2022-09-01 09:49:08
የትግራይ ወራሪ ኃይል የወልቃይት ጠገዴንና አከባቢውን ከ16 ዓመት ታዳጊ ጀምሮ እስከ 70 ዓመት አዛውንት የሆነ ማንኛውንም ትግራዋይ የወልቃይት ጠገዴ የአማራ ህዝብን እንዲወር የክተት አዋጅ አውጇል።
ማንነታችን እንደ ወንጀል ተቆጥሮ የአማራ ተወላጅ የሆነ ሁሉ በየሄደበት እንደ ዶሮ አፍኖ በመሰወር፣ በመግደል፣ አካልን በማጉደል፣ ከሰማይ በታች ከመሬት በላይ አለ የሚባል ግፍ ሁሉ ተፈፅሞብናል። በሺዎች የሚቆጠሩ ታሪክ አዋቂዎች፣ ስለ ህዝብ መብት ተከራካሪ የሆኑትን የሀይማኖት አባቶችን የት እንደደረሱ ሳይታወቅ ደብዛቸው ጠፍቷል።
ስለሆነም በኢትዮጵያ መከላከያ ኃይል፣ በአማራ ልዩ ኃይል፣ በአንበሳው የአማራ ፋኖ እንዲሁም ሚሊሻና ሌሎች የፀጥታ አካላት ጥምር ተጋድሎ የወልቃይት ጠገዴ አማራ ማህበረሰብ ነፃ ወጥቷል። ይህ የትናንት አኩሪ ገድላችን ነው።
መላው የወልቃይት ጠገዴ አማራ ህዝብ ሆይ ወራሪውና ተስፋፊው የትግራይ ኃይል ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ህልውናህን ሊያጠፋ ቆርጦ ተነስቷል። በመሆኑም በጠላት ዝግጅት መጠን ልክ በተጠንቀቅ እንድትቆም የወቅቱ አስገዳጅ ሁኔታ ሆኗል።
የተከበርከው የአማራ ህዝብ ሆይ!!
በህብረት፣ በአንድነት፣ በፅናት ስለታገልክ የስርዓት ለውጥ አምጥተሃል። ነፃነትም አግኝተሃል። ይሁን እንጂ ድጋሚ ህልውናህን ሊያጠፋ ከመላ ትግራይ የከተተ ወራሪ ኃይል በይፋ ጦርነት አውጆብሃል።
የተከበርከው የኢትዮጵያ ህዝብ ሆይ!!
የወልቃይት ጠገዴ ህዝብ የትግራይ ተስፋፊ ኃይል ባወጀው ጦርነት ምክንያት ከፍተኛ ስጋት ውስጥ ገብቷል። ከአሁን በፊት የወልቃይት ጠገዴ ህዝብ ስቃዩ ስቃዬ፣ በደሉ በደሌ ነው ብለህ ከፍተኛ ዋጋ ከፍለሃል። ይህንን የወልቃይት ጠገዴ ህዝብ ያደንቃል እውቅናም ይሰጣል። ሀብት ማፍራት ይሁን በህይወት መኖርም አገር ሲኖር ነውና፤ ይህንን አገር አጥፊ ወራሪ ቡድን ለመመከት በምናደርገው ተጋድሎ ከጎናችን እንድትቆም ጥሪያችን እናስተላልፋለን።
ይህንን የወልቃይት ጠገዴ አማራ ማንነት አስመላሽ ኮሚቴ ጥሪ ተቀብያለሁ የሚል ሁሉ የአንድ ወር ስንቅ በማዘጋጀት በየቤቱና በየቀበሌው ሆኖ ለምናቀርበው የፈጥነህ ድረስ ጥሪ ዝግጁ ሆኖ እንዲጠብቅ ሲል ኮሚቴው መልዕክቱን ያስተላልፋል።
''ከአማራነታችን ዝቅ የሚያደርገን ምድራዊ ኃይል የለም!!''
የወልቃይት ጠገዴ አማራ ማንነት አስመላሽ ኮሚቴ ሰብሳቢ
ኮ/ል ደመቀ ዘውዱ
ለፈጣንና አዳዲስ መረጃዎች
@GafatStudio
454 viewsÑäťňāêł Ŧãmïřű, 06:49