሂደት ሀላፊ ሳጅን ይርጋ ጀማል እንደገለፁት÷ ተሸከርካሪው ከአቅም በላይ መጫኑና 75 ሜትር የሚሆን ገደል ውስጥ መግባቱን መግለፃቸውን ከቦረና ወረዳ የመንግስት ኮሙንኬሽን ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

4፤በኮሮና ቫይረስ የሞቱ ሰሜን ኮሪያዊያን ቁጥር 15 ደረሰ።

ከዓለም ተገልላ በቆየችው ሰሜን ኮሪያ ኮሮና ቫይረስ እንደ አዲስ በመስፋፋት ላይ ይገኛል። ከሶስት ዓመት በፊት በቻይናዋ ውሃን ከተማ ተከስቶ ዓለምን ያዳረሰው ኮሮና ቫይረስ አሁን ላይ ስርጭቱ እና የጉዳት መጠኑ እየቀነሰ ይገኛል። ይሁንና ባለ ኑክሌር አገሯ ሰሜን ኮሪያ እንደ አዲስ በዚህ ቫይረስ መፈተን የጀመረች ሲሆን በዚሁ ገዳይ ቫይረስ ምክንያት የሞቱ ዜጎች ቁጥር 15 ደርሷል። የቫይረሱን ስርጭት ለመግታት ስትልም ከ1 ነጥብ 5 ሚሊዮን በላይ ዜጎችን በዘመቻ መልክ አሰማርታለች። የእነዚህ ዜጎች ዋነኛ ስራ ከፍተኛ ሙቀት ያላቸውን ሰዎች ወደ ለይቶ ማቆያ እንዲገቡ ማድረግ፣ ስለ በቫይረሱ ሁኔታ ዜጎችን ማስተማር እና ሌሎች የጤና ስራዎችን መስራት ይሆናልም ተብሏል።

5፤ዛሬ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አንድ የአሜሪካን ዶላር በ51 ብር ከ4738 ሳንቲም እየተገዛ ይገኛል።

እንዲሁም መሸጫ ዋጋው 52 ብር ከ5033 ሳንቲም መሆኑን ከድረገጹ ተመልክተናል። የአንድ የእንግሊዝ ፓውንድ መግዣ ዋጋው 59 ብር ከ9328 ሳንቲም እንዲሁም መሸጫው 61 ብር ከ1315 ሳንቲም ሆኗል። በተመሳሳይ አንድ ዩሮ በ53 ብር ከ4607 ሳንቲም እየገዛ በ54 ብር ከ5299 ሳንቲም እየተሸጠ ሲሆን፣ አንድ የቻይና ዩዋን ደግሞ በ6 ብር ከ8581 ሳንቲም ተገዝቶ በ6 ብር ከ9953 ሳንቲም እየተሸጠ እንደሚገኝ ቲንክአቢሲኒያ ተመልክቷል።

6፤የሴካፋ ውድድር የቀን ማሻሻያ ተደረገበት።

በዚህ ሳምንት መጨረሻ እንዲደረግ አስቀድሞ ቀን የተቆረጠለት የሴካፋ ሴቶች ሻምፒዮሺፕ ግንቦት 24 እንደሚጀምር ይፋ ተደርጓል ። ሉሱዎቹ በምድብ ሁለት መደልደላቸው የሚታወስ ሲሆን የምድባቸውን የመጀመሪያ ጨዋታ ግንቦት 25 ከ ዛንዚባር አቻቸው ጋር የሚያካሂዱ ይሆናል ። ውድድሩ ግንቦት 24 ጀምሮ ከአስር ቀናት ቆይታ በኋላ ሰኔ 4 ፍፃሜውን እንደሚያገኝ የወጣው መርሐ ግብር ያመላክታል ። የዘንድሮ የውድድር ዓመት የሴካፋ ሴቶች ሻምፒዮንሺፕ ሁሉም ጨዋታዎች በ ዩጋንዳ ፉፋ ቴክኒካል ሴንተር ንጄሩ የሚካሄድ ይሆናል ።


• @ThinkAbyssinia •
9.1K views07:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-16 10:11:57
Update!

ከፊል የጨረቃ ግርዶሽ ዛሬ ንጋት መታየቱን የኢትዮጵያ እስፔስ ሳይንስና ጂኦ እስፓሻል ኢንስቲትዩት አስታወቀ

ሠመራ ዩኒቨርሲቲ ከኢትዮጵያ እስፔስ ሳይንስና ጂኦ ስፓሻል ኢንስቲዩት እንዲሁም እስፔስ ሳይንስ ሶሳይቲ ጋር በመተባበር የጨረቃ ግርዶሽ ትእይንት ለዩኒቨርሲቲዉ ማህበረሰብና ለሠመራና አካባቢ ህብረተሰብ በሠመራ ዩኒቨርስቲ ቅጥር ግቢ ተከናውኗል።

የኢትዮጵያ እስፔስ ሳይንስና ጂኦ እስፓሻል ኢንስቲትዩት የእስፔስ ሳይንስ ተመራማሪ ዶክተር ኤፍሬም በሺር ለኢዜአ እንደገለጹት ክስተቱ መሬት በጸሃይና ጨረቃ መካከል ስትሆን የሚከሰት ነው።

ይህም በተለያዩ ደቡብ አሜሪካና አውሮፓ ሃገራት እንዲሁም ኢትዮጵያን ጨምሮ በተለያዩ የአለማችን ክፍሎች የተከሰተ መሆኑን ገልጸዋል። በሀገራችንም በተለያዩ አካባቢዎች በከፊል የጨረቃ ግርዶሽ ከንጋቱ 11 ሰአት ጀምሮ ታይቷል ብለዋል።

ኢዜአ

• @ThinkAbyssinia •
8.6K views07:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-16 09:26:05 #Somalia

የጠ/ሚ ዐብይ አሕመድ መልዕክት!

"ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ ሞሀሙድ በድጋሚ የሶማሊያ ፌደራላዊ ሪፐብሊክ ፕሬዝዳንት ሆነው በመመረጥዎ እንኳን ደስ ያለዎት ለማለት እወዳለሁ። የጋራ በሆኑ የሁለትዮሽ እና ቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ ተቀራርበን እንደምንሠራ እምነቴ ነው።"
8.7K views06:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-16 09:19:09
#ቲንክአቢሲኒያ_እለታዊ_የአየር_ትንበያ_መረጃ

ለውሎዎ ጠቃሚ የሆኑ እለታዊ የአየር ትንበያ መረጃዎችን እናድርስዎ


ዛሬ በአንዳንድ የሀገራችን ከተሞች ያለውን ያየር ሁኔታ ስንመለከት መዲናችን አዲስ አበባ ዝቅተኛው 12 ከፍተኛው 31 ድግሪ ሲልሽየስ ፀሀያማ ሆና ትውላለች።

ባህርዳር ዝቅተኛው 12 ከፍተኛው 34 ፀሀያማ ሀዋሳ ዝቅተኛው 12 ከፍተኛው 33 በአብዛኛው ፀሀያማ እንዲሁም መቀሌ ዝቅተኛው 15 ከፍተኛው 30 ፀሀያማ ሆነው እንደሚውሉ ቲንክአቢሲንያ ከቤሄራዊ ሜትሮዎሎጂ ኤጀንሲ ድረገፅ ተመልክቷል።


• @ThinkAbyssinia •
8.3K views06:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ