Get Mystery Box with random crypto!

Think Abyssinia

የቴሌግራም ቻናል አርማ thinkabyssinia — Think Abyssinia T
የቴሌግራም ቻናል አርማ thinkabyssinia — Think Abyssinia
የሰርጥ አድራሻ: @thinkabyssinia
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 157
የሰርጥ መግለጫ

➠ ፈጣን እና ተዐማኒ መረጃ፣
➠ የስፓርት እና መዝናኛ ዘገባዎች፣
➠ የምሁራን እይታዎችና መጽሐፈቶች፣
➠ የአለም ሙሉ መረጃና የታሪክ መዛግብቶች ።
ለማንኛውም መረጃ ➥ @Contact_Thinkabyssinia

🎬 "ተመራጭ የዜና ምንጭ"

Ratings & Reviews

3.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 93

2022-05-12 19:15:13
በህገ- ወጥ መንገድ 7 ሕፃናትን ሲያዘዋውር የተገኘው ግለሰብ በቁጥጥር ስር ዋለ

በህገ- ወጥ መንገድ ሰባት ሕፃናትን ሲያዘዋውር የተገኘው ግለሰብ በፖሊስ ቁጥጥር ስር መዋሉን የቤንች ሸኮ ዞን ፖሊስ መምሪያ አስታወቀ።

በቤንች ሸኮ ዞን የዘረፋና ወንብድና ልዩ ልዩ ወንጀል ማስተባበሪያ ኃላፊ ም/ኢ/ር ወንዳየሁ ገ/ሚካኤል ተጠርጣሪው ሸኮ ወረዳ ጉፊቃ ቀበሌ ግንቦት አንድ ቀን 2014 ዓ/ም ከጠዋቱ 3:00 በተሽከርካሪ ይዞ በመጓዝ ላይ እንዳለ ከህብረተሰቡ በደረሰ ጥቆማ በፖሊስ ቁጥጥር ስር ሆኖ ምርመራ እየተጣራ እንደሚገኝ ተናግረዋል።

ተጠርጣሪው ግለሰብ ከካፋ ዞን ጨና ወረዳ ባላ ሻሻ ቀበሌ ከአስር ዓመት በታች የሆኑ ሰባት ሕፃናትን ከሚኖሩበት ቤተሰብ ከብቶችን ትጠብቃላችሁ በማለት ለጉልበት ብዝበዛ ወደ ቤንች ሸኮ ዞን ይዞ መጓዙን ገልጸዋል።

• @ThinkAbyssinia •
6.7K views16:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-12 19:01:00
ኦፌኮ በኦሮሚያ ክልል 297 ሰዎች በመንግስት ታጣቂዎች ተገድለዋል አለ

የኦሮሞ ፌደራላዊ ኮንግረስ (ኦፌኮ) በኦሮሚያ ክልል ባለፉት ጥቂት ወራት ብቻ 297 ሰዎች በመንግስት ታጣቂዎች ተገድለዋል ብሏል። ፓርቲው በክልሉ የተለያዩ አካባቢዎች እየተካሄደ ነው ባለው “ደም አፋሳሽ ጦርነት” ምክንያት ከ500 ሺህ ሰዎች በላይ መፈናቀላቸውን አስታውቋል።

ኦፌኮ ይህን ያለው ዛሬ ሐሙስ ግንቦት 6፤ 2014 ወቅታዊ ሃገራዊ ጉዳዮችን በተመለከተ በአዲስ አበባ ሜክሲኮ አደባባይ አካባቢ በሚገኘው ዋና ጽህፈት ቤቱ በሰጠው መግለጫ ነው። ፓርቲው በመግለጫው ቅድሚያ የሰጠው በኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት ይስተዋላሉ ላለቸው “የፖለቲካ ውድቀት፣ የእርስ በእርስ ጦርነት እና የኢኮኖሚ ቀውስ” ክስተቶች ነው።

እነዚህ እርስ በእርስ የተሳሰሩ ክስተቶች “ኢትዮጵያን እያናጉ ያሉ አዙሪቶች ናቸው” ያለው ኦፌኮ፤ ለእነዚህ ችግሮች መፍትሔው በሀገሪቱ ያለውን የእርስ በእርስ “ጦርነት በማስቆም ችግሮችን ወደ ፖለቲካ ድርድር መድረክ ማምጣት ነው” ሲል ከችግሮቹ መውጫ መንገዱን ጠቁሟል። ፓርቲው በኢትዮጵያ ያለው የእርስ በእርስ ጦርነት መቋጫ ካላገኘ፤ “የሀገሪቱ ፖለቲካው እና ኢኮኖሚያዊ ቀውስ የበለጠ እየጠነከረና እየተወሳሰበ መሄዱ አይቀርም” ሲልም አስጠንቅቋል።


ኢትዮጵያን ኢንሳይደር

• @ThinkAbyssinia •
6.3K views16:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-12 18:33:43 #ቲንክአቢሲኒያ_የመክሰስ_መረጃዎች

1፤የዘንድሮው የአዲስ አበባ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት በይፋ ተጀመረ።

የዘንድሮው የአዲስ አበባ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት “በጎነት ለዘላቂ አብሮነት” በሚል መሪ ሐሳብ በይፋ ተጀምሯል። የከተማ አስተዳደሩ በመጪው የክረምት ወራት በሚከናወነው የበጎ ፈቃድ አገልግሎት መርሐ ግብር 570 ሺህ የህብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ እንደሚያደርግ ማቀዱን ገልጿል ፡፡
መግለጫውን የሰጡት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሕብረተሰብ ተሳትፎና የበጎ ፈቃድ ማስተባበሪያ ኮሚሽነር አቶ አስፋው ተክሌ እንደተናገሩት ፥ የበጎ ፈቃድ አገልግሎቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በሰጡት አቅጣጫ መሠረት ሰው ተኮር ተግባራቶችን በልዩ ሁኔታ ለመምራት እንዲያስችል ተደርጎ እቅድ ተዘጋጅቷል ብለዋል፡፡

2፤ ኢትዮጵያና ቻይና በኢንቨስትመንት መስክ መስራት የሚያስችላቸውን ስምምነቶች ተፈራረሙ።

ኢትዮጵያና ቻይና በኢንቨስትመንት መስክ መስራት የሚያስችላቸውን ስድስት የተለያዩ ስምምነቶችን ተፈራርመዋል። ስምምነቶቹ የተደረጉት በቻይና ኩባንያዎችና በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን መካከል ነው። ኢንዱስትሪ፣ ፋርማሲዩቲካል፣ ማኑፋክቸሪንግ፣ ግብርና፣ መሰረተ ልማትና ጤና ስምምነት የተደረገባቸው መስኮች ናቸው። በስምምነት ስነ ስርዓቱ ላይ ላይ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን፣ በኢትዮጵያ የቻይና አምባሳደር ዣኦ ዢዩዋንና ሌሎች ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።

3፤የባለይዞታዎች የይዞታ ይረጋገጥልኝ ማመልከቻ ማቅረቢያ ቀነ ገደብ ነገ እንደሚጠናቀቅ ኤጀንሲው ገለፀ።

የአዲስ አበባ የመሬት ይዞታ፣ ምዝገባና መረጃ ኤጀንሲ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ኢንጅነር ጀማል ሀጅ እንደገለፁት ለይዞታ ማርጋገጫ በተመረጡ 25 ቀጠናዎች እና 112 ሰፈሮች የሚገኙ የመሬት ባለይዞታዎች የይዞታ ይረጋገጥልኝ ማመልከቻ እያቀረቡ ነው፡፡ ኤጅንሲው የይዞታ ይረጋገጥልኝ ማመልከቻ ሀሙስ ሚያዚያ 20 መቀበል ከጀመረበት ጊዜ አንስቶ ባሉት 6 ተከታታይ የስራ ቀናት ከ11 ሺህ 300 በላይ ባለይዞታዎች የይዞታ ይረጋገጥልኝ ማመለከቻዎችን ማቅረባቸውን ገልፀዋል፡፡ የይዞታ ይረጋገጥልኝ ማመልከቻ የመቀበል ሂደቱ እስከ ግንቦት 5 ብቻ የሚቆይ በመሆኑ ተናግረዋል።

4፤የፊንላንድ መሪዎች ሀገራቸው ኔቶን እንድትቀለቀል ወሰኑ።

የፊንላንድ መሪዎች ሀገሪቱ የሰሜን አትላንቲክ ጦር ቃል ኪዳን ድርጅት (ኔቶ) ን እንድትቀላቀል መወሰናቸውን አስታወቁ። ሀገሪቱ የኔቶ አባል እንድትሆን ድጋፍ የሰጡት የፊንላንድ ፕሬዝዳንት ሳውሊ ኒኒስቶ እና ጠቅላይ ሚኒስትር ሳና ማሪን ሲሆኑ በጋራ ባወጡት መግለጫ ፊንላንድ በአስቸኳይ የኔቶ አባል እንድትሆን ማመለከቻ ማስገባት አለባት ብለዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ እና ፕሬዝዳንቱ በጋራ መግለጫቸው የፊንላንድ ኔቶን መቀላቀል የጸጥታ ሁኔታዋን ያጠናክርላታል ብለዋል። የሰሜን አትላንቲክ ጦር ቃል ኪዳን ድርጅት (ኔቶ)28 የአውሮፓ ሀገራት፤ አሜሪካ እና ካናዳን ጨምሮ በድምሩ 30 አባል ሀገራት ያሉት የጋራ የመከላከያ ተቋም ነው።

5፤ወላይታ ድቻ ቅዱስ ጊዮርጊስን ከሷል።

የቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ የ23ኛ ሳምንት የሁለተኛ ቀን የመጀመሪያ ጨዋታ ረፋድ 04፡00 ላይ መሪው ቅዱስ ጊዮርጊስ እና ወላይታ ድቻ ተገናኝተው ያለ ጎል ጨዋታቸውን መፈፀማቸው ይታወሳል፡፡ ከዚህ ጨዋታ ጋር በተያያዘ ከደቂቃዎች በፊት የወላይታ ድቻ ክለብ በቅዱስ ጊዮርጊስ ላይ ከተጫዋች ተገቢነት ጋር በተያያዘ ቅሬታ አለኝ በማለት ለፕሪምየር ሊጉ አወዳዳሪ አካል የቅሬታ ደብዳቤ ማስገባቱን የክለቡ ቡድን መሪ አቶ ዘላለም ለሶከር ኢትዮጵያ አረጋግጠዋል፡፡ ክለቡ “ቅዱስ ጊዮርጊስ በጨዋታው ላይ ሦስት ጊዜ ብቻ አምስት ተጫዋቾችን መቀየር ሲኖርበት ክለቡ ይሄን ህግ በመጣስ በአራት የቅያሬ ጊዜ የለወጠበት ሂደት ከተቀመጠው ደንብ ውጪ በመሆኑ የጨዋታው ውጤት ይገባናል።” በማለት አቤቱታውን ማቅረቡን የቡድን መሪው ጨምረው ገልፀውልናል፡፡


• @ThinkAbyssinia •
6.5K views15:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-12 16:36:52
የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የሐጅ ተጓዦች ምዝገባ መጀመሩን አስታወቀ


የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የሐጅ ምዝገባ መጀመሩን አስታወቀ። በዚህም መሰረት የ2014 ዓ.ም የሐጅ ተጓዦች አጠቃላይ አገልግሎት ዋጋ 183 ሺህ 500 ብር መሆኑን ምክር ቤቱ ያወጣው የዋጋ ዝርዝር ያመለክታል።

ምክር ቤቱ የዋጋ ዝርዝሩን እና ብር የሚገባባቸው የባንክ እና ቁጥሮች ይፋ ያደረገ ሲሆን ሀጃጁ ባንክ ያስገባበትን ደረሰኝ ፎቶ ኮፒ አድርጎ በመያዝ ዋናውን ይዞ መምጣት እንደሚጠበቅበትም ነው ያስታወቀው።


• @ThinkAbyssinia •
7.4K viewsedited  13:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-12 16:36:29
የማላዊ ከፍተኛ ፍርድ ቤት አልቢኖ ያለበትን ግለሰብ የገደሉ ሦስት ሰዎችን እያንዳንዳቸውን በ155 ዓመት እስራት ቀጣ

የ44፣ 45 እና 71 ዓመት የሆናቸው ሦስቱ ግለሰቦች ባለፈው ጥር የ23 ዓመቱን ወጣት መግላቸውን አምነዋል። ከወንጀለኞቹ አንዱ የሟች አጎት ነው ተብሏል።

ባለፉት አስር ዓመታት በማላዊ አልቢኖ ያለባቸው ሰዎች ተዳጋጋሚ ጥቃት እና ግድያ ሲደርስባቸው ቆይቷል። ለዚህ ደግሞ ዋነኛው ምክንያት የሰውነት አካላቸው ጥሩ እድል እና ሃብት ያመጣል በሚል ሃሰተኛ እምነት ነው።

አልቢኖ የቆዳ ቀለም በመንጣቱ ምክንያት የሚከሰት ህመም ሲሆን በዘር የሚተላለፍ ነው። አልቢኖ ጥቁር ቆዳ ባላቸው ሰዎች ላይ በጣም ጎልቶ የሚታይ ቢሆንም ሁሉንም የሰው ልጆች ሊያጠቃ ይችላል።

bbc Amharic

• @ThinkAbyssinia •
7.4K views13:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-12 12:34:59
አስር ተጨማሪ የአውሮፓ ጋዝ ገዢዎች ክፍያቸውን በሩብል ለማድረግ ወሰኑ

በመላው አውሮፓ ያሉ ኩባንያዎች በ ጋዝፕሮም ባንክ መለያ መክፈታቸውን ቀጥለዋል። አስር ተጨማሪ የአውሮፓ ጋዝ ገዢዎች ክፍያቸውን በሩብል ለማድረግ የወሰኑ ሲሆን ለሩሲያ ነዳጅ በ ሩብልስ የሚከፍሉ ደንበኞች ቁጥር በእጥፍ ጨምሯል። ሌላ 14 ድርጅቶች ጥያቄ አቅርበዋል። ጣሊያን እና ጀርመንም ከሩሲያ ጋዝ ተጠቃሚዎች መካከል ይገኙበታል ።

ሩሲያ ጠላቴ ናቸው ያለቻቸው የአውሮፓ ህብረት ሀገራት እና አሜሪካ ከሩሲያ ነዳጅ በሩብል እንዲገዙ ትዕዛዝ ማስተላለፋቸው ይታወሳል፡፡


RT News

• @ThinkAbyssinia •
8.9K views09:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-12 11:34:22
የአፋን ኦሮሞ እና የትግረኛ ቋንቋዎች በGoogle Translate ሥርዓት ውስጥ ተካተቱ

የተለያዩ ቋንቋዎችን የሚተረጉመው Google Translate ተጨማሪ 24 ቋንቋዎችን ወደ ሥርዓቱ ማስገባቱን አስታውቋል። ከዚህ ውስጥም የአፋን ኦሮሞ እና የትግረኛ ቋንቋዎች መካተታቸው ተገልጿል።

አዲስ ከተካተቱት ቋንቋዎች ጋር ተደምሮ አገልግሎቱ 133 የዓለም ቋንቋዎችን መተርጎም ያስችለዋል ተብሏል። ከዚህ ቀደም የአማርኛ ቋንቋ በስርዓቱ ውስጥ ተካቶ አገልግሎት ላይ መዋሉ ይታወሳል።

ድርጅቱ ይህንን አገልግሎት ይፋ ያደረገው በትላንትናው ዕለት ሲሆን እስከ ሳምንቱ መጨረሻ ድረስ ለሁሉም ተጠቃሚዎች ተደራሽ ይሆናል ተብሎ ይጠበቃል።


• @ThinkAbyssinia •
9.0K views08:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-12 10:22:11 #ቲንክአቢሲኒያ_የቡናቁርስ_መረጃዎች

1፤የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የፐብሊክ ዲፕሎማሲ ማዕከል የማስጀመሪያ መርሃግብር መካሄድ ጀመረ።

የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የፐብሊክ ዲፕሎማሲ ማዕከል የማስጀመሪያ መርሃግብር በሐረማያ ዩኒቨርሲቲ እየተካሄደ ነው። በመርሃግብሩ ማስጀመሪያ ላይ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲን ጨምሮ የዩኒቨርሲቲው ሴኔት አባላት መምህራን፣ ተማሪዎች እና አመራሮች ተሳትፈዋል:: የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳድር ዲና ሙፍቲ ዩኒቨርሲቲው በግብርናው ዘርፍ ለሀገር ችግር ፈቺ የምርምር ውጤቶችን እያበረከት አመታትን የዘለቀ ነው ብለዋል:: መርሀግብሩ በሀገራዊ ጉዳይ ላይ ታላቁ የኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብን ጨምሮ ብሔራዊ ጥቅሞች ላይ ሁሉም ዜጎች በፐብሊክ ዲፕሎማሲ ለሀገራቸው እንዴት መሞገት እና ተጽዕኖ ማሳደር እንደሚችሉ ተማሪዎችን ማብቃት እንደሚገባም ተናግረዋል።

2፤በትግራይ ክልል ላይ የጣለው እገዳ እንዲነሳ እና ዕርዳታ እንዲገባ የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ቴዎድሮስ አድኻኖም ጠየቁ።

የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ቴዎድሮስ አድኻኖም የኢትዮጵያ እና ኤርትራ መንግሥታት በትግራይ ክልል ላይ የጣሉትን እገዳ እንዲያነሱ እና ዕርዳታ እንዲገባ እንዲፈቅዱ በድጋሚ እጠይቃለሁ ሲሉ በትዊተር ገጻቸው አስፍረዋል። መንግሥትና የትግራይ ኃይሎች ተኩስ ካቆሙ 10 ሳምንታት እንደሆናቸው የገለጡት ዶ/ር ቴዎድሮስ፣
እስካሁን ወደ ትግራይ የገባው ዕርዳታ ግን 5 በመቶ ብቻ ነው ብለዋል።

3፤መንግሥት የጀመረውን ሕግ የማስከበር እርምጃ አጠናክሮ መቀጠል እንደሚኖርበት ተገለጸ።

መንግሥት የዜጎችን ደህንነትና መብት ለማስጠበቅ የጀመረውን አጥፊዎችን ለሕግ የማቅረብ እርምጃና ችግሩ በሌላ ጊዜ እንዳይደገም ከመሠረቱ የመከላከል ሥራን አጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት የሰብዓዊ መብት ተሟጋቹ አቶ ኦባንግ ሜቶ ገልጸዋል። የሰብዓዊ መብት ተሟጋቹ ኦባንግ ሜቶ በአገሪቱ የሕግ የበላይነትን በማስጠበቅ ዙሪያ ምን መደረግ አለበት ለሚል ወቅታዊ ጉዳይ ዙሪያ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት በኢትዮጵያ በየጊዜው እየታየ ያለውን የጸጥታ መደፍረስ ተከትሎ መንግሥት የጀመረውን የዜጎችን መብትና ደህንነት የማስጠበቅ ኃላፊነቱን በአግባቡ መወጣት አለበት። በየጊዜው እየታየ ያለውን የጸጥታ መደፍረስ ለመከላከል የመንግሥት ዋና ሥራና ትኩረት የዜጎችን መብትና ደኅንነት መጠበቅ መሆን ይኖርበታል።

4፤ ዩክሬን ወታደሮቿ ጣልቃ እየገቡ መሆኑን በመግለጽ የሩሲያ ጋዝ መተላለፊያን ዘጋች።

ቁልፍ ነው የተባለለት ጋዝ መተላለፊያው ሩሲያ ለአውሮፓ ከምታቀርበው ነዳጅ ሶስት እጅ ያህሉ የሚተላለፍበት ነበር ተብሏል፡፡ ነዳጁን የማስተላለፍ ግዴታ ያለባት ዩክሬን በሌላ የማስተላለፊያ መስመር ለአውሮፓ አደርሳለሁ ብትልም እርምጃው በአውሮፓ ያለውን የነዳጅ ዋጋ ንረት የበለጠ እንዳያባብሰው ተሰግቷል፡፡
ኪቭ የሶክራኒቭካ መተላለፊያን የዘጋችው አካባቢውን የተቆጣጠሩት የሩሲያ ወታደሮች ቴክኒካል በሆኑ ነዳጅ የማስተላለፍ ስራዎች ጣልቃ እየገቡ ነው በሚል ነው፡፡ ከረቡዕ ጀምሮ በሶክራኒቭካ በኩል ጋዝ ወደ አውሮፓ ማስተላለፉን እንደሚያቆምም የሃገሪቱ የጋዝ መተላፊያዎች አስተዳደር (GTSOU) አስታውቋል፡፡

5፤ማንችስተር ዩናይትድ የወጣቶቹን ኤፌ ካፕ አሸንፏል።

በተመልካች ቁጥር አዲስ ታሪክን ያስመዘገበው የወጣቶቹ ( ከ 18ዓመት በታች ) የኤፌ ካፕ ፍፃሜ በማንችስተር ዩናይትድ 3 ለ 1 አሸናፊነት ተጠናቋል ። 67,492 ታዳሚያን በ ኦልድ ትራፎርድ ጨዋታውን ሲታደሙ አሊያንድሮ ጋራንቾ ሁለት ግቦች እና ቤኔት ኖቲንግሀም ፎረስትን የረቱበትን ጎሎች አስቆጥረዋል ። አሁን ላይ በአካዳሚው ጥሩ ብቃቱን እያሳየ የሚገኘው አሊያንድሮ ጋራንቾ በውድድሩ ላይ በአስር ጎሎች ላይ ተሳትፎን በማድረግ ቀዳሚውን ደረጃ ይይዛል ። ጨዋታውን የክለቡ የቀድሞ ታላላቅ ግለሰቦች ራያን ጊግስ እና ሰር አሌክስ ፈርጉሰን ታድመውታል ።


• @ThinkAbyssinia •
8.8K views07:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-12 09:39:44
የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ፀሃፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ የአልጀዚራዋ ጋዜጠኛ ላይ የተፈጸመው ግድያ "አስደንጋጭ ነው አሉ

የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ፀሃፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ትላንት ረቡዕ በአንጋፋዋ ፍልስጤም-አሜሪካዊ የአልጀዚራ ጋዜጠኛ ሺሪን አቡ አቅላ ላይ የተፈጸመው ግድያ "አስደንጋጭ ነው" ብለዋል።

የ51 አመቷ ዘጋቢ አቡ አቅላ የእስራኤል ሃይሎች በያዙት ዌስት ባንክ ውስጥ ያደረጉትን ወረራ ስትዘግብ ህይወቷ ሲያልፍ አብሯት በስራ ላይ የነበረው አዘጋጇም ጉዳት ደርሶበታል።

አልጀዚራ የእስራኤል ወታደሮች "ሆን ብለው" ጥይት ተኩሰውባታል ሲል የእስራኤል ጠቅላይ ሚንስትር በበኩላቸው በፍልስጤም ታጣቂዎች ተመትታ ሳይሆን እንደማይቀር ተናግረዋል።

የሚመለከታቸው የመንግሥት ሃላፊዎች ገለልተኛ እና ግልጽ የሆነ ምርመራ እንዲያደርጉ ብሎም ድርጊቱን የፈጸሙትንም ተጠያቂነት እንዲያረጋግጡ'' ሲሉ የተባበሩት መንግሥታት ዋና ጸሃፊ አንቶኒ ጉቴሬዝ በቃል አቀባያቸው በኩል ጥሪያቸውን አቅእርበዋል።

ዋና ጸሃፊው በጋዜጠኞች ላይ የሚደርስ ማንኛውም አይነት ጥቃት እንዲሁም ግድያን ያወገዙ ሲሆን ጋዜጠኞች የማንኛውም አይነት ጥቃት ኢላማ መሆን እንደሌለባቸው ተናግረዋል።

በሌላ በኩል የዋይት ሃውስ ቃል አቀባይ ጄን ፓሳኪ ''አሜሪካዊያን ግድያውን ሲሰሙ ልባቸው ተሰብሯል'' ሲሉም በትዊተር ገጻቸው ላይ አስፍረዋል።


bbc Amharic

• @ThinkAbyssinia •
8.2K views06:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-12 09:15:32
የኢትዮጵያ ቡና በታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ 1 ቢሊየን ዶላር የውጭ ምንዛሪ አስገኘ


የኢትዮጵያ ቡና በታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ 1 ቢሊየን የአሜሪካ ዶላር የውጭ ምንዛሪ አስገኘ። የኢፌዴሪ የግብርና ሚኒስትር ኡመር ሁሴን ለዚህ ታሪካዊ ላሉት ስኬት እንኳን ደስ ያላችሁ ብለዋል።

ሀገሪቱ በተለይም ወደ ቻይና የምትልከው የቡና ምርት በከፍተኛ መጠን አድጓል። በፈረንጆቹ 2021 ዓመተ ምህረት ላይ ቻይና ከኢትዮጵያ ያስገባቸው የቡና ምርት መጠን ከቀደመው ዓመት ጋር ሲነፃፀር በ196 በመቶ አድጓል።

በቅርቡ የኢትዮጵያን የቡና ምርት በቻይና ገበያ የበለጠ ለማስተዋወቅ በተዘጋጀ መድረክ ላይ የሀገሪቱ የቡና ማህበር እንዳስታወቀው በቻይና ከትላልቅ ከተሞች እስከ መለስተኛ ከተሞች የቡና ተጠቃሚዎች ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ ዕድገት ያሳየ ሲሆን፥ ይህም ለኢትዮጵያ ቡና አምራቾች እና ላኪዎች ሰፊ የገበያ ዕድል መፈጠሩ ተመልክቷል።

ሚኒስትሩ ባለፉት የበጀት ዓመቱ ወራት የተገኘው የውጭ ምንዛሪ ምን ያህል የቡና መጠን ወደ ውጭ ተልኮ እንደሆነ አልጠቆሙም።

fana bc

• @ThinkAbyssinia •
8.1K views06:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ