2022-08-30 09:32:51
ከወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አስተዳደር የፀጥታ ምክርቤት በወቅታዊ ጉዳይ የተሰጠ መግለጫ!
እንደሚታወቀው ሀገራችን ኢትዮጵያ ፈተናዎችን በድልና በብቃት በብልሃት ና በጥበብ አሸባሪውን ትህነግ/ህወሐት እና ታሪካዊ ጠላቶቻችንን እያሸነፈች የምትሻገር እንጂ በፈተናዎች ብዛት ተደናቅፈን የምንወድቅ ኢትዮጵያውያን አይደለንም። ምክንያቱም እኛ ኢትዮጵያውያን ለሰላም የሚዘረጉ እጆች ያለን እንጂ ኢትዮጵያን ለማፍረስ የሚመጣ ማንኛውም የሰማይም ይሁን የምድር ሃይል ሽንፈትና ውርደት ተከናንቦ የሚመልስ ታሪክ ያለን ህዝቦች መሆናችንን የአደባባይ ሚስጢር ነው ።
ስለሆነም ኢትዮጵያዊነት የአሸናፊነት ምልክት በመሆኑ አሁናዊ የአሸባሪው ህወሃት ሦስተኛው የጦርነት ትንኮሳዎች የመጨረሻው የመሞቻው ጊዜ የኢትዮጵያና የኢትዮጵያውያን የድልና የትንሳኤ ጊዜ ነው።
ስለዚህ ወራሪው ቡድን የተሰጠውን የሰላም አማራጮችን እያጨናገፈና እያፈረሰ በትግራይ ህዝብ ጫንቃ ላይ ተጣብቆ ደሙን እየመጠጠ እና በውር ድንብር ጉዞ ለመኖር አማራና አፋር ክልሎችን በመውረርና በማዋረድ ኢትዮጵያን ማፍረስ የሚል ሰይጣናዊ ግቡ ለማሳካት በህዝባችን ያልፈነቀለው የሴራ ድንጋይ: ያልፈፀመው ደባ የለም።
ይሁን እንጂ መላው ኢትዮጵያውያን ይህንን ወራሪ ቡድን ለአንዴና መጨረሻ እስከወዲያኛው እንዲያሸልብ ከወትሮው በተለየ ኢትዮጵያዊነታችንን አጠናክረን እንደ አንድ ሰው አስበን እንደ አንድ ቃል ተናግረን ለታሪካዊ ጠላቶቻችንን ውርደት አከናንበን በዲፕሎማሲው ተሰሚነቷ የገነነች በኢኮኖሚው ተፅዕኖ ፈጣሪ የሆነች ኢትዮጵያ እውን ለማድረግ መላው ህዝባችን ድካ የለሽ እንቅስቃሴ እንዲያደርግ ታሪካዊ ጥሪ ስናቀርብለት ትልቅ ኩራት ይሰማናል።
የተከበራችሁ የፀጥታ ጥምር ሃይሎች፣ የፖለቲካ አመራሮችና መላው ህዝባችን ዛሬም እንደትላንቱ የማያዳግም እርምጃ በአሸባሪው ህወሃት እና በታሪካዊ ጠላቶቻችን የመረረ ጥላቻ ይዘን የመረረ ምት አሳርፈንና አሳፍረን በሁለንተናዋ የተከበረችና የተፈራች ሀገር ለመገንባት ትግላችን ከውስጥ ባንዳ እስከ ውጭ ጠላት ያለውን ሀገር የማፍረስ ቅንጅት አፍርሰንና ደርምሰን በሁለንተናዊ የበለፀገች ኢትዬጲያ እውን ለማድረግ የሚከተሉትን ተግባራትን እንድንሰራ የፀጥታው
ምክርቤት ያቀረበው ጉዳይ:-
1.ሁሉም ወረዳዎችና ከተሞች ከመንግስት ተሽከርካሪወች ውጭ የተሽከርካሪ እንቅስቃሴ ከጧቱ12:00 እስከ ምሽት 1:00 ብቻ እንዲሆን የወሰነ መሆኑ ታውቆ ይህን ተላልፎ የተገኘ የተሽከርካሪ ባለ ንብረትና አሽከርካሪ ህጋዊ እርምጃ የሚሰድ ይሆናል!!
2.መላው የዞናችን ህዝብ ከዚህ በፊት በተደራጀበት የመንግስት አደረጃጀት መሠረት አካባቢውን ከሰር-ጎገብና ከውስጥ ባንዳ ያላለሰለሰ ትግል በማካሄግድ ከጠላት አስተሳሰብና ተግባር የፀዳ ከባቢ እንድታደርጉ ጥሪያችን እናቀርባለን!!
3.ማንኛውም ሀገሩን እንዳትፈርስና በጠላት እንዳት ወረር የሚፈልግ ሰው ሁሉ (ተቆርቋሪ) ፀጉረ-ልውጥ ሲያገኝ በፍጥነት በአካቢው ለተሰማራው የፀጥታ መዋቅር የመጠቆም:የመያዝ:ወደ ህግ አካላት እንዲያስረክቡ ጥሪያችንን እናቀርባለን !!
4.በወረዳ የቀበሌ ከተሞችን ጨምሮ ባለሆቴሎች ባለ ምግብ ቤቶች ማንነቱ/አድራሻው/ ያልታወቀ ሲያጋጥም ለሚመለከተው የፀጥታ አካል እንድታስረክቡ
ከዚህ ውጭ በመሆን ማንነቱ ያልታወቀ፣ ያስጠጋ፣ ያሳደረ፣ ለጠላት ተባባሪ በሆነ አካል ላይ እርምጃ ይወሰዳል።
5.በተለይ በከተሞች አካባቢ ተከራይተውና አከራይተው የሚኖሩ ዜጎች በፍጥነት ተመዝግበው በአቅራቢያ ላለው የፀጥታ ተቋም ሪፖር እንድታደርጉ።
6.በዞናችን ጠላት የሚኖርባቸው አጎራባች ወይም አዋሳኝ ቦታዎች ቀይ መስመር መሆናቸውን ታውቆ በእነዚህ አካባቢ የእርሻና እርባታ ያላቹሁ አልሚዎቻችን ከጧቱ 12:00 እስከ ቀኑ 12:00 ብቻ እንቅስቃሴ የምታደርጉ መሆኑን እያሳሰብን ለጉልበት ስራ የምትወስዷቸውን አካላት ማንነት በማረጋገጥ ለሚለከተው የፀጥታ አካል አስመዝግባቹሁ የምታሰሩ ሆኖ ይህን የተላለፈ ባለ ሃብትም ይሁን ወኪል በህግ ይጠየቃል።
7.በዞናችን በሁሉም አካባቢዎች የሰው እንቅስቃሴ እስከ ምሸቱ 3:00 ብቻ መሆኑ ታውቆ እነዚህን ክልከላዎችን በሚተላለፍ አካል ላይ ህግ እንዲያስከብር ለጸጥታ መዋቅሩ ትዛዝ ተሰጥቷል።
8.በሁሉም የዞናችን አካባቢወች አዲስ መታወቂያ እንዳይሰጥ ተከልክሏል።
9.በዞናችን ውስጥ ያለ የታጠቀ ሃይል በሙሉ ካለበት ወረዳ ከተማና ቀበሌ አስፈላጊውን ወታደራዊ ዝግጅት አድርጎ እንዲጠብቅ ታዟል።
10.መላው የዞናችን ህዝብ ለፀጥታ ጥምር ሃይሎች የተለመደውን ደጀንነቱን በአስተማማኝነት እያጠናከረ እንዲሄድ ጥሪያችንን እናቀርባለን!
በመጨረሻም በጠላት ላይ የመረረ ጥላቻ በመያዝ እና በመዋጋት ክብራችንን እና ነፃነታችንን እንጂ ከቀያችን ሸሽተንና ተፈናቅለን ህልውናችንን አናረጋግጥም እና መታገልና መደራጀት ብቻ ነው አማራጫችን!!
ኢትዮጵያ እያሸነፈች ትሻገራለች!!
ነሐሴ23/2014 ዓ.ም
የወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አስተዳደር የፀጥታ ምክር ቤት
ሰቲት ሁመራ
3.3K views06:32