Get Mystery Box with random crypto!

Think Abyssinia

የቴሌግራም ቻናል አርማ thinkabyssinia — Think Abyssinia T
የቴሌግራም ቻናል አርማ thinkabyssinia — Think Abyssinia
የሰርጥ አድራሻ: @thinkabyssinia
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 157
የሰርጥ መግለጫ

➠ ፈጣን እና ተዐማኒ መረጃ፣
➠ የስፓርት እና መዝናኛ ዘገባዎች፣
➠ የምሁራን እይታዎችና መጽሐፈቶች፣
➠ የአለም ሙሉ መረጃና የታሪክ መዛግብቶች ።
ለማንኛውም መረጃ ➥ @Contact_Thinkabyssinia

🎬 "ተመራጭ የዜና ምንጭ"

Ratings & Reviews

3.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 86

2022-05-17 15:17:13
በህገ-ወጥ መንገድ የተከማቸ 50 በርሜል ነዳጅ ከነተጠርጣሪዎቹ በቁጥጥር ስር ዋለ

ከሰሞኑን በአሶሳ ከተማ ውስጥ በግለሰቦች ቤት በተደረገ ፍተሻ የተከማቸ 50 በርሜል ነዳጅ ከነተጠርጣሪዎቹ በቁጥጥር ስር ውሏል።

የአሶሳ ከተማ ፖሊስ ለኢዜአ በሰጠው ቃል ፤ በህገ-ወጥ መንገድ የተከማቸው 50 በርሜል ነዳጅ (ቤንዚን እና ናፍጣ) ከ4 ተጠርጣሪዎች ጋር በህብረተሰብ ጥቆማ በቁጥጥር ስር የዋለ ሲሆን በተጠርጣሪዎች ላይም ምርመራ እየተደረገ መሆኑንም ገልጿል።

በአሁኑ ወቅት በከተማው ቤንዚን እና ናፍጣ በጥቁር ገበያ በሊትር እስከ 200 ብር እየተሸጠ መሆኑን ፖሊስ የጠቆመ ሲሆን የዚህ ህገ-ወጥ የነዳጅ ግብይት ምንጭ በህጋዊ መንገድ ከነዳጅ ማደያዎች ተቀድቶ በህገ-ወጥ መንገድ ወደ ጥቂት ግለሰቦች እጅ መግባት መሆኑን አስረድቷል።

ኢዜአ

• @ThinkAbyssinia •
8.4K views12:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-17 13:29:49
"በሱዳን የተወሰደው ግዛታችን በየትኛውም መመዘኛ ይመለሳል" - አቶ ደመቀ መኮንን

በሱዳን የተወሰደው የኢትዮጵያ ግዛት "በየትኛውም መመዘኛ" እንደሚመለስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡

የሚኒስቴሩ የዘጠኝ ወራት የሥራ አፈጻጸም ዛሬ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ቀርቧል፡፡ ኢትዮጵያ ያላት የሁለትዮሽና የባለብዙ ወገን ዲፕሎማሲ ላይ ያተኮሩ ጉዳዮች የተነሱ ሲሆን የኢትዮጵያ እና ሱዳን አሁናዊ ግንኙነት ላይም ማብራሪያ ተሰጥቷል፡፡

የሱዳን መንግስት ድንበር ጥሶ ወረራ ከመፈጸሙ ባለፈ ለህወሓት መሰረት በመስጠት ወደ ኢትዮጵያ ጥቃት እንዲሰነዘር እያደረገች ነው ሲሉ ተናግረዋል።

ይህ "የመውጋት ያህል" እንደሆነ የገለጹት አቶ ደመቀ ይህንንም እንዲያውቁት አድርገናልም ብለዋል። ኢትዮጵያ፤ ከሱዳን ጋር ያለው ጉዳይ በሰላም እንዲፈታ ማድረግ ያለባትን ሁሉ እያደረገች እንደምትቀጥል አቶ ደመቀ ተናግረዋል፡፡


• @ThinkAbyssinia •
9.0K views10:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-17 12:55:53
#Russia

265 የአዞስታል ታጣቂዎች እጃቸውን መስጠታቸው ተነገረ

ባለፉት ቀናት 265 የአዞስታል(ማሪፖል, ዩክሬኔ) ታጣቂዎች መሳሪያ ጥለው እጃቸውን በሰላም መስጠታቸውን የሩሲያ መከላከያ ሚኒስትር ገለፀ።

Ruptly news watch

• @ThinkAbyssinia •
8.7K views09:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-17 11:59:32
በሞዛምቢክ ከእስር እንዲፈቱ የተደረጉ 32 ኢትዮጵያውያን ወደ አገራቸው ተመለሱ

በሞዛምቢክ በእስር ላይ የነበሩ 32 ኢትዮጵያውንን በማስፈታት በሰላም ወደ አገራቸው እንዲመለሱ ማድረጉን በፕሪቶሪያ የኢትዮጵያ ኤምባሲ አስታወቀ፡፡

ኤምባሲው የዜጋ ተኮር ዲፕሎማሲ ሥራዎችን ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን እና በዚህም በሕገ ወጥ የሰዎች አዘዋዋሪዎች ምክንያት ወደ ደቡብ አፍሪካ ሲጓጓዙ በሞዛምቢክ የጸጥታ አካላት ለእስር የተዳረጉ 32 ኢትዮጵያውያንን ከሚመለከታቸው የአገሪቱ የመንግስት አካላት እና በሞዛምቢክ ዓለምቀአፉ የፍልሰት ድርጅት ጋር በመነጋጋር ማስፈታቱን ገልጿል፡፡

በተጨማሪም በዚምባቡዌ፣ በዛምቢያ እንዲሁም በናሚቢያ በእስር ላይ የሚገኙ ዜጎችን ለማስፈታት ከሚመለከታቸው የመንግስት አካላት እና የዓለምቀፉ የፍልሰት ድርጅት ጋር የቅድመ ማጣራትና የጉዞ ሰነድ ዝግጅት ሥራዎችን እያከናወነ ሲሆን መሆኑንም ነው ኤምባሲው ያሳወቀው፡፡


fanabc

• @ThinkAbyssinia •
9.0K views08:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-17 11:14:14
ፈረንሳይ ከ 30 አመት በኋላ የመጀመሪያዋን ሴት ጠቅላይ ሚኒስትር አገኘች

ኤልሳቤት ቦርን በ30 አመታት ውስጥ የመጀመሪያዋ የፈረንሳይ ሴት ጠቅላይ ሚኒስትር በመሆን በፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን ተሹመዋል። የፈረንሳይ የመጀመሪያዋ ሴት ጠቅላይ ሚኒስትር የነበረችው እኤአ በ 1991 የተመረጠችው ኤዲዝ ክሬሰን ነበረች።

በሀገሪቱ የሰራተኛ ሚኒስትር የነበሩት ኤልሳቤት ቦርን፣ የ61 አመቱን የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር ዣን ካስቴክስን ተክተው የፈረንሳይ ጠቅላይ ሚንስትር ሆነው መሾማቸው ተሰምቷል።

ተሰናባቹ የፈረንሳይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዣን ካስቴክስ የፕሬዚዳንት ማክሮን ዳግም መመረጥን ተከትሎ ለአዲሱ መንግስት የለውጥ አካል ለመሆን በሚል ስልጣናቸውን በገዛ ፈቃዳቸው መልቀቃቸው ተዘግቧል።


• @ThinkAbyssinia •
8.7K views08:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-17 10:17:41 #ቲንክአቢሲኒያ_የቡናቁርስ_መረጃዎች

1፤በአዲስ አበባ 30 ሺህ ብቻ የነበረ የስደተኞች ቁጥር አሁን ላይ ወደ 80 ሺህ አሻቅቧል ተብለዋል።

በሰሜን ኢትዮጵያ የተፈጠረው ግጭት ወደ ከተማ የሚገቡየስደተኞችን ቁጥር በእጅጉ እንዲያሻቅብ ማድረጉን የተባበሩት መንግስታት የስደተኞች ከፍተኛ ኮሚሽን (ዩኤን ኤች ሲአር) አስታወቀ። በኢትዮጵያ የድርጅቱ ተወካይ ማማዱ ዲያን (ዶ/ር) እንደገለፁት በሺዎች የሚቆጠሩ ስደተኖች ወደ አዲስ አበባና ሌሎች አካባዎች ለመሰደድ መገደዳቸውን የተገለፁ ሲሆን በተፈጠረው የጸጥታ ቀውስ ምክንያት በቤንሻንጉል ጉሙዝ፤ የወደመው የጉሬ ሾምቦላ መጠለያ ጣቢያን ጨምሮ ከሌሎች መጠለያ ጣቢያዎች ሸሽተው የመጡ በርካታ ስደተኞች በአዲስ አበባ ይገኛሉም ብለዋል። ከዚህ በፊት በአዲስ አበባ ከተማ 30 ሺህ የነበረው የስደተኞች ቁጥር አሁን ላይ 80 ሺህ መድረሱንም የድርጅቱ ተወካይ ገልጸዋል።

2፤ለሁለኛው ዙር የኢድ እስከ ኢድ ዝግጅት ስኬት ሁሉም ባለድርሻ ሃላፊነቱን እንዲወጣ ጥሪ ቀረበ።

ሰኔ 24 ለሚጀመረው ሁለኛው ዙር የኢድ እስከ ኢድ ዝግጅት የኢትዮጵያን ገፅታ ይበልጥ ለማስተዋወቅ በሚያስችል ደረጃ እንዲዘጋጅ ሁሉም ባለድርሻ ሃላፊነቱን እንዲወጣ ጥሪ ቀረበ። ከኢድ እስከ ኢድ ክብረ በአል የመርሃ ግብሮች አፈፃፀም፣ የእስካሁን ስራዎች እና ቀጣይ ተግባራትን የገመገመ ውይይት ብሄራዊ ፈፃሚ ኮሚቴው ትላንት በበይነ መረብ አከናውኗል። በውይይቱ የተገኘው ተሞክሮም የሁለተኛው ዙር ስራዎችን በላቀ ሁኔታ ለማከናወን እገዛ እንደሚኖረውም ተመሌክቷል። በቀጣይ መርሃ ግብር የተያዙ ታላላቅ ሃይማኖታዊ እና ህዝባዊ መርሃ ግብሮች እንዳሉም ጠቁመዋል።

3፤ዛሬ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አንድ የአሜሪካን ዶላር በ51 ብር ከ4841 ሳንቲም እየተገዛ ይገኛል።

እንዲሁም መሸጫ ዋጋው 52 ብር ከ5138 ሳንቲም መሆኑን ከድረገጹ ተመልክተናል። የአንድ የእንግሊዝ ፓውንድ መግዣ ዋጋው 60 ብር ከ3037 ሳንቲም እንዲሁም መሸጫው 61 ብር ከ5098 ሳንቲም ሆኗል። በተመሳሳይ አንድ ዩሮ በ53 ብር ከ7385 ሳንቲም እየገዛ በ54 ብር ከ7929 ሳንቲም እየተሸጠ ሲሆን፣ አንድ የቻይና ዩዋን ደግሞ በ6 ብር ከ8576 ሳንቲም ተገዝቶ በ6 ብር ከ9948 ሳንቲም እየተሸጠ እንደሚገኝ ቲንክአቢሲኒያ ተመልክቷል።

4፤ቱርክ ስዊድንና ፊንላንድ ኔቶን እንዳይቀላቀሉ አስጠነቀቀች።

የቱርክ ፕሬዝዳንት ራሲፕ ጣይብ ኤርዶጋን ሁለቱ የስካንዲኒቪያን አገራት ኔቶን ለመቀላቀል የሚያደርጉትን ሩጫ እንደሚቃወሙ ዝተዋል። ኤርዶጋን ይህን ያሉት ስዊድንና ፊንላንድ ኔቶን ለመቀላቀል በይፋ መወሰናቸውን ባስታወቁ በሰዓታት ውስጥ ነው። የሩሲያው ፑቲን በበኩላቸው ፊንላድና ስዊድን የጦር ቃል ኪዳን ድርጅቱን መቀላቀላቸው ሞስኮን ያን ያህልም እንደማያስጨንቃት፣ ቀጥተኛም ጉዳት እንደማያደርስባት ተናግረዋል። ኤርዶጋን ትናንት ሰኞ በሰጡት በዚህ ጋዜጣዊ መግለጫ የስዊድንን እና የፊንላንድን ወደ ኔቶ መምጣት በበጎ እንደማያዩት ብሎም እንደሚቃወሙት ዝተዋል። ሁለቱ አገሮች አሸባሪ አቃፊ ናቸው ሲሉም ወርፈዋቸዋል።

5፤ፕሬዝዳንት ማኪ ሳል አሕጉራዊ የብድር ከፋይነት ደረጃ አውጪ ድርጅት እንዲቋቋም ጥሪ አቀረቡ።

የአፍሪካ ኅብረት የወቅቱ ሊቀመንበር የሴኔጋሉ ፕሬዝዳንት ማኪ ሳል አሕጉራዊ የብድር
ከፋይነት ደረጃ አውጪ ድርጅት እንዲቋቋም ጥሪ ማድረጋቸውን የተለያዪ የዜና ምንጮች
ዘግበዋል። ዓለማቀፍ ደረጃ አውጪ ድርጅቶች ለአፍሪካ የሚሰጡት ግምገማ አገራቱ ብድር
እንዳያገኙ አድርጓል በማለት ሳል አማረዋል። በተወሰነ መጠን ትላልቆቹ ድርጅቶች ለአፍሪካ
አገራት ግምገማ ጥቅም ላይ የሚያውሏቸው ከጉዳዩ ጋር ግንኙነት የሌላቸው መስፈርቶች
እንደሆኑ ማኪ ሳል ጠቁመዋል።

6፤አርሰናል በአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ላይ የመሳተፍ እድሉን አጥብቧል።

ትላንት ምሽት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የሰላሳ ሰባተኛው ሳምንት ጨዋታ በሴንት ጀምስ ፓርክ ስታዲየም ቀጥሎ ሲካሄድ አርሰናል ከ ኒውካስትል ጋር ያደረገውን ጨዋታ 2 - 0 በሆነ ውጤት ተሸንፏል ። የኒውካስትልን የማሸነፊያ ግብ ቤን ኋይት በራሱ መረብ ላይ እና ብሩኖ ጉማሬስ አስቆጥረዋል ። ቤን ኋይት በዘንድሮ የውድድር አመት በእንግሊዝ ፕሪሚየር ላይ ለመጀመሪያ ጊዜ በራሱ መረብ ላይ ግብ አስቆጥሯል ። አርሰናል በኒውካስትል ሽንፈትን ማስተናገዱን ተከትሎ ቼልሲ በቀጣዩ የውድድር አመት በአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ላይ መሳተፉን አረጋግጧል ። በቀጣይ እሁድ አርሰናል ከ ኤቨርተን እንዲሁም ቶተንሀም ከ ኖርዊች ሲቲ ጋር የሚገናኙ ይሆናል ። ውጤቱን ተከትሎ አርሰናል በ 66 ነጥብ አምስተኛ ደረጃ ላይ ሲቀምጥ ኒውካስትል በ 46 ነጥብ አስራ ሁለተኛ ደረጃ ላይ ይገኛሉ ።

• @ThinkAbyssinia •
8.7K views07:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-17 09:04:25
ኢዜማ የፓርቲ አመራሮቹነም ሆነ አባላቱን እንዳላገደ ገለፀ

ኢዜማ የፓርቲ አመራሮቼን ከአባልነት እንዳገድኩ ተደርጎ የተሰራጨው መረጃ ሐሰት ነው ሲል በማኅበራዊ ትስስር ገጹ አስታውቋል። አመራሮቹ እና አባላት ከፓርቲው ሥራ አስፈጻሚም ሆነ ከብሄራዊ ምክር ቤት እንዳልታገዱ ፓርቲው ገልጧል።

ሕገወጥ ሰነድ አሰራጭተዋል የተባሉት የፓርቲ ሥራ አስፈጻሚ አመራሮችና አባላት ላይ የተወሰደው ርምጃ የፓርቲው ዲስፕሊን ኮሚቴ ጉዳዩን አጣርቶ ውሳኔ እስኪሰጥ ድረስ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴው ከሰጣቸው የተለያዩ ሃላፊነቶች ለጊዜው ማገድ ብቻ መሆኑን ፓርቲው ገልጧል።

wazema

• @ThinkAbyssinia •
8.9K views06:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-17 08:05:30
#ቲንክአቢሲኒያ_እለታዊ_የአየር_ትንበያ_መረጃ

ለውሎዎ ጠቃሚ የሆኑ እለታዊ የአየር ትንበያ መረጃዎችን እናድርስዎ


ዛሬ በአንዳንድ የሀገራችን ከተሞች ያለውን ያየር ሁኔታ ስንመለከት መዲናችን አዲስ አበባ ዝቅተኛው 12 ከፍተኛው 30 ድግሪ ሲልሽየስ ፀሀያማ ሆና ትውላለች።

ባህርዳር ዝቅተኛው 12 ከፍተኛው 34 ፀሀያማ ሀዋሳ ዝቅተኛው 12 ከፍተኛው 33 በአብዛኛው ፀሀያማ እንዲሁም መቀሌ ዝቅተኛው 15 ከፍተኛው 30 ፀሀያማ ሆነው እንደሚውሉ ቲንክአቢሲንያ ከቤሄራዊ ሜትሮዎሎጂ ኤጀንሲ ድረገፅ ተመልክቷል።


• @ThinkAbyssinia •
9.4K views05:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-16 20:30:34
የሳዑዲ ዓረቢያው ኩባንያ የሶላር ኤሌክትሪክ ኃይል ለማመንጨት የገባውን ውል እንደተሰረዘ ተገለፀ

አንድ የሳዑዲ ዓረቢያ ኩባንያ በአፋር እና ሱማሌ ክልሎች በ300 ሚሊዮን ዶላር የሶላር ኤሌክትሪክ ኃይል ለማመንጨት የገባውን ውል እንደተሰረዘ ሪፖርተር ዘግቧል።

ፕሮጀክቱ በስምምነቱ መሠረት በ6 ወር ባለመጀመሩ፣ መንግሥት ጊዜውን ከሁለት ዓመት በላይ አራዝሞ ነበር። ሆኖም ኩባንያው የሰሜኑን ጦርነት በመጥቀስ፣ ጊዜው በድጋሚ እንዲራዘምለት ጠይቆ ተቀባይነት አላገኘም።

ኩባንያው ጋድ እና ደቸቶ ከተባሉት ፕሮጀክቶች 250 ሜጋ ዋት ኃይል እንደሚያመነጭ ተጠብቆ ነበር። ገንዘብ ሚንስቴር ለፕሮጀክቶቹ ሌላ ጨረታ አውጣለሁ ብሏል።

ሪፖርተር

• @ThinkAbyssinia •
5.8K views17:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-16 20:30:03
የአሜሪካ ወታደሮች በሶማሊያ እንዲሰማሩ ጆ ባይደን ወሰኑ

ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን ከሳቸው በፊት በነበሩት ዶናልድ ትራምፕ የተወሰነዉን ውሳኔ በመቀልበስ የአሜሪካ ወታደሮች ወደ ሶማሊያ እንዲሰማሩ ፈቅደዋል፡፡ ይህንኑ ተከትሎ በመቶዎች የሚቆጠሩ የአሜሪካ ወታደሮች ወደ ሶማሊያ ሊመለሱ ይችላሉ ተብሏል።

ፕሬዚዳንቱ በአልሸባብ የታጣቂ ቡድን መሪዎች ላይ ዒላማ ለማድረግ ከፔንታጎን የቀረበላቸዉን ጥያቄ ምላሽ መስጠታቸዉን በፊርማቸውን አኑረዋል ሲል ኒውዮርክ ታይምስ ዘግቧል፡፡

የብሔራዊ ደኅንነት ምክር ቤት ቃል አቀባይ የሆነችዉ አድሪያን ዋትሰን እንደተናገሩት "እንደገና ለማስጀመር የወሰነው የኃይላችንን ደህንነት እና ውጤታማነት ከፍ ለማድረግ ብሎም ለአጋሮቻችን ቀልጣፋ ድጋፍ ለመስጠት ነው" ብለዋል ። አክለዉም "በአልሸባብ ላይ የበለጠ ውጤታማ ትግል" ለማድረግ ያስችላል ሲሉ ተናግረዋል፡፡

አሜሪካ ይህንን ዉሳኔ ያሳለፈችዉ የሶማሊያ የፓርላማ አባላት እሁድ እለት አዲሱን ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ መሀመድን መምረጣቸዉን ተከትሎ ነዉ ሲል ዋዜማ ኒውዮርክ ታይምስ ጠቅሶ ዘግቧል፡፡

• @ThinkAbyssinia •
5.4K views17:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ