Get Mystery Box with random crypto!

ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ

የቴሌግራም ቻናል አርማ ortodoxtewahedo — ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ
የቴሌግራም ቻናል አርማ ortodoxtewahedo — ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ
የሰርጥ አድራሻ: @ortodoxtewahedo
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 46.78K
የሰርጥ መግለጫ

ይህ ቻናል የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ዶግማንና ቀኖናን ትውፊትን እንዲሁም አስተምሮን የጠበቁ የተለያዩ የሚያስተምሩ ነገሮች ይለቀቁበታ፡፡ በተጨማሪ በ youtube #subscribe በማድረግ አገለግሎቱን ይደግፉ።
‹‹ከትውልዱ ማን አስተዋለ››
ት.ኢሳ 58÷3
https://youtu.be/csxxAMGtC4I
ለመቀላቀል
http://t.me/ortodoxtewahedo

Ratings & Reviews

4.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2023-07-24 20:43:15
በፀሎት ሁላችንም ተግተን ወደ ፈጣሪያችን እንፀልይ በውጭም በሀገር ውስጥም ያላቹ አባቶች :ምዕመናን :አጠቃላይ የቤተክርስቲያን ልጆች የቤተክርስቲያን አንድነት የሚሰብክ ነገር እንድታስተላልፍ በእግዚአብሔር ስም እንጠይቃለን ምክንያቱም አንዳንድ መልዕክቶች ይበልጥ ቤተክርስቲያን የሚከፋፍሉ አሉና ጥሩን ነገር ብቻ እንድታስተላልፍ ጥሪ እናቀርባለን ::

ብፁዕ አብነ አብርሃም

የቅዱስ ሲኖዶስ ጠቅላይ ስራ አስኪያጅ


@ortodoxtewahedo
1.5K viewsedited  17:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-24 17:44:48
http://t.me/ortodoxtewahedo
1.9K views14:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-24 17:44:42 በትግራይ በተከናወነው የሕገ ወጥ ኤጲስ ቆጶሳት ሹመት አስመልክቶ ቅዱስ ሲኖዶስ ጽ/ቤት ለሐምሌ 25/2015 ዓ.ም ምልዐተ ጉባኤ ጠራ።

1. በክልል ትግራይ በተከሰተው ጦርነት ምክንያት በክልሉ ከሚገኙት አህጉረ ስብከት ጋር ተቋርጦ የነበረውን መዋቅራዊ ግንኙነት ችግር በውይይት እንዲፈታ ቅዱስ ሲኖዶስ ተደጋጋሚ የሰላም ጥሪና ልዑካኑን በአካል ልኮ ከፍተኛ ጥረት እያደረገ ባለበት ወቅት በክልሉ የሚገኙ ብፁዓን አባቶች ሕገ ቤተ ክርስቲያንንና ቀኖና ቤተ ክርስቲያንን በመጣስ ቅዱስ ፓትርያርኩ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ተብለው በሚጠሩበት በማዕከላዊ ትግራይ ዞን አክሱም ሀገረ ስብከት በርእሰ አድባራት ወገዳማት አክሱም ጽዮን ቤተ ክርስቲያን ሐምሌ 15 እና 16 ቀን 2015 ዓ.ም. በተከናወነ ሕገ ወጥ ሢመተ ኤጲስ ቆጶሳት መፈጸሙን በመገናኛ ብዙኃን ለማወቅ ችለናል፡፡ በመሆኑም በዚህ የዶግማና የቀኖና ጥሰት ተግባር የቅዱስ ሲኖዶስ ጽ/ቤት በእጅጉ አዝኗል፡፡

2. በመሆኑም የተከሰተው የዶግማ፣ የቀኖና እና አስተዳደራዊ ጥሰት አስመልክቶ ተወያይቶ ተገቢውን ለመወሰን ለሐምሌ 25 ቀን 2015 ዓ.ም. አስቸኳይ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ጥሪ ተላልፏል፡፡

3. የስብሰባው ቀን ሊራዘም የቻለው በውጭው ክፍለ ዓለማት ያሉት ሊቃነ ጳጳሳት መገኘት ስላለባቸው የጉዞ ቀኑ እንዳያጥር እና በሀገር ውስጥ የሚገኙትም ሊቃነ ጳጳሳት ለቅዱስ ገብርኤል ዓመታዊ ክብረ በዓል ምክንያት ለአገልግሎት ወደ አህጉረ ስብከታቸው የሄዱ በመሆኑ ለመመለሻ የሚያስፈልገውን ጊዜ ታሳቢ በማድረግ ነው፡፡

4. በየደረጃ ያሉ የቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን የሥራ ኃላፊዎች እና ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን እንዲሁም ምዕመናን ከአሁን ቀደም በቤተ ክርስቲያናችን ላይ በደረሰው ፈተና በሐዘንና በጸሎት ከቤተ ክርስቲያናችን ጎን በመቆም ላሳያችሁት ጽናት እያመሰገንን አሁንም በደረሰው ፈተና እንዳሁን ቀደሙ ሁሉ በሐዘንና በጸሎት ከቤተ ክርስቲያናችን ጎን ጸንታችሁ እንድትቆሙ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን፡፡

5. በመላው ዓለም የምትገኙ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን እምነት ተከታዮች የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ በጉዳዩ ላይ ተወያይቶ ተገቢውን ውሳኔ እስከሚሰጥ ድረስ በትግዕስት እንድትጠብቁ እናሳስባለን፡፡

6. ምንም እንኳን ለቅዱስ ሲኖዶስ አባላት በሙሉ ጥሪው በደብዳቤ የተላለፈ ቢሆንም የመልእክቱ በፍጥነት መድረስ ካለው ስጋት አንጻር የችግሩን ተደጋጋሚነትና አሳሳቢነት ከግምት ውስጥ በማስገባት በሀገር ውስጥም ሆነ በውጭው ክፍለ ዓለማት የምትገኙ ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት በሙሉ እስከ ሐምሌ 24 ቀን 2015 ዓ.ም. ድረስ ተጠቃላችሁ ወደ ጽርሐ መንበረ ፓትርያርክ እንድትመጡ በጥብቅ እናሳስባለን፡፡


7. ሁሉም የቤተ ክርስቲያናችን ሚዲያዎችና ሌሎች መገናኛ ብዙኃን ይህን መልዕክት ለሁሉም ተደራሽ እንዲሆን መልእክቱን በማስተላለፍ ኃላፊነታችሁን እንድትወጡ በቤተ ክርስቲያናችን ስም እንጠይቃለን፡፡

ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ሐምሌ 17 ቀን 2015 ዓ.ም.

ምንጭ: ኢኦተቤ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ

http://t.me/ortodoxtewahedo
1.5K viewsedited  14:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-24 15:56:42
“እስከ ትበጽህ ለሞት ተበዓስ በእንተ ጽድቅ እስመ እግዚአብሔር አምላክከ ይትበአስ
በእንቲአከ”

“እስክትሞት ለእውነት ታገል። እግዚአብሔር ላንተ ይታገልለሀልና”

           ሲራክ 4 ፡ 2

ምዕመናን መረጃ ይደርሳቸውና ይነቁ ዘንድ ይሄን ሊንክ ለሁሉም ኦርቶዶክሳዊ አድርሱ ቀላል የሚመስል ግን ብዙ ጥቅም አለው አድርጉት።

በዚ ግዜ ለዚያልሆንን መቼ ልንታዘዝ ነው። 

#share #share #share 

http://t.me/ortodoxtewahedo
1.7K viewsedited  12:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-24 15:54:15
“ሰማዕታት የዚችን ዓለም ጣዕም በእውነት ናቁ፤ ደማቸውን ስለ እግዚአብሔር አፈሰሱ፤ ስለ መንግሥተ ሰማያት መራራ ሞትን ታገሱ፡፡”

የኅሙስ ውዳሴ ማርያም

ወኢያረትዕ ቅድሜየ ዘይነብብ ዐመፃ
አመጻን የሚናገር በፊቴ አይጸናም

     መዝ 100:1

በትቢት እና በአመጽ የተሞላችሁ የዱድያኖስ ግብራ አበሮች ወደ ልባችሁ ተመለሱ እንቢ ካላችሁ ግን ብርቱዎችን ደካማ የሚያደርገው የእግዚአብሔርን ክንድ አትችሉትም።


ምዕመናን መረጃ ይደርሳቸውና ይነቁ ዘንድ ይሄን ሊንክ ለሁሉም ኦርቶዶክሳዊ አድርሱ ቀላል የሚመስል ግን ብዙ ጥቅም አለው አድርጉት።

በዚ ግዜ ለዚያልሆንን መቼ ልንታዘዝ ነው። 

#share #share #share 

http://t.me/ortodoxtewahedo
1.4K views12:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-24 15:54:15
መልካም ቢሆን ወይም ክፉ እንዳደረገ፥ እያንዳንዱ በሥጋው የተሠራውን በብድራት ይቀበል ዘንድ ሁላችን በክርስቶስ በፍርድ ወንበር ፊት ልንገለጥ ይገባናል።”

— 2ኛ ቆሮ 5፥10

ምዕመናን መረጃ ይደርሳቸውና ይነቁ ዘንድ ይሄን ሊንክ ለሁሉም ኦርቶዶክሳዊ አድርሱ ቀላል የሚመስል ግን ብዙ ጥቅም አለው አድርጉት።

በዚ ግዜ ለዚያልሆንን መቼ ልንታዘዝ ነው። 

#share #share #share 

http://t.me/ortodoxtewahedo
1.2K views12:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-24 15:50:12
ከጴጥሮሳውያን የማኅበራት ኅብረት
የተሰጠ መግለጫ ::

@ortodoxtewahedo
1.3K views12:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-24 15:45:06
1.3K views12:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-24 15:26:27
#ብፁዓን አባቶች ጅጅጋ ገቡ።

ዛሬ በጅጅጋ ከተማ በገራድ ዊልዋል አየር መንገድ ሲደርሱ ደማቅ አቀባበል የተደረገላቸው በቅዱስ ሲኖዶስ አዲስ የተሾሙት ብፁዓን ኤጲስ ቆጶሳት እና ብፁዓን አባቶች ብፁዕ አቡነ መቃሪዮስ
የሶማሌ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ
ብፁዕ አቡነ ኒቆዲሞስ
የምሥራቅ ሐረርጌ ሀገረ ስብከት ኤጲስ ቆጶስ
ብፁዕ አቡነ በርተሎሜዎስ
የድሬዳዋ ሀገረ ስብከት ኤጲስ ቆጶስ
ብፁዕ አቡነ ገሪማ
የጌዴኦ አማሮ ና ቡርጂ ሀገረ ስብከት ኤጲስ ቆጶስ
በምስራቀ ፀሀይ ቅድስ ኪዳነምሕረት እና ቅዱስ አማኑኤል ካቴድራል ሲገቡ የቤተክርስቲያን ሊቃውት ካህናት አባቶች የአብያተ ቤተክርስቲያናት አስተዳዳሪዎች የሀገረ ስብከቱ ከፍተኛ ሀላፊዎች እና ሰንበት ትምህርት ቤቶች እና ማኀበራት እና ምእመናን በመገኘት ደማቅ አቀባበል ተደርጎላቸዋል ።

መረጃ ምንጭ :አማኑኤል የጅጅጋ ወጣቶች መንፈሳዊ ማኀበር

@ortodoxtewahedo
1.3K views12:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-24 15:26:23
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት ለሐዋርያዊ አገልግሎት ወደ ቁልቢ ቅዱስ ገብርኤል ተጉዘዋል።

ሐምሌ 17 ቀን 2015 ዓ.ም (ተ.ሚ.ማ/አዲስ አአባ)

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት ከብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ጋር በመሆን የሐምሌ 2015 ዓ.ም የቁልቢ ቅዱስ ገብርኤል በዓለ ንግሥ ለማክበር ዛሬ ድሬዳዋ ከተማ ገብተዋል ።

ዛሬ ሐምሌ 17 ቀን 2015 ዓ,ም ቅዱስነታቸው ድሬዳዋ ከተማ ሲገቡ በአውሮፕላን ማረፊያ እና በመንበረ ጵጵስናው ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል ካቴድራል የድሬዳዋ ከንቲባ ክቡር አቶ ከድር ጁሀር ፣ ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳትና የድሬዳዋ ገዳማትና አድባራት አስተዳዳሪዎች ካህናትና ምእመናን ደማቅ አቀባበል አድርውላቸዋል።

ቅዱስነታቸው በአቀባበሉ ላይ ለተገኙ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያንና ምእመናን ቃለ ምእዳንና ቡራኬ ሰጥተዋል ።

@ortodoxtewahedo
1.2K views12:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ