Get Mystery Box with random crypto!

ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ

የሰርጥ አድራሻ: @ortodoxtewahedo
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 47.96K
የሰርጥ መግለጫ

ይህ ቻናል የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ዶግማንና ቀኖናን ትውፊትን እንዲሁም አስተምሮን የጠበቁ የተለያዩ የሚያስተምሩ ነገሮች ይለቀቁበታ፡፡ በተጨማሪ በ youtube #subscribe በማድረግ አገለግሎቱን ይደግፉ።
‹‹ከትውልዱ ማን አስተዋለ››
ት.ኢሳ 58÷3
https://youtu.be/csxxAMGtC4I
ለመቀላቀል
http://t.me/ortodoxtewahedo

Ratings & Reviews

4.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 7

2023-05-19 21:09:46
"እኔ የሃይማኖት መምህር ነኝ፤ በተከሰስኩበት ወንጀል አልተሳተፍኩም"

መምህር ኃ/ማርያም ዘውዱ ከ4 ጠበቆቻቸው ጋር የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ 1ኛ ይግባኝ ወንጀል ችሎት ዛሬ ረፋድ ቀረቡ።

ግንቦት 4/2015 ዓ᎐ም ባሕር ዳር ከተማ ተይዘው ወደ አዲስ አበባ ፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን ወንጀል ምርመራ የመጡት መምህር ኃ/ማርያም ግንቦት 7 በነበረ ችሎት ፖሊስ በጠየቀው መሠረት ፍርድ ቤቱ የ14 ቀናት የምርመራ ጊዜ መፍቀዱ ይታወሳል።

ሆኖም ትናንት ግንቦት 10/2015 ዓ᎐ም በጠየቁት ይግባኝ መሠረት ዛሬ ግንቦት 11/2015 ዓ᎐ም ረፋድ 4 ሰዓት ላይ የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ 1ኛ ይግባኝ ወንጀል ችሎት ቀርበዋል።

በችሎቱ 4 ጠበቆች የቆሙላቸው ሲሆን ክሱ "በማኅበራዊ ሚዲያ ሁከትና ብጥብጥ ለመፍጠር ሕገ መንግስቱንና ሕገ መንግስታዊ ስርዓቱን በኃይል ለመናድ᎐᎐᎐" የሚል ነው። ለዚህም ማስረጃ ለማምጣት የሚያስፈልገው አትሞ ማምጣት ብቻ ነው። ይህንን ለማድረግ 14 ቀናት መቀጠሩ አግባብ አይደለም።" በሚል ክርክራቸውን አቅርበዋል።

መምህር ኃ/ማርያም ዘውዱ በበኩላቸው" እኔ የሃይማኖት መምህር ነኝ፤በተከሰስኩበት ወንጀል አልተሳተፍኩም፤ በአሁኑ ሰዓት ወሎ ዩኑቨርስቲ በሰጠኝ እድል በባህር ዳር ዩኒቨርስቲ 2ኛ ድግሪ ተማሪ ነኝ።እዚህ በመሆኔ ፈተና እና መሰል ጉዳዮች እያለፉኝ ነው፤ይህም 1 ተጨማሪ ዓመት የሚያስደግመኝ በመሆኑና ብፈለግም የታወቀ አድራሻ ያለኝ በመሆኑ የዋስትና መብት ይሰጠኝ።" ሲሉ ሃሳባቸውን ገልጸዋል።

ፍርድ ቤቱም ግራ ቀኙን ከሰማ በኋላ ለሰኞ ግንቦት 14/2015 ዓ᎐ም 3 ሰዓት የፖሊስ ምርመራ መዝገብ ለማየት እና በዛው ቀን 5 ሰዓት ከሁለቱ ወገን በቀረበው መከራከሪያ ላይ ውሳኔ ለመስጠት ቀጠሮ ሰጥቷል።

@ortodoxtewahedo
2.6K viewsedited  18:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-16 09:49:07 የአለም የመዝናኛ ሚድያዎች ላይ በሚሊየን የሚከተል ኦርቶዶክሳዊ ቤተ ክርስትያን በዚ ባለችበት የስደት ዘመን አንድ ላይ ለመሰባሰወብ ምን ከበደን ። መረጃ ወሳኝ ነው ለሁሉም ነገር በአንድ ተሰባስበን መረጃ እንለዋወጥ ሁላችንም ሰዎችን ወደዚ ግሩኘ እናምጣ።

በዚ ግዜ ያልታዘዝን መቼ ልንታዘዝ ነው።

ለመቀላቀል ይህን ይጫኑ

@orthodoxtewahedo
2.4K viewsedited  06:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-16 09:44:41
መምህር ኃይለ ማርያም ከባሕርዳር ተይዘውጰወደ አዲስ አበባ መምጣታቸው ታውቋል። ይሁን እንጂ እስካሁን ፍርድ ቤት አልቀረቡም።

@orthodoxtewahedo
2.3K viewsedited  06:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-16 09:44:27
ሰሞኑን በወሀብያ ሙስሊም ሚዲያዎች ይህ ፎቶ ሲዘዋወር ነበር። በሐድያም አንድ ቄስ እስልምናን ተቀበለ ተብሎ ወሬው ተናፈሰ።
ነገር ግን የሀድያ፣ ሥልጤና እና ሆሣዕና ሀገረ ስብከት ይህ ግለሰብ በሀገረ ስብከቱ ያልነበረ አዲስ ገጸ ባሕሪ መሆኑን ገለጸ።
ይህንን ሙስሊም ግለሰብ ወሀብያዎች ጋቢና ቆብ በማልበስ ወደ እስልምና ገባ አሉ። ይህ ወደ ክርስትና የሚሄደውን ሙስሊም ለመግታት የተፈጸመ ቁማር መሆኑን እንድታውቁት።

ድምፀ ተዋሕዶ

@orthodoxtewahedo
1.7K viewsedited  06:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-16 09:43:44 ዘመቻ

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክሰሰ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሚዲያ እስካሁን ድረስ በመምህሩ መታፈን ምንም አላለም። ይህም በመምህሩ የግፍ ግዞት ውስጥ ቤተ ክህነቱ እጁ እንዳለበት ታላቅ ማሳያ ነው። የቤተ ክርስቲያኗ ሚዲያ ለአብነት መምህራን ድምፅ መሆን ካልቻለ ግቡ ሌላ እንደሚሆን ምንም ጥርጥር የለውም። ድምፀ ተዋሕዶ በመምህሩ እሥራት እጃቸው ያለበትን የቤተ ክህነት ሰዎች በሚገባ አውቋል። በመሆኑም እስከሚመጣው አርብ ድረስ የቤተ ክርስቲያኗ ሚዲያ በግፍ ለታሠሩት መምህር ድምፅ መሆን ካልጀመረ፤
1, በዩቱዩብ የምንከታተል ኦርቶዶክሳውያን ዩቱዩቩን unsubscribe በማድረግ ዘመቻ የምናደርግ መሆኑን
2, ካልተገመቱት ሊቀ ጳጳስ ጀምሮ እስከ ማኅበራት መሪዎች ድረስ በእሥራቱ እጃቸው ያለበትን ግለሰብ በስም ለሚዲያ የምናውል መሆኑን እናሳውቃለን።

ይህንን ዘመቻ ለመቀላቀል ዝግጁ ናችሁ?
1.6K views06:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-16 09:39:20
@orthodoxtewahedo
1.4K viewsedited  06:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-16 09:39:18 በእየቀኑ አንድ ተዊት በማድረግ ለቤተ ክርስቲያን ድምጽ እንሁን https://iotaethio.org/clicktotweet/
1.4K views06:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-16 08:58:15 መምህራን እውነትን በጥራት ይናገሯታል። የሁሉ ነገር መለኪያቸው ቃለ እግዚአብሔር ነው። ከቃለ እግዚአብሔር ያፈነገጠ አካሄድ ካዩ ንጉሡንም፣ ጳጳሱንም፣ ወታደሩንም፣ ፓትርያርኩንም፣ ፖለቲከኛውንም ተው ብለው ይመክራሉ። ምክራቸውን አልሰማ ሲል በአደባባይ ስሕተቱን ለሰው ሁሉ ይገልጡበታል። (ይህንንም የሚያደርጉት በስሕተቱ ሌሎች ምእመናን አብረው እንዳይሳሳቱና ከእግዚአብሔር መንግሥት እንዳይለዩ በማሰብ ነው)። የመምህራን መመሪያ ቃለ እግዚአብሔር ነው። ትኩረታቸው እግዚአብሔር ምን አለ? የሚለውን ማወቅና ማሳወቅ ላይ ነው።

የያዙትን እውነት በማሰር፣ በማሰቃየት፣ በማሳደድ፣ በመግደል ማስተው አይቻልም። እውነትን የያዘ ሰው ከእግዚአብሔር ውጭ የሚፈራው ምድራዊ ኃይል የለም። መምህራን ሰውን ሁሉ ይወዳሉ። መምህራን ሰውን ሁሉ ያከብራሉ። ሰውን ሲወዱ ግን ከፍቅረ እግዚአብሔር ቀጥሎ ነው። የሚወዱት ሰው ቃለ እግዚአብሔርን ሲቃወም ካዩት ይቃወሙታል። ምክንያቱም ማንኛውም ሰው ከእግዚአብሔር በታች ነውና። ልክ እንደ መምህራቸው እንደ ክርስቶስ ኃጢአትን እንጂ ኃጢአተኛን አይጠሉም። በተቻላቸው አቅም ሰውን ሁሉ ከኃጢአት እስር ቤት ለማውጣት ይጥራሉ።

የመምህራን መፈክራቸው እንደ ቅዱስ ጳውሎስ እመኒ ሐዮነ ለእግዚአብሔር ነሐዩ። ብንኖር ለእግዚአብሔር እንኖራለን። ወእመኒ ሞትነ ለእግዚአብሔር ንመውት። ብንሞትም ለእግዚአብሔር እንሞታለን ማለት ቃለ እግዚአብሔርን መስክረን እንሞታለን የሚለው ነው። የመምህራን የኑሮ መመሪያቸው እስካለን ድረስ ቃለ እግዚአብሔርን ጠብቀን እናስጠብቃለን የሚል ነው። መኖርን የሚተረጉሙት እንደ እግዚአብሔር ቃል መጓዝ ብለው ነው።

ቃለ እግዚአብሔርን በአደባባይ የሚቃወሙ ሰዎች እያሉ ዝም ማለት ለመምህራን ሞት ነው። መምህር ፍጡራንን ፈርቶ ፈጣሪ ለሰው ልጆች በቅዱሳኑ አድሮ የሠራው ዶግማና ቀኖና ሲሻር ዝም ካለ ይህ ገና መምህር አልሆነም ማለት ነው። እከብር ባይ ልቡናን ገና አልተወም ማለት ነው። መምህር ሆነው ሕገወጥነትን ካልተቃወሙማ ምኑን መምህር ሆኑታ!?

የኔታ ኃይለማርያም ሕገወጥነትን በመቃወማቸው፣ እውነትን በመመስከራቸው ነው የታሠሩት። ይህ ለእርሳቸው ክብር ነው። ለአሣሪዎች ግን ብረትን ብትመረኮዙት በእናንተው ይብስባችኋል። ስለዚህ ለራሳችሁ ስትሉ መምህራችንን ፍቷቸው።

የመምህራን መምህር ክርስቶስ ዝም አይልም።

በትር ማርያም አበባው


@orthodoxtewahedo
1.5K viewsedited  05:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-16 08:58:13 ትናንትም የነበረው፣ ዛሬም ያለው፣ ነገም ሆነ ለዘላለም የሚኖረው ለወገነኖቹ በመጽሐፍ እንዲህ ብሎ የተናገረውና እኛ ዛሬ የምናመልከው፣ አባት ብለን የምንጠራው እግዚአብሔር መሆኑን አንዘንጋ! በቤቱ አንቀልድ:-

መቃባያን ቀዳማዊ 13፣ 30-41
ክፉ ሥራ ሁሉ ቅሚያና ትዕቢት፥ ስስትም በአሳባቸው የተዘጋጀ ነው። ስለዚህም እግዚአብሔር ቸል አላቸው፣
ከተሞቻቸውንም ገለበጣቸው፤ እስከ መሠረታቸው ድረስ በእሳት ያቃጠላቸውም አሉ እስከ ዘለዓለም ድረስ ፈጽመው ጠፉ ከእነርሱ አንድ ስንኳ አልቀረም" 0ኀጢአት ታስረዋልና የዘለዓለም ፍርድ እስከሚሰ ጥባት እስክ ታላቋ የፍርድ ቀን ድረስ ይቈያሉ፤ በክፉ ሥራቸውም አሳዝነውኛልና አልምራቸውምº ይቅርም አልላቸውም" እኔም ቸል አልኋቸው፤ እንደዚሁም የኢየሩሳሌም ልጅ: በፍርድ ቀን አንቺ ጐስቋላ የኢየሩሳሌም ልጅ እንደእነርሱ ትታሰሪያለሽ፤ ሥራሽ ሁሉ ቅሚያና ኀጢአት፥ ዝሙትና ስስት፥ ሐሰት መናገርም፥
እኔም የማልወደው የስሕተትና የድጥ መንገድ ስለ ሆነ ተቈጥቼ በያዝሁሽ ጊዜ ምክንያት አታገኝምና። እኔ ለክብር አድርጌሽ ነበር፤ አንቺ ግን ራስሽን ለውርደት አደረግሽ፤ እኔ ለእኔ ብዬሽ ነበር፤ አንቺ ግን ለሌላ ሆንሽ። እኔ ለቅድስና አጭችሽ ነበር፤ አንቺ ግን ለዲያብሎስ ሆንሽ፤ እኔም እንደ ሥራሽ ክፋት እበቀልሻለሁ። ቃሌን ሁሉ ስላልሰማሽ፥ በወደድሁሽም ጊዜ ያዘዝሁሽን ትእዛዝ ስላልጠበቅሽ
የፈጠርሁሽ እግዚአብሔር እኔ ነኝና ክፉ በቀልን አበዛብሻለሁ፤ እንደ አንቺ ባሉ በኃጥኣንም ሁሉ ላይ እቈጣለሁ፤ እንደ ክፋታቸውም በፍርድ ቀን እከፍላቸዋለሁ።
ቃሌንም አልጠበቅሽምና፥ ፍርዴንም ቸል ብለሻልና አንቺንም ከእነርሱ ጋር እቀጣሻለሁ።

በልቡናችሁ እግዚአብሔርን መፍራት የሌላችሁ፥ ሰዶምና ገሞራ፥ ወዮላችሁ። በእሳተ ገሃነም ካንቺ ጋራ በአንድነት የሚፈረድባት እኅትሽ የኢየሩሳሌም ልጅ እንደዚሁ ወዮላት! ለዘለዓለሙ መውጫ ወደሌለበት ወደ ተዘጋጀው ወደ ገሃነም በአንድነት ትወርዳላችሁና ያንቺን ሥራ የሠሩ ሁሉ ወዮላቸው። ቃሌንና ትእዛዜን አልጠበቃችሁምና ቃሌንና ትእዛዜን ያልጠበቃችሁ አንቺና እርሷ, በፍርድ ቀን በአንድ
ነት ወደ ሲዖል ትወርዳላችሁ"
1.7K views05:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-15 21:34:33
"በሕግ አምላክ!"

☞በሀገሪቱ ሕግ ቢኖርም፥ ባይኖርም "በሕግ አምላክ ሊቁን አታንገላቱ" እንላለን!

☞አበው #ጳጳሳት፦ እናንተንም "በሕግ አምላክ" እንላለን፡፡ ሕግን ወደሰጠ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እንከሳችኋለን፡፡

#ምዕመናን፥ #ካህናት፥ #ሊቃውንት ሲንገላቱ ዝም ያላችሁ (ምኝታ የሞቃችሁ) አበው ጳጳሳት እግዚአብሔር ይዳኛችሁ! የጃችሁን አትጡ!

@orthodoxtewahedo
2.3K viewsedited  18:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ