Get Mystery Box with random crypto!

ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ

የሰርጥ አድራሻ: @ortodoxtewahedo
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 47.96K
የሰርጥ መግለጫ

ይህ ቻናል የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ዶግማንና ቀኖናን ትውፊትን እንዲሁም አስተምሮን የጠበቁ የተለያዩ የሚያስተምሩ ነገሮች ይለቀቁበታ፡፡ በተጨማሪ በ youtube #subscribe በማድረግ አገለግሎቱን ይደግፉ።
‹‹ከትውልዱ ማን አስተዋለ››
ት.ኢሳ 58÷3
https://youtu.be/csxxAMGtC4I
ለመቀላቀል
http://t.me/ortodoxtewahedo

Ratings & Reviews

4.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 4

2023-07-04 05:51:07

እንኳን ለቅዱስ ሐናንያ ሐዋርያ (ከ72ቱ አርድእት)፣ ለቅዱስ ቶማስ ሰማዕት (ዘሰንደላት)፣ ለቅዱስ አልዓዛር ነዳይ (በነዌ ደጅ የወደቀ: ቀጥሎ ደግሞ በአብርሐም እቅፍ ውስጥ የተገኘ ጻድቅ - ሉቃ. 16÷19) እንዲኹም ለቅዱስ ማማስ ዓመታዊ የመታሰቢያ በዓል በሰላም አደረሳችኹ



"ጽዮንን የሚወዳት አይደክምም!"

ዳግመኛም ዛሬ ሰኔ 27 ቀን የጌታችንና አምላካችን መድኃኔዓለም ክርስቶስ በዓለ ስቅለት፣ አቡነ መብዐ ፅዮን ጻድቅ፣ ቅዱስ መቃርስ (የመነኮሳት ኹሉ አለቃ)፣ ቅዱስ ያዕቆብ ዘግሙድ፣ ቅዱስ ገላውዴዎስ ሰማዕት (ንጉሠ ኢትዮጵያ)፣ ቅዱስ ቢፋሞን ጻድቅና ሰማዕት እንዲኹም ማር ቅዱስ ፊቅጦር ሰማዕት ወርኃዊ መታሰቢያቸው ነው

አምላከ ቅዱሳን በቃልኪዳናቸው ይማረን አሜን!

"የቅዱሳን መታሰቢያ ለበረከት ነው" ምሳ. ፲፥፯



  #ባለ ማዕተቦችን ወደዚህ ግሩፕ ይጋብዙ
መልካም ቀን  

ለመቀላቀል  
@ortodoxtewahedo
2.5K viewsedited  02:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-03 11:12:17 ‹‹እለ ይዘርኡ በአንብዕ ወበኃሤት የአርሩ፤ በልቅሶ የሚዘሩ በደስታ ይሰበስባሉ›› (መዝ.፻፳፭፥፭)
                                 
ስንዱ እመቤት በሆነች ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን የወቅቶች አከፋፈል መሠረት ከሰኔ ፳፮ ቀን እስከ መስከረም ፳፭ ያለው ጊዜ ዘመነ ክረምት ይባላል፡፡

“ክረምት” የሚለው ቃል ‘ከርመ፣ ከረመ’ ከሚለው የግእዝ ቃል የተገኘ ሲሆን ትርጓሜውም ወርኃ ዝናም፣ ወርኃ ነጎድጓድ፣ ዘመነ ባሕር፣ ዘመነ ነጎድጓድ፣ ዘመነ አፍላግ፣ ዘመነ ጠል፣ ዘመነ ደመና፣ ዘመነ መብረቅ… ማለት ነው፡፡ (ጥዑመ ልሳን ያሬድና ዜማው) ይህ ወቅት ከትርጓሜው እንደምንረዳው የሰው ልጅን ጨምሮ ተንቀሳቃሽ ለሆኑ ፍጥረት ሕይወት ከባድ የሚሆንበት ግን ደግሞ ለመኖር የሚያስችለውን ልብሱንና ጉርሱን የሚያገኘው በክረምት አማካኝነት እንደሆነ ከጥቅሱ እንረዳለን፡፡

ዘመነ ክረምት፡- የዝናም፣ የዘርና የአረም ወቅት በመሆኑ ምድር በጠል ዝናም ትረካለች፡፡ ዕፅዋት አዝርዕትና አትክልት በቅለው፣ ለምልመው የሚያድጉበት፣ ምድር አረንጓዴ ለብሳ በሥነ ጽጌያት የምታሸበርቅበት ወቅት ቢሆንም በሀገራችን አብዛኛው የግብርና ሥራ የሚከወንበት ጊዜ ስለሆነ በላይ ዝናቡ በውስጥ ርኃቡ በታች ዳጡ ማጡ የሚፈትነበት የመከራ ወቅት ነው፡፡ ‹‹እለ ይዘርኡ በአንብዕ ወበኃሤት የአርሩ፤ ሶበሰ የሐውሩ ወፈሩ እንዘ ይበክዩ ወፆሩ ዘርኦሙ፤ ወሶበ የአትው መጽኡ እንዘ ይትፌሥሑ፤ በሔዱ ጊዜ ዘራቸውን ተሸክመው እያለቀሱ ተሰማሩ፤ በተመለሱ ጊዜ ግን ነዶአቸውን ተሸክመው ደስ እያላቸው ይመጣሉ›› በማለት ቅዱስ ዳዊት ይናገራል፡፡ (መዝ.፻፳፭፥፭) ‹‹…….ክረምት ነበርና ስለውርጩ ጽናት ይንቀጠቀጡ ነበር›› እንዳለ ዕዝራ፡፡ (ዕዝ. ካል. ፱፥፲፩)

ወርኃ ክረምት የክርስትና ምሳሌ ነው፤ በክረምት ወር ገበሬ ብርዱንና ዝናሙን ሳይሰቀቅ ለሥራ ይሰማራል፤ በጋው እንደሚመጣ የደከመበትን፣ ዝናቡንና ርኃቡን፣ ድጡን ማጡን የታገሠበትን የድካሙን ፍሬ እንደሚያጭድ፣ ዘጠኝ ወር በጋም ፍሬውን እንደሚመገብ አምኖ የክረምቱን መከራም ይታገሣል፡፡ ክርስቲያንም በዚህ ምድር ላይ የሚደርስበትን መከራ ሁሉ ይታገሣል፤  በጸጋ የሚቀበለው በዚያኛው ዓለም ስለሚያገኘው ተድላና ደስታ ነው፡፡ ‹‹በዚህ ዓለም ሳላችሁ መከራ አለባችሁ›› የሚለውን አምላካዊ ቃል ያውቃሉና፤ (የሐ.፲፮÷፳) ‹‹ዝግባውም የክረምት ዝናብ በእርሱ ላይ ካልወረደ ከሥሩ ይነቀላል›› እንደተባለው ያለዝናም ዝግባ፣ ያለመከራ ክርስትና እንደሌለ እንረዳለን፡፡ (፩ኛመቃ.፰፥፴፬)

አምላካችን እግዚአብሔር ለኖኅ በገባለት ቃል ኪዳን መሠረት በጋና ክረምቱ፣ ብርድና ሙቀቱ፣ ቀንና ሌሊቱ በተወሰነላቸው ጊዜ እየተፈራረቁ ለሰው ልጆች ጥቅም እንዲሰጡ አድርጓቸዋል፡፡(ዘፍ.፰፥፳፪)

ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ወቅቶችን መሠረት አድርጋ ጌታዋን አብነት አድርጋ በወቅቶች እየመሰለች ወንጌልን ታስተምራለች፡፡ እናም የክረምቱን ዝናም፣ ነጎድጓድ፣ ጭቃውን፣ ብርዱን፣ ጨለማውን፣ ጎርፉን ወዘተ በክርስትናው መከራ እየመሰለች ስታስተምር እንዲሁም በዘሩ ቃሉን፣ በልምላሜው ተስፋውን፣ በመከሩ ምጽአቱን፣ በፍሬው መንግሥተ ሰማያትን እየመሰለች  ትሰብክበታለች፡፡ ለዚህም አብነቷ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ‹‹ወጸልዩ ባሕቱ ከመ ኢይኩን ጉያክሙ በክረምት ወበሰንበት፤ ነገር ግን ስደታችሁ በክረምት በሰንበት እንዳይሆንባችሁ ለምኑ›› በማለት አስተምሯልና፡፡ (ማቴ.፳፬፥፳) ለምን ቢሉ ክረምት ላዩ ውኃ ታቹ ውኃ ነው፤ አያሸጋግርምና ሰንበትም ዕለተ ዕረፍት ስለሆነ መንገድ ቢስቱ የሚያመላክት አይገኝምና፤ አንድም ‹‹ዐርፋለሁ ባለበት ጊዜ ስደት ቢመጣ ከቀቢጸ ተስፋ ይደርሳልና በሰንበትና በክረምት እንዳይሆንባችሁ ጸልዩ›› አለ፡፡

ቤተ ክርስቲያን ወቅቶችን እንዲህ በመከፋፈል በወቅቱ ከሚታየው የተፈጥሮ ሁኔታ ጋር ምእመናን ሕይወታቸውን እንዲመረምሩና ለንስሓ እንዲበቁ አጥብቃ የምታስተምራቸው ለዚህ ነው፡፡ በተለይ ቅዱስ ያሬድ በድርሰቶቹ ከደመናው፣ ከዝናቡ፣ ከልምላሜው፣ ከአበቦች፣ ከፍሬው ወዘተ እያስማማ ልብን በሚማርክ ዜማ በብዙ መልኩ አስተምሮናል፡፡ ‹‹ደምፀ እገሪሁ ለዝናም ሶበ ይዘንም ዝናም ይትፌሥሁ ነድያን፤ ይጸግቡ ርኁባን፤ የዝናም ድምፅ ተሰማ፤ ዝናም በዘነመ ጊዜ ችግረኞች ይደሰታሉ፤ ረኃብተኞችም ይጠግባሉ›› ሲል ያሰናስለዋል፡፡

የክርስትናችን ክረምት አልፎ ለመከር እንድንበቃ፣ ስደታችን በሰንበትና በክረምት ሆኖብን በቀቢጸ ተስፋ እንዳንጠፋ፣ በቅጠል ወራት ሳይሆን በፍሬ ወራት እያለቀስን ተሰማርተን፣ ደስ እያለን እንድንመለስ አብዝተን እንጸልይ፡፡ ‹‹እነሆ ክረምት ዐለፈ፤ ዝናቡም አልፎ ሄደ›› እንዳለ ጠቢቡ ሰሎሞን የክርስትናችን ክረምት የመከራችን ዝናብ ከእኛ ላይ በቶሎ ያልፋል፡፡ (መኃ.፪፥፲፩)

አምላካችን እግዚአብሔር መከራና ችግሩን ያሳልፍልን፤ አሜን!
ወስብሐት ለእግዚአብሔር!

ከማህበረ ቅዱሳን ዋናው ማዕከል ቴሌግራም ላይ የተወሰደ

@ortodoxtewahedo
3.3K viewsedited  08:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-03 10:04:59
“የእግዚአብሔር እርሻ ናችሁ፤ የእግዚአብሔር ሕንፃ ናችሁ፤ ከእርሱ ጋር አብረን የምንሠራ ነንና።”1ኛ ቆሮ 3፥9

@ortodoxtewahedo
2.7K viewsedited  07:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-03 10:03:26
“ጽድቅና ትሩፋት እንደ ሃብተ ማርያም "

እንኳን ለጻድቁ አባታችን አቡነ ሀብተ ማርያም አመታዊ ክብረ በዓል በሰላም በጤና አደረሰን አደሰችሁ ።

ጽሩይ እምወርቅ ወእምብሩር ንጡፍ ወኅሩይ እምአእላፍ ሀብተ ማርያም መልአክ ዘውገ ኪሩብ ቀሊለ ክንፍ አማን ስሙዐ ዜና እስከ አጽናፍ ፡፡

ሰላም ለፅንሰትከ እማህፀነ ቅድስት ዮስቴና በብሥራተ ጻድቅ ባሕታዊ ሠናየ ዜና ሐብተ ማርያም ጴጥሮስ ሐዋርያ ወልደ ዮና መሐረኒ ምግባረ ጽድቅ ወጸግወኒ ልቦና አፍቅሮ ቢጽ እኃሥሥ ዘምስለ ፍጽምት ትሕትና::

(መልክአ አቡነ ሀብተ ማርያም)

" እግዚአብሔር ፍርድን ይወድዳልና ::
ቅዱሳኑንም አይጥላቸውምና ::
ለዘለዓለምም ይጠብቃቸዋል . . . ጻድቃን ምድርን ይወርሳሉ:: በእርስዋም ለዘላለም ይኖራሉ :: የጻድቅ አፍ ጥበብን ያስተምራል ::
አንደበቱም ፍርድን ይናገራል ::
የአምላኩ ሕግ በልቡ ውስጥ ነው :: በእርምጃውም አይሰናከልም:: "
(መዝ 36፥28-31 )

ቅዱስ አባታችን ፅንሰታቸው ነሐሴ 26
ልደታቸው ግንቦት 26
ዕረፍታቸው ኅዳር 26 ነው ፡፡

ኦ አምላከ አቡነ ሀብተ ማርያም ዕቀቦ ወአድኅኖ ወባልሆ እመከራ ሥጋ ወነፍስ ወእምኩሉ ተቃራኒ ወእምኩልነ ክቡር ሀብተ ማርያም ለዓለም ዓለም አሜን ለይኩን ለይኩን ::

ወስብሐት ለእግዚአብሔር !

@ortodoxtewahedo
2.5K viewsedited  07:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-03 10:03:25
@ortodoxtewahedo
2.2K viewsedited  07:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-10 07:43:45 " እኔ ጵጵስና የተሾምኩበትን ቀን የማስታውሰው በኀዘንና በልቅሶ ነው፡፡"

ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ሺኖዳ

@ortodoxtewahedo
2.8K viewsedited  04:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-10 07:43:10
"አማን መነኑ ሰማዕት ጣዕማ ለዛ ዐለም። ወከዓው ደሞሙ በእንተ እግዚአብሔር። ወተዓገሡ ሞተ መሪረ በእንተ መንግሥተ ሰማያት።"

"ሰማዕታት የዚህችን ዓለም ጣዕም በእውነት ናቁ፤ ስለ እግዚአብሔር ብለው ደማቸውን አፈሰሱ፤ ስለ መንግሥተ ሰማያትም ሲሉ መራራ ሞትን ታገሡ።"

ይግባኝ ለክርስቶስ !

@ortodoxtewahedo
2.6K viewsedited  04:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-09 14:06:58 ዘርህና እምነትህ የተምታታብህ በዘረኝነት ታመህ ለቤተ ክርስትያን ጀርባህን የሰጠህ ዘሯ ክርስቶስ የሆነውን ቤተ ክርስትያን ዘር ውስጥ ለመክተት የምትጥር ። ሰይጣን ቤተ ክርስትያንን ለመዋጋት ያመጣው መሆኑን ያልተረዳህ መንግስተ ሰማያት በዘር የሚወረስ ይመስል ግራ የገባህ የመዳን ቀን ዛሬ ነው ስለ አንዲት ቤተ ክርስትያንና ስለ አንዲት ሃገር የምንቆምበት ።

#ኦርቶዶክስ ተዋህዶ

@ortodoxtewahedo
3.2K viewsedited  11:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-09 14:02:17
መምህር ኃይለማርያም ዘውዱ ከእስር ከተለቀቁ በኃላ ወደ ባህር ዳር ከተማ ሲገቡ በማህበረ ካህናት እና ምዕመናንን ደማቅ አቀባበል ተደርጎላችዋል
***

ቤተክርስቲያን ከነገሰው ሻጯ ይልቅ የታሰረላትን ወዳጇን እንዴት እንደምታከብር ታውቅበታለች።

እግዚአብሔር ይመስገን !!!

@ortodoxtewahedo
3.1K views11:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-09 14:01:38
ቅዱስ ፓትርያርክ አሁንም ግፍን እያወገዙ ነው።

ቅዱስነታቸው በተባበሩት ዓረብ ኢምሬቶች አቡዳቢ ደብረ ሰላም መድኃኔ ዓለም የመቃረቢያ ቤተ ክርስቲያን የምረቃ ሥነ ሥርዓት ላይ በአስተላለፋት አባታዊ መልእክት ላይ እንዲህ ብለዋል።

". . . [ልጆቻችን] እናት ዕድለኞች ናችሁ። ለዚህም እግዚአብሔርን ልታመሰግኑ ይገባል። [ይህ] አሁን በሀገራችን ካለው የተለየ ነው። በሀገራችን ያሉት [ልጆቻችን] ይህን ዕድል አላገኙም። [እነርሱ] ዜግነታቸው፣ መብታቸውና ንብረታቸው ሁሉ ተወስዷል። የማይገባ ሥራ እየተሠራ ነው። ተገቢም ያልሆነ ነገር እየተሠራ ነው። የሰው ሀገር መቶ ፕርሰንት ይመቻል ባይባልም፤ እናተ ግን በሰው ሀገር በጃችሁም አልበጃችሁም ቢያንስ በሰላም ትኖራላችሁ ። ይህ ልዮነት የለውም ? እኛ እንኳን በሀገራችን ሁሉ ተውስዶብናል። መብቱ፣ ዜግነቱ፣ ሀብቱ፣ ንብረቱ ሁሉ ተወስዷል። ለምን ቢባል ማነው ተጠያቂው ? ማን ጠያቂ፤ ማን ተጠያቂ ይሆናል። በጭራሽ የሚቻል አልሆነም። . . . "

@ortodoxtewahedo
2.4K viewsedited  11:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ