Get Mystery Box with random crypto!

ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ

የሰርጥ አድራሻ: @ortodoxtewahedo
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 47.96K
የሰርጥ መግለጫ

ይህ ቻናል የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ዶግማንና ቀኖናን ትውፊትን እንዲሁም አስተምሮን የጠበቁ የተለያዩ የሚያስተምሩ ነገሮች ይለቀቁበታ፡፡ በተጨማሪ በ youtube #subscribe በማድረግ አገለግሎቱን ይደግፉ።
‹‹ከትውልዱ ማን አስተዋለ››
ት.ኢሳ 58÷3
https://youtu.be/csxxAMGtC4I
ለመቀላቀል
http://t.me/ortodoxtewahedo

Ratings & Reviews

4.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 3

2023-07-04 23:08:22
"ለችግረኛና ለምስኪን የሚያስብ ምስጉን ነው፤ እግዚአብሔር በክፉ ቀን ያድነዋል። እግዚአብሔር ይጠብቀዋል፥ ሕያውም ያደርገዋል፥ በምድር ላይም ያስመሰግነዋል፥ በጠላቶቹም እጅ አያሳልፈውም።" መዝ 41፤ 1-2

ታላቅ እናት አበበች ጎበና ነፍስ ይማር!!

@ortodoxtewahedo
2.3K viewsedited  20:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-04 23:04:39

እንኳን ለአባ ቴዎዶስዮስ ሊቀ ጳጳሳት፣ ለቅዱስ ያዕቆብ ዘእልበረዳይ፣ ለቅዱስ ባስልዮስ እንዲኹም ለቅዱስ ባሊዲስ ዓመታዊ የመታሰቢያ በዓል በሰላም አደረሳችኹ



"ጽዮንን የሚወዳት አይደክምም!"

ዳግመኛም ዛሬ ሰኔ 28 ቀን አማኑኤል ቸር አምላካችን፣ ቅዱሳን አበው (አብርሐም: ይስሐቅና ያዕቆብ)፣ ቅዱስ እንድራኒቆስና ሚስቱ ቅድስት አትናስያ፣ ቅድስት ዓመተ ክርስቶስ እንዲኹም ቅዱስ ቴዎድሮስ ሮማዊ (ሰማዕት) ወርኃዊ መታሰቢያቸው ነው

አምላከ ቅዱሳን በቃልኪዳናቸው ይማረን አሜን!

"የቅዱሳን መታሰቢያ ለበረከት ነው" ምሳ. ፲፥፯



@ortodoxtewahedo
2.2K viewsedited  20:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-04 14:21:59
@ortodoxtewahedo
2.9K views11:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-04 14:21:50 ማኅበረ ቅዱሳን በትግራይ ክልል አስቸኳይ ሰባዊ ድጋፍ እንዲደረግ ለኦርቶዶክሳውያንና የሚመለከታቸው አካላት ጥሪ አቀረበ።

የማኅበሩ ዋና ጸሐፊ መምህር ዋሲሁን በላይ ዛሬ ሰኔ26/2015 ዓ.ም ረፋድ መግለጫ ሰጥተዋል።
+++++++++++++++++++++++++++++++++

"አብነት ት/ቤቶች ተበትነዋል፤ ገዳማትና አድባራትም ከፍተኛ ማኅበራዊ ድጋፍ ይፈልጋሉ" ያሉት ዋና ጸሐፊው በርካታ ታላላቅ ገዳማት፣ማስመስከሪያ ጉባኤ ቤቶች፣ በርካታ ሊቃውንት እና በርካታ ምእመናንን ያሉበት በመሆኑ በተለይም ኦርቶዶክሳውያን አስቸኳይ ድጋፍ ሊያደርጉ እንደሚገባ ተናግረዋል።

ማኅበረ ቅዱሳን በጦርነቱ፣ በግጭት እና በተፈጥሮ አደጋ ለተጎዱ ለቦረና፣ ሻሸመኔ፣አዲስ አበባ ዙርያ፣ ሰሜን ሸዋ፣ ሰላሌ ፍቼ፣ አምቦ፣ ዋግሕምራና ጎንደር አዘዞ ለሚገኙ የተለያዩ አህጉረ ስብከቶች በያዝነው ዓመት ድጋፍ ማድረጉንም አስታውሰዋል።

በጦርነቱ ወቅት ቀይ መስቀልን በመሰሉ በዓለም አቀፍ ተቋማት በኩል ድጋፍ ሲልክ መቆየቱንም ተናግረዋል።

ከጦርነቱ በኋላ ከወር በፊትም ትግራይ ክልል ለሚገኙ ለ10 ገዳማትና አብነት ት/ቤቶች በባንክ አካውንቶቻቸው ብር በመላክ ለመርዳት ሞክረናል ያሉት ዋና ጸሐፊው ነገር ግን ካለው ችግር አሳሳቢነት አንጻር በማኅበሩ አቅም ብቻ የሚቻል ባለመሆኑ ጥሪ ለማቅረብ ተገደናል ብለዋል።

መምህር ዋሲሁን በላይ አክለውም በአከባቢው አስተዳደራዊ ችግር እንዳለ ይታወቃል ነገር ግን ልዩነቶች በአባቶች ውይይት ይፈታሉ ብለን እናምናለን ሲሉ ተናግረዋል።

ዘላቂ መፍትሔ እስኪገኝም ጉዳት በደረሰባቸው አካባቢዎች ያሉ ብፁዓን አባቶች በዚህ በጎ ተግባር ተሳታፊ ብቻ ሳይሆን ባለቤት በመሆን እንዲያስተባብሩም ጠይቀዋል።

ይህ የድጋፍ ዘመቻ ዋግምኽራ ሀገር ስብከትን እንደሚያካትት የገለጹት ዋና ጸሐፊው ማንኛውም ድጋፍ ማድረግ የሚፈልግ አካል በማኅበሩ በኩል ወይም አከባቢው ባለው የቤተ ክርስቲያን ሕጋዊ መዋቅር ወይም በቀጥታ ለገዳማትና አብነት ት/ቤቶች መለገስ እንደሚችሉ ገልጸዋል።

ይህ ዘመቻ እንደተጠናቀቀም በባለሙያዎች የተጠና ሪፖርት እንደሚቀርብ ታውቋል።

በትግራይ ክልል ዓለም አቀፍ እርዳታ ሰጭ አካላት ከወጡ በኋላ የከፋ ችግር ውስጥ መሆናቸውን በተለያዩ ሚዲያዎችና ተቋማት እየተገለጸ መሆኑ ይታወቃል።

@ortodoxtewahedo
2.7K viewsedited  11:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-04 11:44:40
ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤ/ክ ኅዳር 1964 ዓም / St George Church, November 1971

@ortodoxtewahedo
2.5K viewsedited  08:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-04 11:32:40 በእለት ተእለት የአገልግሎታችን እነዚህ 7ቱ የኦርቶዶክሳውያን ጥያቄዎች ምላሽ እንዲያገኙ ምን ያህል አስተዋጽዖ ጉልህ አስተዋጽዖ አድርገን ይሆን?

ይህን ማድረግ የሚችል ሌላ ሰው አለ አንበል ለተሻለ ውጤት እንትጋ፣ ሌሎችን አንጠብቅ በግል የምናደርገው አስተዋጽዖ የጋራ ውጤት እንደሚኖረው ለደከሙትም ብርታትና መነቃቃት እንደሆነ እናስተውል።

እነዚህ የእኔ ድርሻዎች ናቸው! ስለ ውጤቱ ተጠየቂ እንጂ ከሌሎች ጠባቂ አይደለሁም፤ በግል እና በጋራ ውጤት ለማምጣት እተጋለሁ ብለን በእግዚአብሔር ፊት ለራሳችን ቃል እንግባ፤ ያን ጊዜ ውጤቱን መመልከት እንችላለን።

ወደ ጉዳያችን

አስቸኳይ የመንግሥት ምላሽ የሚፈልጉ የኦርቶዶክሳዊያን ጥያቄዎች

1. በሕገመንግሥት፣ በፖለቲካ ማኒፌስቶ፣ በመደበኛ ትምህርት፣ በሚዲያና መሰል መንገዶች ኦርቶዶክሳዊ አስተምህሮንና ኦርቶዶክሳዊያንን ለጥቃት የሚያጋልጡ መልዕክቶች በአስቸኳይ በሕግ እንዲታገዱ::

2. ኦርቶዶክሳዊያንን ለይቶ ከሥራ፣ ከመንግሥት ኃላፊነት፣ ከሀብት ማፍራት እድሎች የሚያገል ከቀበሌ እስከ ፌደራል የተዘረጋው ሃይማኖታዊ መንግሥትና መዋቅር በአስቸኳይ እንዲቆምና ሃይማኖታዊ ሳይሆን ሕዝባዊ መሆኑን በተግባር እንዲያረጋግጥ::

3. ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያንን በቋንቋና በተለያዩ ዘውጎች ለመከፋፈል የሚደረገው ፖለቲካዊ ጥረት በጥናትና በምርምር ስም የሚደረጉ የመከፋፈል ዘመቻዎች እና ተግባራት እንዲታደጉ::

4. በኦርቶዶክሳዊያን ላይ ያነጣጠሩ የአካል፣ የሥነልቦና፣ የኢኮኖሚ፣ የማኀበራዊ፣ የፖለቲካ፣ የማፈናቀል፣ ከአገራዊ ተሳትፎ የመገለልና የፍጅት ጥቃቶች በአስቸኳይ እንዲቆሙ::

5. እስከ አሁን የተፈጸሙ ጥቃቶች በዝርዝር ተገልጾ አጥፊዎች ለሕግ እንዲቀርቡ እና የተጎዱት እንዲካሱ::

6. በመላው አገሪቱ የተፈናቀሉ ኦርቶዶክሳዊያን ወደ ቀደመ ቦታቸው እንዲመለሱ::

7. “አዲሲቷ ኢትዮጵያ” በሚል ሽፋን ኦርቶዶክሳዊ አሻራዎችን የማጥፋት ፖለቲካዊ ሂደት በአስቸኳይ እንዲገታ እና በግልጽ ይቅርታ ተጠይቆ እርምት እንዲወሰድ::

@ortodoxtewahedo
2.4K viewsedited  08:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-04 11:13:59
"ወዳጄ ሆይ ሮማውያን ወታደሮች ጎንጉነው በጌታችን እራስ ላይ እሾህ እዳቀዳጁት ባሰብህ ጊዜ እጅግ ማዘንህ አይቀርም ። ሆኖም አንተም እሾህ የተባለውን አንድ ኃጢአት በሰራህ ቁጥር በጌታችን ላይ የተደፉትን እሾኾች ቁጥር እንደጨመርህ አስብ ።በፈጣሪ የማያምኑት ሮማውያን ወታደሮች ከጎነጎኑት እሾኽ በላይ የጌታችንን እራስ የበለጠ ዘልቆ የሚወጋው ደሙን አፍስሶ ያዳነን እኛ ክርስቲያኖች በኃጢአታችን የምንጎነጉነው የእሾኽ አክሊል ነው ።{ስለመተላለፋችን የቆሰለው አምላክ በመተላለፋችንም ይቆስላል ።!}

{በእርሱ ቁስል እኛ ተፈወስን ከሚለው ርዕስ የተወሰደ )

[ ሕማማት]
{በዲ/ን ሄኖክ ኃይሌ}

መድኃኔዓለም ሆይ አባት ሆይ ይቅር በላቸው በማለት በታላቅ ቃል በመስቀል ላይ ፥ ለተናገረ ቃልህ ሰላም እላለሁ በመስቀል ላይም በሰቀሉህ ጊዜና ጎንህን በጦር በወጉ ጊዜ አንዳችም የተቃውሞ ትንፋሽ ላልተነፈሰ እስትንፋስህም ሰላም እላለሁ ።
መድኃኔዓለም ሆይ ጻድቃንን ያይደለ ኃጥአንን ለማዳን በራሱ ደም ራሱ ለተጥለቀለቀ ስነ መልክህ ሰላም እላለሁ !

( መልክአ - መድኃኔአለም )27

@ortodoxtewahedo
2.2K views08:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-04 11:12:52
መድኃኔአለም

መድኃኔዓለም ማለት== =የአለም መድሃኒት
መድኃኔዓለም ማለት=== የሁሉ ቤዛ
መድኃኔዓለም ማለት ===የገዢዎች ሁሉ ገዢ
መድኃኔዓለም ማለት===የነገስታት ሁሉ ነጉስ
መድኃኔዓለም ማለት ==የፍጥረታት ሁሉ ፊጣሪ ነው።

ሀይሌን ጉልበቴን ታድሳለህ
ቀና ቀና እንድል ታድርጋለህ
መድኃኒዓለም መድኃኒቴ
ቀሪው አንተ ነህ ለህይወቴ

መድኃኒዓለም …………………
✞ጌታ ሆይ...................
✞ኢየሱስ ሆይ..................
✞መድኃኒዓለም ሆይ.........
✞አማኑኤል ሆይ............
✞ጎዶልያስ ሆይ..............
✞ኤልሻዳይ ሆይ..............
✞እግዚአብሔር ሆይ........

••••••>አማኑኤል ሆይ ቻይ እንደሆንክ አዉቅ ሀሳብህም ሁሉ ይሆን ዘንድ ከቶ እንደማይከለከል በአለማት ላይ አንተ ብቻ እንደሰለጠንክ የሁሉ ፍጥረታት ስራ አስኪያጅ እንደሆንክ ያለጥርጥር በሙሉ ልቤ አምናለሁ፡፡
••••••>ዉዴ የህይወቴ አባት ካንተ ሌላ:-
☞ሳለቅስ እንባዬን የሚያብስ
☞ስወድቅ የሚያነሳኝ
☞ስራብ የሚያበላኝ
☞ስጠፋ የሚፈልገኝ
☞ስጨነቅ የሚደርስልኝ
☞አንገቴን ስደፋ ቀና የሚያደርገኝ
ካንተ በቀር ማንም እንደሌለኝ አዉቃለሁ፡፡ ••••••>መድኃኔዓለም ሆይ:-
ሌት ተቀን እንደ ንስር እናት የምትጠብቀኝ እና የምታየኝ -አቤቱ እንዴት ባለ አንደበት ላመስግንህ....
በአንድ ነገር ተስፋ አለኝ እርሱም አንተ ዘወትር ከኔጋር ነህ.
እዉነት ነዉ እግዚአብሔር ባስቀመጥነዉ ሁሉ አለ..
ጥበቃው አይለየን አሜን!

@ortodoxtewahedo
2.2K viewsedited  08:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-04 05:53:53
"ከሰው ወገን ማንም እንደ እኔ ኃጢአት የሠራ በደለኛ የለም፤ እንደ አንተም ያለ መሐሪ ይቅር ባይ አምላክ አይኖርም፤ ፈጣሪዬ ክርስቶስ ሆይ ዓለማትን ሁሉ የፈጠርህ ፈጣሪ እንደመሆንህ መጠን በኋለኛው ዘመን በዓለም ላይ ለመፍረድ በምትመጣበት ጊዜ ከጎንህ በፈሰሰው ደም ኃጢአቴን እጠብልኝ!"

መልክአ መድኃኔዓለም



  #ባለ ማዕተቦችን ወደዚህ ግሩፕ ይጋብዙ
መልካም ቀን  

ለመቀላቀል  
@ortodoxtewahedo
2.6K viewsedited  02:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-04 05:53:13
“የተቀጠቀጠን ሸምበቆ አይሰብርም፥ የሚጤስንም ክር አያጠፋም፤ በእውነት ፍርድን ያወጣል።”
  — ኢሳይያስ 42፥3



  #ባለ ማዕተቦችን ወደዚህ ግሩፕ ይጋብዙ
መልካም ቀን  

ለመቀላቀል  
@ortodoxtewahedo
2.2K viewsedited  02:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ