Get Mystery Box with random crypto!

ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ

የሰርጥ አድራሻ: @ortodoxtewahedo
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 47.96K
የሰርጥ መግለጫ

ይህ ቻናል የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ዶግማንና ቀኖናን ትውፊትን እንዲሁም አስተምሮን የጠበቁ የተለያዩ የሚያስተምሩ ነገሮች ይለቀቁበታ፡፡ በተጨማሪ በ youtube #subscribe በማድረግ አገለግሎቱን ይደግፉ።
‹‹ከትውልዱ ማን አስተዋለ››
ት.ኢሳ 58÷3
https://youtu.be/csxxAMGtC4I
ለመቀላቀል
http://t.me/ortodoxtewahedo

Ratings & Reviews

4.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 9

2023-05-04 07:31:14 በማኅበረ ካህናትና ምእመናን ስም በጅማ ከተማ የተከናወነው ሕገወጥ ስብሰባ እንደማይወክለው የሀገረ ስብከቱ ጽ/ቤት አስታወቀ።

ሚያዚያ 25 ቀን 2015 ዓ.ም (ተ.ሚ.ማ /አዲስ አበባ)

በማኅበረ ካህናትና ምእመናን ስም በጅማ ከተማ የተከናወነው ሕገወጥ ስብሰባ ከሀገረ ስብከቱ እውቅና ውጪ እንደሆነ እና ሀገረ ስብከቱን እንደማይወክል የሀገረ ስብከቱ ጽ/ቤት አስታወቀ።

ፕራይም በተባለ ሚዲያ ዘጋቢነት "በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በጅማ  ሀገረ ስብከት የካህናት እና የምዕመናን ህብረት በወቅታዊ ጉዳይ ላይ ተወይቷል።" በሚል በተሠራጨው ዘገባ ዙርያ የጅማ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት በሰጠው መግለጫ ዘገባው የጅማ ሀገረ ስብከትን የማይወክልና ከሀገረ ስብከቱ እውቅና ውጭ በማኅበረ ካህናትና ምእመናን ስም የተከናወነ ሕገወጥ ስብሰባ መሆኑን አስታውቋል።

የጅማ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት ተከናወነ ለተባለው ሕገወጥ ስብሰባ ፈጽሞ ፈቃድ ያልሰጠና እንደማያውቀውም ጭምር በመግለጽ ያለ መደበኛው መዋቅር ለተከናወነው ለዚህ ሕገወጥ ስብሰባ የሚድያ ሽፋን የሰጠውን ፕራይም ሚድያን (Prime Media) በሕግ እንደሚጠይቅ አስታውቋል።

ሀገረ ስብከቱ በቅዱስ ሲኖዶስ የተመደቡለትና ላለፉት 23 ዓመታት ሲያገለግሉ የቆዩ አባት ብጹዕ አቡነ እስጢፋኖስ የጅማ፣ የየም፣ የኮንታ፣ የዳውሮ፣ የሰሜን ጎንደር አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል እያሉ እና በኢፌድሪ ጠቅላይ ሚንስትር ዶ/ር ዓብይ አህመድ እና በብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት አቀራራቢነት በተደረሰው 10 የስምምነት ነጥቦች መሠረት ህገ ወጥ ሲመት የተፈፀመላቸው መነኮሳት  በሙሉ ወደ ቤተ ክርስቲያኒቱ ተመልሰው በቤተ ክርስቲያኒቱ ሕግና ሥርዓት መሠረት ብቻ በተደረሰው ስምምነት ላይ የተመሠረተ አካሄድ እንዲሄዱ በቁርጠኝነት ያስተላለፉትን ውሳኔ ወደጎን በመተው በሕገወጥ መንገድ ከተሾሙት መካከል "አባ ሚናስ" የተባሉ ለሀገረ ስብከቱ እንደተመደቡለትና ለእሳቸውም አቀባበል ለማድረግ በዝግጅት ላይ መሆናቸው በስብሰባው እንደተገለጸ ሀገረ ስብከቱ ደርሶበታል።

በመሆኑም በጅማ ሀገረ ስብከት የምትገኙ ካህናትም ሆነ ምእመናን ይህ በሕገወጥ መንገድ በጅማ ሀገረ ስብከት ማኅበረ ካህናትና ምእመናን ስም የተከናወነው ሕገወጥ ስብሰባ ሀገረ ስብከቱንና በጅማ የሚገኙ ማኅበረ ካህናትንና ምእመናንን የማይወክል መሆኑን እናሳውቃለን ሲል የጅማ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት አስታውቋል።

@ortodoxtewahedo
620 viewsedited  04:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-02 19:29:23
2.9K views16:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-02 14:16:13 “እግዚአብሔር ሕዝቤን ስለሚያስቱ ነቢያት እንዲህ ይላል፤ በጥርሳቸው ሲነክሱ በሰላም ይሰብካሉ፤ በአፋቸው ግን አንዳች በማይሰጥ ሰው ላይ ሰልፍን ያስቡበታል።”

  — ሚክያስ 3፥5

@ortodoxtewahedo
3.4K viewsedited  11:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-02 05:36:03
እንኳን ለሊቀ ሰማዕታት ቅዱስ ጊዮርጊስ የእረፍት በዐል በሰላም አደረሳችሁ።

ሰማዕቱ አባቶቻችንን በአድዋ ላይ ረድቶ ጣሊያንን እንዳስወጣ እኛንም ሀገራችንንም ካለንበት ችግር ከእውነት እና እውነተኞች ጋር ቆሞ ነፃ ያውጣልን።

@ortodoxtewahedo
3.3K viewsedited  02:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-02 05:34:46
የታላቁ ሰማዕት የቅዱስ ጊዮርጊስ ክብረ በዓል በጥንታዊው እና ታሪካዊው በጋሞ ዶርዜ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስትያን በደምቀት ተከብሮ ውሏል!!

@ortodoxtewahedo
3.0K views02:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-01 03:26:10
#23
#የአራዳው ንጉሥ
#የልዳው ኮከብ
#ጦረኛው ሰማዕት
#የኢትዮጵያ ገበዝ
ዛሬም ከኛ ጋር ነው::

መልካም ዕለተ ይኹንልን

#መልካም ቀን

#ባለ ማዕተቦችን ወደዚህ
ግሩፕ ይጋብዙ

ለመቀላቀል
@ortodoxtewahedo
3.7K views00:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-29 21:04:58 በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን

ጉዳዩ፡- በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤ/ክ የፊታችን ግንቦት 2015 ዓ. ም. በሚካሄደው የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ ላይ ጳጳሳት እንዳይሾሙ ስለ መጠየቅ

በቅርቡ መንግሥታዊው ሥርዐት ፈጥሮት የነበረው ቤተ ክርስቲያናችንን የመከፋፈልና የማዳከም ተግባር ምን ያህል አደጋ ፈጥሮ እንደ ነበር ሁላችንም የምናስታውሰው ነው፡፡ ከፊታችን ግንቦት በሚኖረው የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ አዳዲስ ኤጲስ ቆጶሳት እንዲሾሙ ከፍተኛ ፖለቲካዊ ግፊትና ጫና እየተደረገ እንደሆነ እንሰማለን፡፡ በሕገ ወጡ ሲመት ተሳትፈው ከነበሩትም በሲመቱ ውስጥ እንዲካተቱ ከፍ ያለ ፖለቲካዊ ፍላጎትና ግፊት መኖሩ ይሰማል፡፡ 

እኛ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤ/ክ ምእመናን ይህ በፊታችን ግንቦት 2015 ዓ. ም. ላይ እንዲደረግ እየታሰበ ያለው ሲመተ ኤጲስ ቆጶሳት ለቤተ ክርስቲያናችን የማይበጅ ስለሆነ ቢያንስ ወደ ቀጣዩ ዓመት እንዲተላለፍ ቢደረግ ስንል እንጠይቃለን፡፡ ይህን ከምንልባቸው ብዙ ምክንያቶች መካከልም፡-

1)    በቅርብ ጊዜ በተካሄደው ሕገ ወጥ ሲመት የተሳተፉት በቤተ ክርስቲያን ቀኖና መሠረት እንኳንስ ወደ ኤጲስ ቆጶስነት እንዲመጡ ሊደረጉ ይቅርና የተሳተፉባቸው ተግባሮች ከክህነትም የሚያሽሩ ከባድ ኢክርስቲያናዊ ተግባራት በመሆናቸው (በመማለጃ ኤጲስ ቆጶስ የተሾመ ይሻር፤ በዚህ ዐለም መኳንንት [ለሹመት] ቢረዳ ከእነርሱም ዘንድ ለቤተ ክርስቲያን ቢሾም ይሻር፤ እርሱና ግብረ አበሮቹ ሁሉ ይለዩ፡፡ . . . በተንኮል ቢሾምም የተለየ ነው፡፡ በእናንተም ዘንድ እንደ አረማዊ ይሁን፡፡ ከእግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያን ይለይ፡፡ ፍትሐ ነገሥት 5 አንቀጽ ቁ. 173-176)      

2)    ባለፈው ተሞክሮ ያልተሳካውና ለጊዜውም ቢሆን ቆም ያለ የመሰለው ፈተና መልኩን ቀይሮ በውጭ የታጣውን በውስጥ የማስፈጸም ነገር ላለመኖሩ እርግጠኛ መሆን ስለማይቻል፤

3)    በባለፈው ሲመት የተሳተፉት ግለሰቦች በእነርሱ ሕገ ወጥ ተግባር ምክንያት ከ50 በላይ ክርስቲያኖች እንዲገደሉና ብዙ ደም እንዲፈስ ያስደረጉ በመሆናቸው፤ ከዚህ የተነሣም ከእነዚህ መካከል ይሾም የሚባል ቢኖር ይህን ሰው በአባትነት ለመቀበል በእጅጉ የምንቸገር በመሆኑና በቤተ ክርስቲያን አንድነት ላይም ችግር ሊፈጥር ስለሚችል፤ 

4)    አገራችን አሁን ካለችበት ተጨባጭ ሁኔታ አንጻር፤

ስለዚህ ቅዱስ ሲኖዶስ የዚህን ዐመት ሲመተ ኤጲስ ቆጶሳት ጉዳይ እንዲያስተላልፈው ስንል በልጅነት መንፈስ እንጠይቃለን፡፡ 

ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ሲኖዶሳዊት መሆኗ የታወቀ ነው፣ ሲኖዶሳዊት ማለት ደግሞ ከቅዱስ ፓትርያርኩና ብፁዓን ሊቃነ ጳጳስት ጀምሮ እያንዳንዱ ምእመን ያለባት የሁላችን የሆነች ቤተ ክርስቲያን እንደ መሆኗ፣ ብፁዓን አባቶቻችን የባለፈውን ፈተና ከልጆቻችሁ ጋር በመሆን እንደ ተወጣችሁት አሁንም እኛ ልጆቻችሁ ለቤተ ክርስቲያናችን ያለንን ጭንቀት በአባትነታችሁ እንደምትረዱንና ጥያቄያችንን እንደምትቀበሉን እናምናለን፡፡ 

ቡራኬያችሁ አይለየን!
1.9K views18:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-29 21:04:58 https://chng.it/rqvLSr7d


በመፈረም እንተባበር!!
1.7K views18:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-29 00:06:13


ወይቤላ ምሁሩ ወመሀሩ
ለዘየአምን ወንጌለ መንግስተ ሰማያት

ለመቀላቀል @ortodoxtewahedo

2.9K views21:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-28 23:32:56
ጎሳ ልብየ ቃለ ሰናይ/2/
ወአናአእድ ቅዳሴሐ ለማርያም /2/
እኔስ የማርያምን ቅዳሴዋን እናገራለሁ
እንደ አባቴ ዳዊት በበገና እዘምራለሁ
ቀን ከለሊት ሳልል በምስጋና እተጋለሁ
የሀጢያቴ ቁስል እንዲፈወስ እጮሃለሁ
ምርኩዜን ነሽና እመቤቴ ባንቺ እመካለሁ

ኦ እመቤቴ በእውነት እንወድሻለን
የእውነት መዳን ክርስቶስን ወለድሽልን
ምክንያተ ድህነት ሆይ ድንግል ማርያም የአምላክ መገኛ
በማላጅነትሽ በመታመን እንጮሀለን እኛ
ምህረትን አሰጭን ኪዳነ ምህረት የአለም መዳኛ

ስለቸርነትሽ እመቤቴ ለኔ እናቴነሽ
ስለንግስትነትሽም እመቤቴነሽ
ዝናባት ሳያጠጡት አየራት ሳያሳድጉት
ሰማያዊ እንጀራ የሰጠሽን ቤተለማዊት
ቅድስተ ቅዱሳን የዋህ መርከብ የአምላክ እናት

ቃና ዘገሊላ በሰርጉ ቤት በዚያ ተገኝተሽሳለሽ
ውሃውን ወደ ወይን ባንቺ ምልጃ እንዳስለውጥሽ
ዛሬ የኔ ሕይወት ወይኑ አልቆ ባዶ ሆኖልና
አንቺ የአምላክ እናት ንፅህት ቅድስት ርህርዕተ ህሊና

@ortodoxtewahedo
2.8K viewsedited  20:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ