Get Mystery Box with random crypto!

ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ

የሰርጥ አድራሻ: @ortodoxtewahedo
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 47.96K
የሰርጥ መግለጫ

ይህ ቻናል የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ዶግማንና ቀኖናን ትውፊትን እንዲሁም አስተምሮን የጠበቁ የተለያዩ የሚያስተምሩ ነገሮች ይለቀቁበታ፡፡ በተጨማሪ በ youtube #subscribe በማድረግ አገለግሎቱን ይደግፉ።
‹‹ከትውልዱ ማን አስተዋለ››
ት.ኢሳ 58÷3
https://youtu.be/csxxAMGtC4I
ለመቀላቀል
http://t.me/ortodoxtewahedo

Ratings & Reviews

4.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 6

2023-05-20 15:56:34
@ortodoxtewahedo
1.4K viewsedited  12:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-20 15:56:30
#ግንቦት_12

የመምህር ወመገስጽ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ የእረፍቱ ቀን፣ የአባታችን የጻድቁ አቡነ ተክለሃይማኖት ፍልሰተ አጽም እና የእናታችን ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ የቃልኪዳን ዓመታዊ ክብረ በዓል ነወ።

#ቅዱስ_ዮሐንስ_አፈወርቅ
ባሕረ ምስጢራት የሆነ የሰውን ፊት አይቶ የማያደላ "መምህር ወመገስጽ ዘኢያደሉ ለገጽ" (በርሱ ዘንድ ንጉሥ፣ ሐብታም፣ ደሃ፣ ነዳይ እኩል ነውና)፣ አፈ በረከት፣ አፈ መዐር (ማር)፣ አፈ ሶከር (ስኳር)፣ አፈ አፈው (ሽቱ)፣ ልሳነ ወርቅ፣ የዓለም ሁሉ መምሕር፣ ርዕሰ ሊቃውንት፣ ዓምደ ብርሃን (የብርሃን ምሰሶ)፣ የሐዲስ ኪዳን ዳንኤል፣ ሊቀ ዻዻሳት ዘበርትዕ (እውነተኛው)፣ ጥዑመ ቃል... እየተባለ የሚጠራው ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ እረፍቱ ነው።

#ቅድስት_ክርስቶስ_ሠምራ
ብፅዕት ቅድስት ክርስቶስ ሰምራ ሰይጣንን ከፈጣሪ ጋር ልታስታርቅ በሄደች ጊዜ ከሲኦል ቅዱስ ሚካኤል እየተራዳት ብዙ ነፍሳትን ያወጣችበት የቃልኪዳን በዓል ነው።

#አቡነ_ተክለሃይማኖት
የአባታቸንና የኢትዮጵያ ፀሐይ የፃድቁ አቡነ ተክለሃይማኖት ግንቦት 12 ከደብረ አሰቦ ወደ ደብረ ሊባኖስ አጽማቸው የፈለሰበት (ፍልሰተ አጽም) ይከበራል።

አምላከ ቅዱሳን በቅዱሳኑ ጸሎት ልመናና ቃልኪዳን ሀገራችን ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ከጭንቀትና ከመከራ ይጠብቀን።.

@ortodoxtewahedo
1.6K viewsedited  12:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-20 14:27:51
@ortodoxtewahedo
1.5K views11:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-20 14:27:19 ❖ግንቦት 12 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት=
1.ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ (የዓለም ሁሉ መምሕር)
2አቡነ ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት ጻድቅ (ፍልሠታቸው)
3.ቅድስት እናታችን ክርስቶስ ሠምራ (ቃል ኪዳን
የተቀበለችበት)
4.አባ አብርሃም ዘደብረ ሊባኖስ
5.ቅዱስ ዕንባቆም ነቢይ
6.እስክንድር ንጉሠ ኢትዮዽያ
7.ቅዱስ መስቀል (የተአምር በዓሉ)
8.አባታችን ያሬድ (የማቱሳላ አባት)
9.ቅዱስ ሚናስ ዲያቆን❖ወርኃዊ በዓላት
1፡ ቅዱስ ሚካኤል ሊቀ መላእክት2፡ ቅዱስ ድሜጥሮስ
3፡ ቅዱስ ማቴዎስ ሐዋርያ
4፡ ቅዱስ ቴዎድሮስ በናድሌዎስ
5፡ አባ ሳሙኤል ዘዋልድባ
6፡ ቅዱስ ላሊበላ
7፡ ቅድስት መስቀል ክብራ

++"+ እናንተ የምድር ጨው ናችሁ . . . እናንተ የዓለም
ብርሃን ናችሁ:: በተራራ ላይ ያለች ከተማ ልትሠወር
አይቻላትም:: መብራትንም አብርተው በዕንቅብ በታች
አይደለም እንጂ በመቅረዙ ላይ ያናሩታል:: በቤት ላሉት
ሁሉም ያበራል::
መልካሙን ሥራችሁን አይተው በሰማያት ያለውን
አባታችሁን እንዲያከብሩ ብርሃናችሁ እንዲሁ በሰው ፊት
ይብራ:: +"+ (ማቴ.
5:13-16)

<<< ወስብሐት ለእግዚአብሔር >>>

ምንጭ ዝክረ ቅዱስ ዳዊት

@ortodoxtewahedo
1.4K viewsedited  11:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-20 14:27:06 ✞✞✞ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ
አምላክ ፡፡ አሜን ፡፡ ✞✞✞

❖ እንኳን አደረሳችሁ ❖

❖ ግንቦት 12 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት

+° ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ °+

=>ለቤተ ክርስቲያን የብርሃን ምሰሶ ስለሆነላት ስለ ታላቁ
ሐዋርያዊ ሊቅ ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ ምን እላለሁ?
ምንስ
እናገራለሁ? እንደ እኔ ያለ ኃጥእ: ለባሴ ሥጋና ገባሬ ንስሃ
ስለሱ ሊናገር አይቻለውምና:: አባቶቻችን እንደ ነገሩን ስለ
አፈ ወርቅ ለመናገር አፈ ወርቅ መሆን ያስፈልጋል:: ግን
እስኪ በቅዱሱ አባት ምልጃ ጥቂት ልሞክር::

<< ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ ማን ነው? >>

+ነገዱ ከሶርያ: የተወለደው በ347 ዓ/ም በእስክንድርያ
ሲሆን አባቱ አስፋኒዶስ እናቱ ደግሞ አትናስያ ይባላሉ::
እነርሱ
ደግ ቢሆኑ ይህንን እንቁ ልጅ እግዚአብሔር ሰጣቸው::
ዮሐንስ ለክርስቲያን እንደሚገባ በትምሕርትና በጥበብ
አደገ:: ገና
በሕጻንነቱ ወደ ግሪክ ሔዶ የዘመኑን ሳይንስ (ፍልስፍና)
ከአፉ እስከ ገደፉ ተምሮ ተመልሷል::

+ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅን ለየት ከሚያደርጉት ነገሮችም
አንዱ ይሔው ነው:: በዘመናዊም ሆነ በመንፈሳዊ
ትምሕርት ይህ
ቀረህ የማይሉት ሊቅ የሆነው ገና በ15 ዓመቱ ነበር:: በ2
ወገን የተሳለ ሰይፍ በመሆኑ ስንኳን በሕይወተ ሥጋ እያለ
ዛሬም ለንፉቃን ትልቅ የራስ ምታት ነው::

+ቅዱሱ ገና በ16 ዓመቱ ሃብት: ንብረት: ውበት: ክብርና
እውቀት የሞላለት ቢሆንም ያለውን ሁሉ ለነዳያን ሰጥቶ
መጻሕፍትን ብቻ ሰብስቦ ከባልንጀራው ቅዱስ ባስልዮስ
ጋር በርሃ ገባ:: ሰውነቱን በጾምና በጸሎት እየቀጣ በበርሃ
ሲኖር
ወንጌላዊው ቅዱስ ዮሐንስና ሊቀ ሐዋርያት ቅዱስ
ዼጥሮስ ወደ እርሱ መጡ::
ሊቀ ሐዋርያት የመንግስተ ሰማያትን መክፈቻ ስልጣን
ቅዱስ ዮሐንስ ደግሞ ወንጌሉን ሰጥተው ተሰወሩት::

+ከዚህች እለት በኋላ ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ ባሕረ
ምስጢራት ሆነ:: ብሉይ ከሐዲስ: ከኦሪት ዘፍጥረት እስከ
ራዕየ
ዮሐንስ ድረስ በአንድምታ ትርጉዋሜ ተነተናቸው:: በተለይ
ሐዲስ ኪዳንን እየመላለሰ አመሰጠረው:: ቅዱስ ሕሊናው
ሳይታክት:
ንጹሕ እጆቹ ሳይዝሉ የጻፋቸው ድርሳናት: መልዕክታትና
ትርጉዋሜያት ቢቆጠሩ አሥር ሺህ ሞሉ:: በእውነት ለዚህ
አንክሮ
ይገባል! የሚገርመው ይህን ሁሉ ሲሰራ እድሜው ገና
ለጋ: ማዕርጉም ዲቁና ነበር::

+ከዚህ በኋላ በእግዚአብሔር ትእዛዝ ቅስና ተሹሞ
በስብከተ ወንጌል ብዙ ቦታዎችን አዳረሰ:: በቅድስናው
ወደውታልና
የቁስጥንጥንያ ፓትርያርክ አድርገው ሾሙት:: አፈ ወርቅ
ሲናገርም ሆነ ሲያስተምር እንኳን የሚያወራ ኮሽ የሚል
የለም::
ከጣዕመ ትምሕርቱ የተነሳ ሕዝቡ በተደሞ ይሰሙት ነበር::

+ሲያስተምር ምድራዊው ሰው ይቅርና ልዑላኑ መላእክት
ተሰብስበው ያደንቁት ነበር:: አንዴም እመቤታችን በሕዝብ
መካከል "
አፈ-ወርቅ" ብላ ጠርታዋለች:: ለዛም ነው አፈ-ወርቅ
የሚባለው:: ቅዱሱ በሥልጣነ ቃሉ መልዐከ ሞትን ገስፆ
10 ዓመት
አቁሞታል::

+ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ ለሰው ፊት አያደላም:: በርሱ
ዘንድ ንጉሥና ደሃ ነዳይ እኩል ነው:: ለሞት ያበቃውም
ይሔው
ነበር:: ምክንያቱም የወቅቱ ንግስት አውዶክስያ ያንዲት
ድሃ መበለትን መሬት ቀምታ አልመልስም በማለቷ መክሮ
አወገዛት::
እርሷ ግን ከኃጥአንና መናፍቃን ጋር መክራ 2 ጊዜ
አጋዘችው::

+በተሰደደበት ፍሬ አፍርቶ: አስተምሮና አሳምኖ በ407 ዓ/
ም አርፏል:: ቤተ ክርስቲያንና ምእመናን ሳይጠግቡት
እንደናፈቁት በ60 ዓመቱ አጡት:: በወቅቱ ታላቅ ሐዘንና
ለቅሶ ተደረገ::

+አንድ ቀን የዘመኑ ደግ ንጉሥ አርቃድዮስ ግብር አገባ
(ግብዣ አዘጋጀ):: በዚያች ሌሊት ደግሞ ቅዱሱ ሊቅ
ታጥቆ ሲጸልይ
ሳለ: አባ ማርዳሪ የሚባል ጻድቅ ደግሞ ከሰማይ 12ቱ
ሊቃነ መላእክት (እነ ቅዱስ ሚካኤል) በግርማ ሲወርዱ
ተመለከተ::

+ደንግጦ "ወዴት ናችሁ ጌቶቼ" ቢላቸው "ቁስጥንጥንያ:
ወደ ዮሐንስ አፈ ወርቅ እንሔዳለን:: እርሱ እመቤታችንን
እንደሚያመሰግናት ጌታ ነግሮናልና" አሉት:: "እባካችሁ
እኔም የአፈ ወርቅ ምስጋናው እንገለጥልኝ መርቁኝ"
አላቸው::
ሊቃነ መላእክቱም መርቀውት ጐዳናቸውን ቀጠሉ::

+በማግስቱ በቤተ መንግስት ውስጥ ሊቃውንቱ:
መሳፍንቱ: ዻዻሳቱ: ሕዝቡ ሁሉ ተሰብስበው ከድግሱ
በሉ:: ቅዱስ ዮሐንስ አፈ
ወርቅ ግን በመንበሩ ተቀምጦ ነበር እንጂ አልበላም::
ድግሱ ሲጠናቀቅ ንጉሡ አርቃድዮስ ሊቁን "ጥያቄ አለኝ"
ብሎ በጉባኤ
መካከል ጠየቀው::

+"ምነው ወንጌላዊ ማቴዎስ 'ኢያዕመራ ዮሴፍ እስከ አመ
ወለደት ወለደ ዘበኩራ-የበኩር ልጇን እስክትወልድ ድረስ
አላወቃትም'
ማለቱ (ማቴ. 1:25) ስለ ምን ነው?" ቢለው ቅዱሱ
ተነስቶ: በመንፈስ ቅዱስ ተቃኝቶ ይተረጉምለት ጀመር::

+"ድንግል ማርያም ንጹሕ ብርሌን ትመስላለች:: ብርሌ
የተለያየ ቀለም ያለው ፈሳሽ ቢያስገቡበት ቀለሙ አብሮ
ይቀያየራል::
እመቤታችንም ጌታን ጸንሳለችና ሕብረ መለኮቱ ሲለዋወጥ
መልኳ አብሮ ሲለዋወጥ እያየ ዮሴፍ ይደነግጥ ነበር::

+'እርሷ ማን ናት? በማሕጸኗ ያለውስ ማን ነው' እያለ
ይጨነቅ ነበር:: ጌታን ከወለደች በኋላ ግን አንድ ሕብረ
መልክ
ሆናለችና:: አስቀድሞ ማን እንደ ነበረች አላወቀም::

+አሁን ግን እርሷም ወላዲተ አምላክ: ልጇም አምላክ
ዘበአማን መሆኗን አወቀ ማለት ነው" እያለ ሲተረጉም
ሰምተው ሁሉም
ሲያደንቁ: በዚያ የነበረች ስዕለ አድኅኖ "አፈ ወርቅ! ልሳነ
ወርቅ! አፈ በረከት!" ስትል ተናገረች::

+ያን ጊዜ አርቃድዮስ የወርቅ ልሳን በሊቁና በስዕሏ ላይ
አደረገ:: አፈ ወርቅ ግን ባጭር ታጥቆ "እሰግድ ለኪ!
እሰግድ
ለኪ! ወእዌድሰኪ . . ." ብሎ ዛሬ በተአምረ ማርያም
የምናውቀውን ምስጋና ሰተት አድርጐ አደረሰላት:: ይህንን
ምስጋናም
ሊቃነ መላእክቱ ሰምተው እያደነቁ ወደ ሰማይ
ወጥተዋል::

+ሊቁ ባረፈ በ35 ዓመቱ: በትንሹ ቴዎዶስዮስ ዘመን:
ሥጋው ፈልሷል:: ወደ ቁስጥንጥንያ ሲደርስም ከናፍቆት
የተነሳ ታላቅ
ዝማሬና እንባ ተደርጓል:: አፈ ወርቅም ቀና ብሎ ሕዝቡን
ባርኳል::

ቅዱሱ ሲጠራ እንዲሕ ነው:-
*ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ
*አፈ በረከት
*አፈ መዐር (ማር)
*አፈ ሶከር (ስኳር)
*አፈ አፈው (ሽቱ)
*ልሳነ ወርቅ
*የዓለም ሁሉ መምሕር
*ርዕሰ ሊቃውንት
*ዓምደ ብርሃን (የብርሃን ምሰሶ)
*ሐዲስ ዳንኤል
*ሊቀ ዻዻሳት ዘበርትዕ (እውነተኛው)
*መምሕር ወመገስጽ ዘኢያደሉ ለገጽ
*ጥዑመ ቃል - - -

+እግዚአብሔር ከቅዱሱ በረከት አብዝቶ: አብዝቶ: አብዝቶ
ይክፈለን::

+ዳግመኛ በዚህ ቀን ታላቁ ጻድቅ አቡነ ተክለ ሃይማኖት
ሥጋቸው ፈልሷል:: ይሕ የተደረገው ጻድቁ ከረፉ ከ56
ዓመታት
በኋላ ነው:: በዕለቱም ድንቅ ድንቅ ተአምራት
ተፈጽመዋል::

+እናታችን ርሕርሕቷ ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ ደግሞ
በዚሕ ቀን ስሟን ለጠራና መታሠቢያዋን ላደረገ የምሕረት
ቃል ኪዳን
ተቀብላለች::

❖ቸር አምላካቸው ከሁለቱም ብሩሃን ቅዱሳኑ ክብር
ያድለን::
1.6K views11:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-20 06:51:38
@ortodoxtewahedo
2.3K views03:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-20 06:51:29 ጠቅላይ ሚንስትሩ የቤተ ክርስቲያን ወዳጅ ወይስ አሳዳጅ?
****
ዛሬ
ዓርብ ግንቦት 11 ቀን 2015 ዓ.ም. በዋለው የሲኖዶስ ጉባኤ በሕገ ወጡ ሹመት ጉዳይ ሳይስማሙ ለሰኞ ተቀጥሮ አጀንዳው አድሯል። ብፁዕ ሥራ አስኪያጁ ሰሞኑን ይዘውት ከነበረው አሳብ በመቀልበስ ብፁዕ ዋና ጸሐፊው አቡነ ጴጥሮስ ጋር ቅድሚያ የቤተ ክርስቲያን ቀኖና ይከበር ብለው ሲከራከሩ ውለዋል። የብፁዕ ዋና ሥራ አስኪያጁ የአቋም ለውጥ ስልታዊ ይሁን መንፈሳዊ እስካሁን አልታወቀም። በተቃራኒው የእነ አባ ሳዊሮስ እና አባ ሩፋኤል ቡድን ደግሞ ጠቅላይ ሚንስትሩ አዝዘዋል መሾም አለበት፤ አለበት የሚል አቋም ይዟል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጳጳሳት ይሾሙ ዘንድ የሚያዙት ማን ስለሆኑ ነው? ከዚህ በፊት ቀድመው ተጀምረው ለፍጻሜ የተቃረቡ ጉዳዮች ላይ የድል አጥቢያ አርበኛ በመሆን ራሳቸውን እንደ ቤተ ክርስቲያን ባለውለታ የሚቆጥሩት ጠቅላይ ሚኒስትር ዛሬም "ጳጳሳቱ መስማማት ከብዷቸው ሔጄ አስታረቅኋቸው" ብለው የሚሳለቁበት ጥሪ በመለካውያን ቀርቦላቸዋል። አባ ሳዊሮስ የተመለሱት የመንግሥትን ተልእኮ ለማስፈጸም መሆኑን ያስመሰከሩበትን ንግግር ተናግረዋል። "በዚህ ጉዳይ ላይ ጠቅላይ ሚንስትሩ ይዳኙን፤ እሳቸው ከሰኞው ጉባኤያችን ላይ ይገኙልን" ብለዋል። ጠቅላይ ሚንስትሩም "አሁን ስማችን ተጠርቷል መግባት እንችላለን" እንዳለው ሰይጣን ሰኞ ከቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤ መገኘታቸው ይጠበቃል።

ከዚያም በተለመደው አፈ ቅቤ ንግግራቸው "ጉዳዩን ለራሳችሁ ብንተወውም ያለ እኛ መፈጸም አልቻላችሁም" በማለት በጥቂት መለካውያን ጥሪ ለቤተ ክርስቲያን የረጅም ጊዜ ነቀርሳ የሚሆኑ ሰዎችን ተክለው ሊወጡ ይችላሉ። ባለፈው ሲያደርጉ እንደነበረው ስድብና ማስፈራሪያውን በመቁረጥ ስለ ቤተ ክርስቲያን ጥሩ የተናገሩበትን በመምረጥ በሚዲያ በማውጣት፣ በድጋሜ አባቶችን ከመከፋፈል እንዳዳኑ በመግለጽ ከበሬታውን ለመውሰድ ይተጋሉ።

ግን ጠቅላይ ሚኒስትሩ በተቀደሰው ጉባኤ ይገኙ ዘንድ ማናቸው? እናም እንደ ልጅ እንላለን፤ እኛ ከእግዚአብሔር ይልቅ ለምድራዊ መሪ እንታዘዝ ዘንድ አይገባንም እንድትሉ እንሻለን። የተሾማችሁት እኛን ለመጠበቅ እንጂ የጠቅላይ ሚኒስትር ትእዛዝ ለማስጠበቅ አይደለም። ይህ ጉባኤ መንፈስ ቅዱስ የሚገኝበት ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት ብቻ የሚታደሙበት ነው። እግራችሁን ቤተ መንግሥትና ቤተ ክህነት ተክላችሁ በሁለት ቢላዋ የምትበሉ መለካውያን ለራሳችሁ ክብር ባይኖራችሁ ስንኳ ለጉባኤው ክብር ስጡ። የምትንፈላሰሱበት መኪና፣ የምትኖሩበት ቅንጡ ቤት፣ የምትመሩት የተንደላቀቀ ሕይወት ቤተ ክርስቲያንን በመቅረብ ያገኛችሁት መሆኑን አትርሱ። በዚህ ጉባኤ ከእግዚአብሔር ፈቃድ ይልቅ ለምድራዊ መንግሥት በመታመን በቤተ ክርስቲያን ላይ እሾህ ለመትከል፣ አረም ለማብቀል የምትተጉ "አባቶች" ግን እግዚአብሔር ቢታገሣችሁ ልጆቻችሁ እንምራችሁ ዘንድ ፈቃዳችን አይደለም። ምክንያቱም አሳደጁን ወዳጅ አድርጎ በጉባኤ እንዲገኙ መጥራት የዓላማ እንጂ የአሳብ ልዩነት አይደለምና።

@ortodoxtewahedo
2.3K viewsedited  03:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-20 06:48:51
"ስልጣኔን #እለቃለሁ"

በዚ 2 ቀን ትልቅ #ተጋዱሎ እየተደረገበት የሚገኘዉ የሲመተ ጵጵስና አጀንዳ ትላንትና ባለመስማማት አጀንዳዉ ለዛሬ አድሮ ነበር በመሆኑም በሶስቱ “#ጳጳሳት” የተሾሙት የጫካው “ኤጲስቆጶሳት” ሹመት ሲኖዶሱ #እንዲያረጋገጥ ከጀርባ በአብይ አህመድ በሚዘወሩት አቡነ ሳዊሮስ፣ አቡነ ዜናማርቆስ እና አቡነ ኤዎስጣቴዎስ በጉባኤው ላይ ቢጠየቅም ቅዱስ ሲኖዶስ ታሪካዊ #ስህተት ሰርቶ የሚባለውን #ሹመት ካፀደቀ ስልጣኔን እለቃለሁ ሲሉ እኝህ አባቶቻችን #ወጥረው ይዘዋል!!!

የዲዮስቆሮስን ገድል እየተማር ለኖረ ዲዮስቆሮሳዊነት እንዲህ ነው !!!


@ortodoxtewahedo
2.1K views03:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-19 21:24:11
ከእነርሱ ጋር ካለው ይልቅ ከእናንተ ጋር ያለው ይበልጣል
***

መንጋውን ጠብቃችሁ፣የቅድስት ቤተክርስቲያንን አንድነት አጽንታችሁ ታልፉ ዘንድ የእዚህ ዘመን የመንፈስቅዱስ የአደራ ተቀብላችዋል።

የሐና እና ቀያፋ በትር ሳይሆን የበረሃው መናኝ ፣የተክሳጹ ጌታ የሆነውን የመጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስን ፍኖት ነፍሳችሁ እንደምትመኝ እናምናለን።

ከሹማምንቶች ዛቻ ይልቅ የአምላካችሁ የጥባቆት መዳፉ ሰፊ ነው ። ከመላካውያንን ሐሳብ ይልቅ የእግዚአብሔር ዋጋ ግዙፍ ነው።

ቢጸ ሐሳውያንን በህገ ተክሳጽ አሳፍራችሁ፣ጠብ የሚዘሩ ምላሶችን አውግዛችሁ፣ድንበር ለማፍለስ ህግ ለመጣስ የመጣውን ለይታችሁ

ከሰው ጭብጨባ ይልቅ የአምላክ አክሊልን ለመቀበል እንደምትዘጋጁ እንተማመናለን።

በረከታችሁ ይደርብን !!! እግዚአብሔር ይርዳችሁ!!!

@ortodoxtewahedo
2.5K viewsedited  18:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-19 21:17:56 በቤተ ክርስቲያን ታሪክ ትልቅ ስሕተት የሚሠራበት፣ ወይም የሲኖዶሱን ልዕልና ከፍ የሚያደርግ ውሳኔ ሊወሰን ጫፍ ላይ ነን። የዛሬዋ ቀን ዕለተ ዓርብ እና መጭው ሰኞ ወሳኝ ዕለታት ናቸው።
ትናንት የተጀመረው ሲመተ ኤጲስ ቆጶሳት ጉዳይ እልባት አልተገኘም። ሲኖዶሱ በሁለት ሐሳቦች እልህ አስጨራሽ ክርክር ላይ ነው። ክርክሩ የቤተ ክርስቲያንን መብት በሚያስጠብቁ አባቶች እና የመንግሥትን ትእዛዝ በሚያስፈጽሙ መለካውያን አባቶች መካከል ነው። ከሁለቱም ወገን ሳይሆኑ በሁለት ቢላ የሚበሉ መሃል ሰፋሪዎችም ጥቂት አይደሉም (ስም ጠቅሰን እንመጣለን)
በዚህ ሰአት ከምእመናን ጸሎት ያስፈልጋል። ዛሬ ወይም ሰኞ ውሳኔውን እናውቃለንና እውነተኛ አባቶችን በጸሎት እናግዛቸው።

@ortodoxtewahedo
2.2K viewsedited  18:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ