Get Mystery Box with random crypto!

Think Abyssinia

የቴሌግራም ቻናል አርማ thinkabyssinia — Think Abyssinia T
የቴሌግራም ቻናል አርማ thinkabyssinia — Think Abyssinia
የሰርጥ አድራሻ: @thinkabyssinia
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 157
የሰርጥ መግለጫ

➠ ፈጣን እና ተዐማኒ መረጃ፣
➠ የስፓርት እና መዝናኛ ዘገባዎች፣
➠ የምሁራን እይታዎችና መጽሐፈቶች፣
➠ የአለም ሙሉ መረጃና የታሪክ መዛግብቶች ።
ለማንኛውም መረጃ ➥ @Contact_Thinkabyssinia

🎬 "ተመራጭ የዜና ምንጭ"

Ratings & Reviews

3.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 90

2022-05-14 10:52:53
#india

በህንድ በደረሰ ከባድ የእሳት አደጋ ቢያንስ 27 ሰዎች መሞታቸው ተነገረ

በህንድ ኒውደልሂ በደረሰ ከባድ የእሳት አደጋ ቢያንስ 27 ሰዎች ሲሞቱ በደርዘን የሚቆጠሩ ቆስለዋል። እሳቱ በትላንት እለት ከሰአት በኋላ በምእራብ ደልሂ ባለ አራት ፎቅ የንግድ ህንፃ ላይ ነው የተነሳው። አሁንም ተጎጂዎችን የማዳን እና የማፈላለግ ስራዎች በመካሄድ ላይ ናቸው።


TRT World

• @ThinkAbyssinia •
3.7K views07:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-14 10:05:52 #ቲንክአቢሲኒያ_የቡናቁርስ_መረጃዎች

1፤በጅግጅጋ ከተማ ሲካሄድ የቆየው የሶማሌ እና የአፋር ክልሎች የጋራ ውይይት ተጠናቀቀ ።

በመድረኩ የሰላም ሚኒስትሩ ብናልፍ አንዱአለም ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ከተከሰቱ ግጭቶች መካከል በአፋርና ሶማሌ ሕዝቦች መካከል የተስተዋለው ግጭት ይጠቀሳል ብለዋል። የተከሰተው ግጭት የሁለቱ ክልል ነዋሪዎችን ያፈናቀለና የአካባቢውን ሰላም ያደፈረሰ እንደነበረ ጠቅሰው ፣ሰው ሰራሽ ግጭቶችን ለመፍታት ተቀራርቦ መስራት አስፈላጊ ነው ብለዋል ሚኒስትሩ። በጅግጅጋ ከተማ ሲካሄድ በቆየው ውይይት በሶማሌና ወንድም ከሆነው የአፋር ሕዝብ መካከል የነበረውን ግጭት በውይይት ለመፍታት ዝግጁ መኾናቸውን የሁለቱ ክልሎች ርእሰ መስተዳድሮች አስታውቀዋል።
የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ሙስጠፌ ሙሁመድ በውይይት የተደረሠባቸውን ስምምነቶች ተፈፃሚ እናደርጋለን ብለዋል። የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ውይይቱ የህብረተሰቡን ሰላምና ልማት
ለማረጋገጥ የአመራር ቁርጠኝነት የታየበት ነው ብለዋል።

2፤ የኢትዮጵያ መንግስት ለችግሮች እልባት ለመስጠት እየተጓዘበት ያለው መንገድ አበረታች መሆኑን የአውሮፓ ህብረት ገለፀ።

ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን የአውሮፓ ህብረት የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛን ዶክተር አኔት ዌበርን በፅህፈት ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል። አቶ ደመቀ በኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን እና በሰሜኑ ግጭት እና በድርቅ ምክንያት ጉዳት ለደረሰባቸው ዜጎች እየተደረገ ስላለው ሰብአዊ እርዳታ አቅርቦት ወቅታዊ ሁኔታ ዙሪያ እና በቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ ለልዩ መልዕክተኛዋ ገለጻ አድርገዋል ። የአውሮፓ ህብረት የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ ዶ/ር አኔት ዌበር በበኩላቸው መንግሥት ያልተገደበ ሰብአዊ እርዳታ እንዲዳረስ ያሳለፈው የተኩስ አቁም ውሳኔ እና ለችግሮች እልባት ለመስጠት እየተጓዘበት ያለው መንገድ አበረታች ነው ብለዋል ።

3፤ከአልሸባብ የሽብር ተልዕኮ የተሰጣቸው ስድስት ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ዋሉ።

በሶማሊያ በሚንቀሳቀሰው አልሸባብ የሽብር ቡድን ሰልጥነው በኢትዮጵያ የጥፋት ተልዕኮ ተሰጥቷቸው ወደ ስምሪት ሊገቡ የነበሩ ስድስት ተጠርጣሪ ግለሰቦች በአዲስ አበባ ከተማ እና በኦሮሚያ ክልል በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት አስታውቋል። ተጠርጣሪዎቹ በኢትዮጵያ በህቡዕ ድጋፍ በሚያደርጉ አካላት አማካኝነት ከተለያዩ የሀገሪቱ ክፍል ተሰባስበው ከየካቲት 2 ቀን 2014 ዓ.ም ጀምሮ በተለያዩ ወቅቶች ወደ ሶማሊያ እንዲገቡ የተደረገ ቢሆንም የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት በአልሸባብ ቡድን ላይ በሚያደርገው ክትትልና የመረጃ ስምሪት መነሻነት የጥፋት እቅዱን ከውጥኑ ጀምሮ ሲከታተል ቆይቶ ከጸጥታ አካላት ጋር በተከናወነ ኦፕሬሽን ተጠርጣሪዎቹ በአዲስ አበባ ከተማ እና በኦሮሚያ ክልል በቁጥጥር ስር እንዲውሉ መደረጉን ገልጿል።

4፤ቱርክ ፤ የፊንላንድ እና ስውዲን ኔቶን መቀላቀል እንደማትደግፍ አስታወቀች።

የቱርክ ፕሬዜዳንት ሬሲፕ ጣይብ ኤርዶጋን ፤ ሀገራቸው ስዊድን እና ፊንላንድን ኔቶን በአባልነት የመቀላቀል እቅድ እንደማትደግፍ ገልፀዋል። ምንም እንኳን ፕሬዝዳንቱ በግልፅ ባያብራሩም የኖርዲክ ሀገራት የብዙ አሸባሪ ድርጅቶች መገኛ ናቸው ሲሉ ተናግረዋል። አንካራ ውስጥ ለጋዜጠኞች መግለጫ የሰጡት ኤርዶጋን ፥ " ስዊድን እና ፊንላንድን በሚመለከት ያለውን ሂደት እየተከታተልን ነው ፤ ነገር ግን በጉዳዩ ላይ አዎንታዊ አመለካከት የለንም " ብለዋል። ከዚህ ቀደም ኔቶ ግሪክን በአባልነት መቀበሉ ስህተት ነበር ሲሉም ተደምጠዋል። " እንደ ቱርክ ተመሳሳይ ስህተቶችን መድገም አንፈልግም " ሲሉ አክለዋል።

5፤ሲዳማ ቡና ጊዜያዊ ዋና አሰልጣኙን አሳውቋል፡፡

ትላንት አመሻሹን ከአሰልጣኝ ገብረመድህን ኃይሌ ጋር የተለያየው ሲዳማ ቡና ጊዜያዊ ዋና አሰልጣኙን አሳውቋል፡፡ በቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ የ23ኛ ሳምንት ጨዋታው በመከላከያ 5-3 የተረታው ሲዳማ ቡና ዋና አሰልጣኙ ገብረመድህን ኃይሌ ‘ክለቡ በጠበቀው የውጤታማነት መንገድ መሰረት እየተጓዙ አይደለም’ በሚል ከኃላፊነት ማንሳቱን አሳውቋል። የአሰልጣኙ ረዳት በመሆን የቆየው
ወንድማገኝ ተሾመ እስከ ውድድር ዓመቱ መጨረሻ ድረስ ክለቡን በዋና አሰልጣኝነት (ለሰባት ጨዋታዎች) እንዲመራ ተመርጧል፡፡ የቀድሞው የሲዳማ ቡና እና ሀዋሳ ከተማ የግራ መስመር ተከላካይ ወንድማገኝ እግርኳስን ካቆመ በኋላ የሲዳማ ቡና ከ20 ዓመት በታች ቡድን አሰልጣኝ በመሆን ያገለገለ ሲሆን ዘንድሮ ደግሞ የዋናው ቡድን ረዳት ሆኖ ያለፉትን ስምንት ወራት ሲሰራ ቆይቷል፡፡


• @ThinkAbyssinia •
4.2K views07:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-14 09:13:35
የአማራ ክልል የጸጥታ ምክር ቤት ህገወጥነትን ለመቆጣጠር የጸጥታ ኃይሎች እርምጃ እንዲወስዱ ውሳኔ አሳለፈ

የአማራ ክልል መንግስት የጸጥታ ምክር ቤት በክልሉ አሁን ላይ እየተስፋፋ መጥቷል ያለውን “ህገወጥነትን ለመቆጣጠር እና ህግን ለማስከበር” በየደረጃው የጸጥታ ኃይሎች እንዲቋቋሙና እርምጃ እንዲወስዱ ውሳኔ አሳልፏል።

ምክር ቤቱ ትላንት አርብ ግንቦት 5 ባደረገው ስብስባ “ሕገ-ወጦችን እና ሥርዓት አልበኞች” ያላቸውን አካላት መቆጣጠር እና የክልሉን ሰላምና ደህንነት ማስጠበቅ “ግንባር ቀደም የትኩረት አቅጣጫ እንዲሆን” ከውሳኔ
ላይ መድረሱን አስታውቋል።

ምክር ቤቱ ከስብሰባው መገባደድ በኋላ ባወጣው መግለጫ፤ “የወያኔ ወራሪ ቡድን” ሲል የጠራው ኃይል “በአማራ ክልል ላይ ዳግም ጦርነት አውጇል” ሲል ከስሷል። ይህን ጦርነት “ለመመከት እና ለመቀልበስ” እንዲቻልም፤ በክልሉ “በየደረጃው ያለው የጸጥታ መዋቅር ዝግጁ መሆን እንዳለበት” ምክር ቤቱ “አቅጣጫ
ማስቀመጡን” አመልክቷል።

በመግለጫው ላይ ሰፊውን ቦታ ሰጥቶ የዳሰሰው “ህገ ወጥነት እና ሥርዓት አልበኝነት” ሲሆን የክልሉን ሰላም ደህንነት ስጋት ውስጥ እየጣለ ይገኛል” ብሏል።


• @ThinkAbyssinia •
4.8K viewsedited  06:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-14 08:31:33
መንግስት ለአምራች ኢንደስትሪው የመሬት ፖሊሲውን ቀየረ

በዚህም መሰረት ለአዳዲስ አምራች ኢንደስትሪዎች የተመቻቸ መሰረተ ልማት ባላቸው የኢንደስትሪ ፓርኮች ውስጥ ቦታ ይመቻቻል ተብሏል፡፡ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ እንዳሉት አሁን ላይ ለሚታየው ምቹ የቢሮክራሲ ጥያቄ እና ብልሹ አሰራር የመሬት ጉዳይ ዋነኛው ነው፡፡

በመሆኑም ይህን ችግር ለመቅረፍ ከዚህ በኋላ በኢንደስትሪው ዘርፍ ለመሰማራት ለሚፈልግ ኢንቨስተር በከፍተኛ ሃብት በተገነቡ ግን በበቂ ባልተያዙ የኢንደስትሪ ፓርኮች ቦታ ይመቻቻል ብለዋል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ አክለውም ከዚህ በኋላ በአዲስ አበባም ሆነ በክልሎች ለኢንደስትሪው ዘርፍ መሬት አይቀርብም፤ ለብልሹ አሰራር በር አይከፈትም ብለዋል፡፡ባለፉት ጥቂት አመታት ብቻ 13 የኢንደስትሪ ፓርኮች እና ሶስት የግብርና ማቀነባበሪያዎች የተገነቡ ቢሆንም በባለሃብቶች ሙሉ ለሙሉ አልተያዙም፡፡


Capital

• @ThinkAbyssinia •
1.5K views05:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-14 08:07:28
#ቲንክአቢሲኒያ_እለታዊ_የአየር_ትንበያ_መረጃ

ለውሎዎ ጠቃሚ የሆኑ እለታዊ የአየር ትንበያ መረጃዎችን እናድርስዎ


ዛሬ በአንዳንድ የሀገራችን ከተሞች ያለውን ያየር ሁኔታ ስንመለከት መዲናችን አዲስ አበባ ዝቅተኛው 14 ከፍተኛው 28 ድግሪ ሲልሽየስ ፀሀያማ ሆና ትውላለች።

ባህርዳር ዝቅተኛው 14 ከፍተኛው 32 ፀሀያማ ሀዋሳ ዝቅተኛው 14 ከፍተኛው 31 ከፊል ደመናማ እንዲሁም መቀሌ ዝቅተኛው 17 ከፍተኛው 28 ፀሀያማ ሆነው እንደሚውሉ ቲንክአቢሲንያ ከቤሄራዊ ሜትሮዎሎጂ ኤጀንሲ ድረገፅ ተመልክቷል።


• @ThinkAbyssinia •
2.0K views05:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-13 21:27:28
በዳኝነት ስርዓቱ ላይ የሚታዩ የሙስና ተግባራትን ለመከላከል የሚያስችል ስትራቴጂ ይፋ ሆነ

የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በዳኝነት ስርዓቱ ላይ የሚታዩ የሙስና ተግባራትን ለመከላከል የሚያስችል ስትራቴጂ ይፋ አደረገ።

በስትራቴጂው ፋይዳ እና በቀጣይ አተገባበሩ ዙሪያ በማተኮር ከዳኞችና ከሌሎች ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ውይይት ተካሂዷል። በመድረኩ ላይ የተገኙት የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት መዓዛ አሸናፊ በፍትህ አሰጣጥ ሂደት የትውውቅ አሰራር፣ ጉቦና የመሳሰሉት ብልሹ አሰራሮች ፈተና እየሆኑ መምጣታቸውን ገልጸዋል።

የዳኞች አገልግሎት አሰጣጥ ከሙስና ተግባር የፀዳ መሆን እንዳለበት ጠቅሰው አንዳንድ ዳኞች፣ የጉባኤ ተሿሚዎችና የፍርድ ቤት ሰራተኞች በሙስና ፍትሕ እንዲዛባ እየሰሩ መሆኑን ተናግረዋል።

• @ThinkAbyssinia •
1.8K views18:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-13 18:59:14
የኢትዮጵያ እና የዑጋንዳ የመከላከያ ኃላፊዎች ተወያዩ

ኡጋንዳ የጸረ-ኢትዮጽያ ኃይሎች መናኸሪያ አትሆንም ሲሉ የአገሪቱ መከላከያ ሚንስትር ለኢትዮጵያው ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ እንዳረጋገጡቸው ውጭ ጉዳይ ሚንስቴር በማኅበራዊ ትስስር ገጹ ገልጧል።

የኡጋንዳው ሚንስትር የትግራዩ ሕወሃት አባላት በአሜሪካ፣ ግብጽ እና ደቡብ ሱዳን ድጋፍ በኡጋንዳ ወታደራዊ ሥልጠና እያገኙ ነው ተብሎ ባንዳንድ የማኅበራዊ መገናኛ ዘዴዎች የተሰራጨው መረጃ ከእውነት የራቀ ነው በማለት አስተባብለዋል።


• @ThinkAbyssinia •
5.0K views15:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-13 18:56:45
#Update

ትላንት ምሽት 3: 00 አካባቢ በአዲስ አበባ ፊሊፖስ ኢንዱስትሪ መንደር በድንገት የተነሳው የሳት ቃጠሎ በንብረት ላይ ከፍተኛ ጉዳት ማድረሱ የተነገረ ሲሆን በሰው ሕይወት ላይ ያደረሰው ጉዳት እንደሌለ ተገልጧል።

በእሳት እና አደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን የሕዝብ ግንኙነት አቶ ንጋቱ ማሞ ለዶቼ ቨይሌ (DW) እንደተናገሩት የድረሱልን ስልክ ጥሪ እንደመጣ ወደ የእሳት አደጋ ሠራተኞችን መላካቸውን ተናግረዋል። ሆኖም እሳቱን መቆጣጠር ባለመቻላችን ከሌሎች ቅርንጫፍ ጣቢያዎች ተጨማሪ 15 የአደጋ ግዜ ተሽከርካሪ እና 78 ያአደጋ ግዜ ባለሞያዎችን ኃይል በማስመጣት እሳቱ ከዚህ የከፋ ጉዳት እንዳያደርስ ለመቆጣጣር ችለናል» ሲሉም አክለዋል።

«ሺዶቹ የተሰሩበት ቁሳቁስ ቀላል እና በቀላሉ በሳት ተቀጣጣይ የሆኑ እና ቆርዎሮ በቆርቆሮ
የተገነባ በመሆኑ ከዚህ በተጨማሪ ቅጥባልያዘ እና በተዝረከረከ መልኩ የተዘረጋው
ኤሌክትሪክ መስመር በአጠቃላይ ውስጥ ያለው አስራር በጥናት እና ባግባቡ አለመሆን
ችግሩን የከፋ እንዲሆን አድርጎታል» ብለዋል። «ባለሞያዎቻችን አስቀድመው በእሳት
የተያያዙት ሼዶች ብቻ ላይ ጉዳቱ እንዲያበቃ ለማድረግ ችለናል» ሲሉ አቶ ንጋቱ ማሞ የኮሚሽኑ የህዝብ ግንኙነት ባለሞያ ለዶይቸ ቨሌ ተናግረዋል።

እሳት አደጋ የደረሰበት አካባቢ ነዋሪዎች ግን ይህ እንደሚፈጠር ዐውቀን መጮህ የጀመርነው ዛሬ አይደለም ገና በፊት ነው። አካባቢው እንኩዋን የእሳት አደጋን የሚያክል ትልቅ መኪና ይቅር እና ትንሽ የቤት መኪናም አያሳልፍም የአካባቢው ባለስልጣነት የነዋሪውን ስጋት እና ጭንቀት ችላ በማለታቸው የተፍጠረ ጥፋት ነው ሲሉም ቅሬታቸውን አክለዋል። መንገዱ በአራቱም አቅጣጫ ተዘግቶ ነው ያለው» ሲሉም ምሬታቸውን አሰምተዋል።


ዶይቸ ቬለ

• @ThinkAbyssinia •
5.2K views15:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-13 18:05:27 #ቲንክአቢሲኒያ_የመክሰስ_መረጃዎች

1፤ አፈ ጉባኤ አገኘሁ ተሻገር ከአውሮፓ ህብረት የአፍሪካ ቀንድ ልዩ ተወካይ ጋር ተወያዩ።

የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አገኘሁ ተሻገር ከአውሮፓ ህብረት የአፍሪካ ቀንድ ልዩ ተወካይ ዶክተር አኔት ዌበር ጋር መክረዋል፡፡ አፈ ጉባኤው በትዊተር ገጻቸው ባሰፈሩት ጽሁፍ ፥ በወቅታዊ የኢትዮጵያ የፖለቲካ እና የጸጥታ ሁኔታ ላይ ከዶክተር አኔት ዌበር ጋር የተሳካ ውይይት ማድረጋቸውን ገልጸዋል።

2፤1 ሺህ 154 ኢትዮጵያውያን ከሳዑዲ አረቢያ ወደ ሀገራቸው ተመለሱ።

ዛሬ በሶስት ዙር በተከናወነ ዜጎችን ከሳዑዲ አረቢያ የመመለስ ስራ 1 ሺህ 154 ኢትዮጵያውያንን ወደ ሀገራቸው መመለስ መቻሉ ተገለፀ፡፡ ከእነዚህ ውስጥ 157 ሴቶች ሁለት ህጻናትና 995 ወንዶች መሆናቸው ታውቋል፡፡ ለተመላሽ ዜጎችም ተገቢውን ድጋፍ እና እንክብካቤ በማድረግ ወደ ተዘጋጀላቸው የማቆያ ማእከላት እንዲሄዱ መደረጉን ከሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡ እስካሁን ድረስ በተከናወነው ዜጎችን የመመለስ ስራ ከ22 ሺህ 600 በላይ ኢትዮጵያውያንን መመለስ ተችሏል፡፡

3፤ልማት ባንክ ለ34 ሺሕ ሠልጣኞች 20 ቢሊዮን ብር ብድር አዘጋጀ።

የኢትዮጵያ ልማት ባንክ እያሠለጠናቸው ላሉ አነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች 20 ቢሊዮን ብር ብድር ማዘጋጀቱን አስታወቀ። ባንኩ አነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ አንቀሳቃሾች ብድር ወስደው ወደ ሥራ እንዲገቡ ለማድረግ ከግንቦት 1 እስከ 5 ቀን 2014 ዓ.ም. የሚቆይ ሥልጠና በመስጠት ላይ መሆኑን፣ በሥልጠናውም 34,000 ሠልጣኞች እንደሚሳተፉ የልማት ባንክ ፕሬዚዳንት ዮሐንስ አያሌው (ዶ/ር) ገልጸዋል። ከዓለም ባንክ ጋር በመተባበር የተዘጋጀው ሥልጠና በ20 ከተሞችና በ32 ማዕከላት በመላ አገሪቱ ለሦስተኛ ጊዜ የሚሰጥ መሆኑን አክለዋል።

4፤ቻይና የሩሲያ ጦር ላይ የሚደረገውን ምርመራ ተቃወመች።

ቻይና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብአዊ መብቶች ምክር ቤት የሩሲያ ጦር በዩክሬን ንጹሀን ላይ “የጦር ወንጀል” መፈጸም አለመፈጸሙን ለማረጋገጥ የሚያደርገውን ምርመራ በመቃወም ድምጽ ሰጥታለች። ምክርቤቱ የጦር ወንጀሎች ምርመራ እንዲፈቀድ የሚጠይቀውን የውሰኔ ሀሳብ በትናንትናው ዕለት በአብላጫ ድምጽ አጸድቋል፡፡ ቻይና ከዚህ ቀደም የሩሲያ- ዩክሬን ጦርነትን አስመልክቶ በምክርቤቱ በሚሰጡ ውሳኔዎች ላይ ድምጸ ተአቅቦ ስታደርግ እንደቆየች የጠቀሰው ዘገባው፥ በምክርቤቱ የሚደረገው ምርመራ ፖለቲካዊ አጀንዳ ያለው ነው በሚል የቀድሞ አቋሟን ቀይራ ተቃውሞ ማቅረቧ ተሰምቷል፡፡ የጦር ወንጀሎች ምርመራ እንዲፈቀድ የሚጠይቀው ውሳኔ በምክርቤቱ በ33 ድጋፍ፣ በ12 ድምፀ ተአቅቦ እና በ2 ተቃውሞ መጽደቁን አር ቲ ዘግቧል፡፡

5፤የርገን ክሎፕ የአውሮፓ እግር ኳስ ማህበር አሰራርን ተቹ።

የመርሲሳይዱ ክለብ ሊቨርፑል ጀርመናዊው አሰልጣኝ የርገን ክሎፕ የአውሮፓ ኔሽንስ ሊግ ውድድር መቀጠል እንደሌለበት ገልፀዋል ። የርገን ክሎፕ ሲናገሩ " የአውሮፓ ኔሽንስ ሊግ በአለማችን ላይ ከሚገኙ አሳፋሪው ውድድሮች መካከል አንዱ ነው ። የውድድር አመቱ ከተጠናቀቀ በኋላ እስከ 70 ጨዋታዎች ያደረጉ ተጫዋቾችን ከአራት እስከ ሰባት የሚጠጉ ጨዋታዎች እንዲያደርጉ የሚያደርግ ውድድር ነው ። የአውሮፓ እግር ኳስ ማህበር ተጨማሪ ገቢን ለማግኘት ኔሽንስ ሊግን በመሰረዝ የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ የፍፃሜ ጨዋታ ላይ ቢሰራ ምርጫዬ ነው " ሲሉ ተደምጠዋል ።


• @ThinkAbyssinia •
424 views15:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-13 17:57:52
የአርቲ ኒውስ ሠራተኞች በዶኔትስክ ጥቃት ደረሰባቸው

የአርቲ ኒውስ የውትድርና ጋዜጠኛው ቫለንቲን ጎርሼኒን በዶኩቻቭስክ አቅራቢያ በሚገኘው የዩክሬን ጦር በሮኬት ተኩስ ጉዳት ደርሶበታል። በተጨማሪም ሁለት የ አርቲ ባልደረቦች ቆስለዋል ።

ጎርሼኒን ላይ ብዙም ጉዳት አልደረሰም ሆኖም ካሜራማን ቭላድሚር ባታሊን እና ቪክቶር ሚሮሽኒኮቭ በእግራቸው እና በጀርባቸው ላይ በደረሰባቸው አደጋ ሆስፒታል ገብተዋል ።


RT News

• @ThinkAbyssinia •
819 viewsedited  14:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ