Get Mystery Box with random crypto!

NiSiR Int. Broadcasting Co. (Official Telegram Channel)

የቴሌግራም ቻናል አርማ nisirbroadcasting — NiSiR Int. Broadcasting Co. (Official Telegram Channel) N
የቴሌግራም ቻናል አርማ nisirbroadcasting — NiSiR Int. Broadcasting Co. (Official Telegram Channel)
የሰርጥ አድራሻ: @nisirbroadcasting
ምድቦች: ዜና
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 14.71K
የሰርጥ መግለጫ

NISIR International Broadcasting Co. is an impartial and independent media agency operates as television; radio; social media & multimedia production.
Facebook: https://www.facebook.com/NISIR-International-Broadcasting-Corporation-105276671420707

Ratings & Reviews

3.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 246

2022-09-01 16:49:04
"ጦርነቱ የአማራ እና የትግራይ ህዝብ ጦርነት አይደለም ። በጦርነቱ የአማራ ልዩ ሀይል፤ ፋኖ እና ሚሊሻ ኢላማ ያደረገ ውግያ ላለማድረግ እና በሂደቱ የተማረኩ ካሉ ወድያው ለመልቀቅ ወስነናል።"
የትግራይ ሰራዊት ዋና አዛዥ ታጋይ ታደሰ ወረደ (ወዲ ወረደ)

ንሥር ብሮድካስት
ነሃሴ 26/2014 ዓ.ም

በትግራይ ህዝብ ላይ የተከፈተው ጦርነት የአማራ እና የትግራይ ህዝብ ጦርነት ባለመሆኑ በጦርነቱ የአማራ ልዩ ሀይል፤ ፋኖ እና ሚሊሻ ኢላማ ያደረገ ውግያ ላለማድረግ እና በሂደቱ የተማረኩ ካሉ ወድያው ለመልቀቅ መወሰኑን የትግራይ ሰራዊት ዋና አዛዥ ታጋይ ታደሰ ወረደ (ወዲ ወረደ) ገለፁ።

የትግራይ ሰራዊት ዋና ኣዛዥ ታጋይ ታደሰ ወረደ በወቅታዊ ጉዳይ ዙርያ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ በትግራይ ላይ የተከፈተው ጦርነት የትግራይ እና የአማራ ህዝብ ጦርነት አለመሆኑን ገልፃል። የትግራይ ሰራዊት ለህዝቡ ህልውና ሲለ ተገዶ እንጂ የአማራ መሬት የጦርነት አውድማ የማድረግ ፍላጎት የለውም። የሁለቱም ህዝቦች ጦርነት ባለመሆኑም የአማራ ልዮ ሃይል፣ፋኖ እና ሚሊሻ ኢላማ ያደረገ ጦርነት ላለማካሄድ ወስነናል ብሏል።

በደቡባዊ ግንባር የነበረው ጦርነት 5000 ሺህ የጠላት ሰራዊት ተሟርካል። ከዚህ መሃል የአማራ ልዩ ሃይል፣ ፋኖ ወይ ሚሊሻ ስለመኖራቸው ሲጠየቁ ቀድሞ በያዙት የተሳሳተ የትግራይ ሰራዊት ለይቶ ይመታል የሚል ትርክት ራሰቸውን ያልገለፁ ይኖራሉ። 8 ራሳቸው የገለፁ ግን ወዲያው ተለቀዋል ብሏል። አሁንም ካሉ እንለቃለን፣ ሲማረኩም ወደ ጦር ምርኮ ሳይገቡ ወዲያው እንዲለቀቁ ተወስኗል። በመሆኑም የአማራ ታጣቂዎች ጥምር ሃይል ከተባለው አደረጃጀቱ ራሳቸውን ሊያርቁ ይገባል ብሏል።

የአማራ ህዝብ እየተፈናቀለ ይገኛል። ይህ ያሰዝናል ፣ ህዝቡ ቀየው የሚለቅበት ምንም አይነት ምክንያት የለም። በመሆኑም በቤቱ ሊቀመጥ ይገባል። የትግራይ እና አማራ ህዝብ ተጎራብቶ መኖሩ ስለማይቀር የተፈጠረው ቀውስ ለማከም ሁሉም ሊሰራ ይገባል ብሏል ታጋይ ታደሰ ወረደ ።

የአማራ ሊህቃን ብስለት ሮቆባቸዋል ያለው ታጋይ ታደሰ ወረደ ከዚህ በፊት የሆነው ሆኗል። ከዚህ ብኋላ ግን ሌላ ቁስል መፍጠር ሊያበቃ ይገባል። በመሰረቱ የትግራይ ህዝብ ጠላት የአማራ ህዝብም ጠላት ነው ብለዋል።

የትግራይ ሰራዊት ዋና አዛዥ ታጋይ ታደሰ ወረደ ለዓፋር ህዝብ ባስተላለፈው መልእክት የትግራይ እና የዓፋር ህዝብ የማይነጣጠሉ ናቸው። በጠላቶች ተፈጥሮ የነበረው ችግርም ህዝቡ እየተነጋገረ ወደ ቀድሞ ሰላም እየተመለሰ ነው ብሏል።

ለሱማሌ ህዝብም ጥያቄዎቻቹሁ እንረዳለን፣ የሶማሌ ልዩ ሃይል ከዚህ ቀደም ላደረከው ነገር እናመሰግናለን አሁንም በትግራይ ጦርነት ላለመሳተፍ እያሳየሀው ያለው ተቃውሞ አጠናክረህ ልትቀጥልበት ይገባል ብሏል።

ሰፊ የኦሮሞ ሃይል በትግራይ ጦርነት ለማሳተፍ ጥረት እየተደረገ ቢሆንም እየከሸፈ ይገኛል። ከኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት እና ሌሎች ታጋዮች ጋር ያለንን ትብብር እናጠናክራለን ያለው ወዲ ወረደ የኦሮሞ ህዝብ እያደረገው ላለው ትግል ምስጋናውን አቅርቧል።

ከመከላከያ ሰራዊት አባላትም ከባእድ ጋር ሆናችሁ የትግራይ ህዝብን በመውጋት ተገፍቶ ከኢትዮጵያ እንዲወጣ እያደረጋቹ ትገኛላቹ። የአሁኑ ጥቃትም የመጨረሻ ሊሆን ይችላል፣ በዚህም የታሪክ ተጠያቂዎች ናቹ ብሏል።

ነሃሴ 26/2014 ዓ/ም
ድምፂ ወያነ ትግራይ
ንሥር ብሮድካስት የሁላችንም ድምፅ!

ወቅታዊ ፤ ትኩስ እና የተሟላ መረጃዎችን ለማግኘት
Youtube:https: https://bit.ly/3No0s7x
FaceBook:https://www.facebook.com/Nisirbroadcasting
1.5K views13:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-01 16:47:49
የትህነግ እና "የሳምሪ"ቡድን በወልቃይት ጠገዴ የከፈቱት ጥቃት

ንሥር ብሮድካስ
ነሃሴ 26/2014 ዓ.ም

ከትላንት በስቲያ ምሽት 24/12/2014 ዓ.ም ድንገት የትህነግ ወራሪ ኃይል እና "የሳምሪ"ቡድን በወልቃይት ጠገዴ በበረከት እና ሉግዲ መሃል ጦርነት መጀመራቸው ተገልፆ ነበረ። ይሁን እንጅ በጥምር ኃይሉ በተወሰደባቸው ጠንካራ እርምጃ ዛሬ ተመልሰዋል።በአካባቢው በለኮሱት ጦርነት ከፍተኛ ሰብአዊ እና ቁሳዊ ኪሳራ አስተናግደዋል።

የህወሓት ወራሪ ኃይል በሰሜን ወሎ በጀመረው ወረራ በቆቦ ከተማና ዙሪያዋ በሚገኙ ንፁሃን ነዋሪዎች ላይ ዳግም ግድያ፣ዘረፋ እና እንግልት አየፈፀመ መሆኑ ይታወቃል።

"በወልቃይት በረከት እና ሉግዲ በጥምር ኃይሉ የተወሰደው አይነት የማያዳግም ዕርምጃ በሰሜን ወሎም በመውሰድ ወራሪው ኃይል የሚያደርሰውን ጥቃት ባስቸኳይ ማቆም ያስፈልጋል" ሲሉ አስተያየት ሰጪዎች አሳስበዋል።

ንሥር ብሮድካስት የሁላችንም ድምፅ!

ወቅታዊ ፤ ትኩስ እና የተሟላ መረጃዎችን ለማግኘት
Youtube:https: https://bit.ly/3No0s7x
FaceBook:https://www.facebook.com/Nisirbroadcasting
Telegram:https://t.me/nisirbroadcasting
Website: https://nisirbroadcasting.com
Twitter:https://twitter.com/NISIRInternati1
1.4K views13:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-01 10:17:37
"ብዙ ስህተት ቢኖርም ለሀገር ጥቅም ሲባል ዋጥ አድርጌዋለሁ። አንዱን ግን አለመናገር አልችልም። ያለ ምንም ቅድመ ሁኔታ የታሠሩ ፋኖዎች በአስቸኳይ ይፈቱ። በሚሳደዱት ላይም የታወጀው ዘመቻ በፍጥነት ይቁም። እነርሱ በሀገር ላይ አያኮርፉም፣ አላኮረፉምም።" -

ዲ/ን አባይነህ ካሴ

ንሥር ብሮድካስት የሁላችንም ድምፅ!
ወቅታዊ ፤ ትኩስ እና የተሟላ መረጃዎችን ለማግኘት
Youtube:https: https://bit.ly/3No0s7x
FaceBook:https://www.facebook.com/Nisirbroadcasting
Telegram:https://t.me/nisirbroadcasting Website: https://nisirbroadcasting.com
Twitter:https://twitter.com/NISIRInternati1
2.7K views07:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-01 10:12:55
ኦፌኮ*********

ኦፌኮ በሰሜን ኢትዮጵያ ዳግም በተቀሰቀሰው ጦርነትና በኦሮሚያ ክልል የቀጠለው ግጭት በመባባሱ እጅግ ማዘኑን ገለጸ

በኹሉም ወገን ያሉ ተፋላሚ ሀይሎች ግጭቱን በማብረድ ሰላማዊ መፍትሄ እንዲሹ ጠይቋል

የኦሮሞ ፌዴራላዊ ኮንግረስ (ኦፌኮ) አገራችንን ለከፍተኛ ሰብዐዊ፣ ዲፕሎማሲያዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ ኪሳራ የዳረጋት ጦርነት ዳግም በሰሜን ኢትዮጵያ በማገርሸቱና በኦሮሚያ ክልል የቀጠለው ግጭት በመባባሱ እጅግ ማዘኑን ገልጿል።

ፓርቲው በዛሬው ዕለት ባወጣው መግለጫ፤ ”የእነዚህ ግጭቶች መባባስ እና መቀጠል ህዝቡን ዳግም ለከፋ ሞት እና መፈናቀል የሚዳርግ ከሆኑ ባሻገር ለንብረትና መሰረተ ልማቶች ውድመት የተዳረጉ አካባቢዎችን ለበለጠ አለመረጋጋት ይዳርጋል።“ ብሏል።

ጦርነት ለኢትዮጵያ ውስብስብ የፖለቲካ ችግሮች መፍትሄ ሊሆን እንደማይችል የገለጸው ኦፌኮ፤ እነዚህ ችግሮች በዘላቂነት ሊፈቱ የሚችሉት በእውነተኛ እና ኹሉን አቀፍ ድርድር ብቻ መሆኑ ፅኑ እምነቱ መሆኑንም አስታውቋል።

ስለዚህም በኹሉም ወገን ያሉ ተፋላሚ ሀይሎች ግጭቱን በማብረድ ሰላማዊ መፍትሄ እንዲሹ የኦሮሞ ፌዴራላዊ ኮንግረስ (ኦፌኮ) ጠይቋል።

በተጨማሪም በግጭት በተጎዱ አካባቢዎች ኹሉ ተጨማሪ ሞት እና የዜጎችን መከራ ለማሰቀረት ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ በንቃት እና በተቀናጀ ልኩ እንዲረባረብም ጥሪ አቅርቧል።

አለም አቀፉ ማህበረሰብ በመላው ኦሮሚያ የተሰፋፋውን ጦርነት ለመፍታት ቀርቶ እውቅና ሊሰጠው አለቻሉን እንዳሳሰበው የገለጸው ኦፌኮ፤ በክልሉ በተለይም በግጭት እና በድርቅ በተጎዱ አካባቢዎች ያለው ሰብዓዊ ኹኔታ አሳሳቢ ደረጃ ላይ መድረሱን ገልጿል። በመሆኑም የዲፕሎማቲክ ማህበረሰብ እየተባባሰ ያለው ግጭት በአስቸኳይ እና ሰላማዊ በሆነ መንገድ በድርድር እንዲፈታ ኹኔታዎችንን እንዲያመቻች ጠይቋል።

በመጨረሻም ፖርቲው ከኢትዮጵያ ህዝብን፣ ገዥው ፓርቲን፣ ተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎችን፣ የሚዲያ ተቋማትን፣ የማህበራዊ ሚዲያ ባለሙያዎች እና አክቲቪስቶች ግጭቱን ከሚያባብሱ ንግግሮች እንዲታቀቡና ችግሩን ለማርገብና ለመፍታት በአንድ ድምፅ እንዲተባበሩ ጥሪውን አቅርቧል።

ንሥር ብሮድካስት የሁላችንም ድምፅ!

ወቅታዊ ፤ ትኩስ እና የተሟላ መረጃዎችን ለማግኘት
Youtube:https: https://bit.ly/3No0s7x
FaceBook:https://www.facebook.com/Nisirbroadcasting
Telegram:https://t.me/nisirbroadcasting Website: https://nisirbroadcasting.com
Twitter:https://twitter.com/NISIRInternati1
2.5K views07:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-01 08:15:37 ሰበር ዜና _የቤተ አምሓራ ፋኖ ወደ ግንባር ሽኝት ተደረገለት

1.1K views05:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-01 07:27:18
ወራሪዉ የትግራይ አሸባሪ መንጋ ኃይል ወልቃይት ጠገዴንና አከባቢውን ከ16 ዓመት ታዳጊ ጀምሮ እስከ 70 ዓመት አዛውንት የሆነ ማንኛውንም ትግራዋይ፤ የወልቃይት ጠገዴ አማራ ህዝብን እንዲወር የክተት አዋጅ አውጇል።

====ኮ/ል ደመቀ ዘውዱ አየለ====

ማንነታችን እንደ ወንጀል ተቆጥሮ የአማራ ተወላጅ የሆነ ሁሉ በየሄደበት እንደ ዶሮ አፍኖ በመሰወር፣ በመግደል፣ አካልን በማጉደል፣ ከሰማይ በታች ከመሬት በላይ አለ የሚባል ግፍ ሁሉ ተፈፅሞብናል። በሺዎች የሚቆጠሩ ታሪክ አዋቂዎች፣ ስለ ህዝብ መብት ተከራካሪ የሆኑትን የሀይማኖት አባቶችን የት እንደደረሱ ሳይታወቅ ደብዛቸው ጠፍቷል።
ስለሆነም በኢትዮጵያ መከላከያ ኃይል፣ በአማራ ልዩ ኃይል፣ ፋኖ እንዲሁም ሚሊሻና ሌሎች የፀጥታ አካላት ጥምር ተጋድሎ የወልቃይት ጠገዴ አማራ ማህበረሰብ ነፃ ወጥቷል። ይህ የትናንት አኩሪ ገድላችን ነው።
መላው የወልቃይት ጠገዴ አማራ ህዝብ ሆይ!!
ወራሪውና ተስፋፊው የትግራይ ኃይል ለአንዴና ለመጨረሻ ግዜ ህልውናህን ሊያጠፋ ቆርጦ ተነስቷል። በመሆኑም በጠላት ዝግጅት መጠን ልክ በተጠንቀቅ እንድትቆም የወቅቱ አስገዳጅ ሁኔታ ሆኗል።
የተከበርከው የአማራ ህዝብ ሆይ!!
በህብረት፣ በአንድነት፣ በፅናት ስለታገልክ የስርዐት ለውጥ አምጥተኃል። ነፃነትም አግኝተኃል። ይሁን እንጂ ድጋሚ ህልውናህን ሊያጠፋ ከመላ ትግራይ የከተተ ወራሪ ኃይል በይፋ ጦርነት አውጆብኃል።
የተከበርከው የኢትዮጵያ ህዝብ ሆይ!!
የወልቃይት ጠገዴ ህዝብ የትግራይ ተስፋፊ ኃይል ባወጀው ጦርነት ምክንያት ከፍተኛ ስጋት ውስጥ ገብቷል። ከአሁን በፊት የወልቃይት ጠገዴ ህዝብ ስቃዩ ስቃዬ፣ በደሉ በደሌ ነው ብለህ ከፍተኛ ዋጋ ከፍለኃል። ይህን የወልቃይት ጠገዴ ህዝብ ያደንቃል እውቅናም ይሰጣል። ኃብት ማፍራት ይሁን በህይወት መኖር መኖርም አገር ሲኖር ነውና፤ ይህንን አገር አጥፊ ወራሪ ቡድን ለመመከት በምናደርገው ተጋድሎ ከጎናችን እንድትቆም ጥሪያችን እናስተላልፋለን።
ይህንን የወልቃይት ጠገዴ አማራ ማንነት አስመላሽ ኮሚቴ ጥሪ ተቀብያለሁ የሚል ሁሉ የአንድ ወር ስንቅ በማዘጋጀት በየቤቱና በየቀበሌው ሆኖ ለምናቀርበው የፈጥነህ ድረስ ጥሪ ዝግጁ ሆኖ እንዲጠብቅ ሲል ኮሚቴው መልዕክቱን ያስተላልፋል።
''ከአማራነታችን ዝቅ የሚያደርገን ምድራዊ ኃይል የለም!!''

የወልቃይት ጠገዴ አማራ ማንነት አስመላሽ ኮሚቴ ሰብሳቢ

ኮ/ል ደመቀ ዘውዱ አየለ

ንሥር ብሮድካስት የሁላችንም ድምፅ!
ወቅታዊ ፤ ትኩስ እና የተሟላ መረጃዎችን ለማግኘት
Youtube:https: https://bit.ly/3No0s7x
FaceBook:https://www.facebook.com/Nisirbroadcasting
Telegram:https://t.me/nisirbroadcasting Website: https://nisirbroadcasting.com
Twitter:https://twitter.com/NISIRInternati1
1.5K views04:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-01 07:10:24
ህፃናትን ለጦርነት የሚማግደው የህውሃት ጦርነት
1.5K views04:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 23:02:30
ግንባር ላይ እየተዋደቁ ነው:: በአካባቢው ምግብ የሚያቀርብላቸው የለም ነገር ግን በደረቅ ራሽን ትግላቸውን ቀጥለዋል:: የምሥራቅ ዐማራ ፋኖን መደገፍ ለምትችሉ:: ሸርም አድርጉ

ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
የባንክ ሂሳብ ቁጥር
1000485333146

ምሬ ወዳጆ (የምሥራቅ ዐማራ ፋኖ ዋና አዛዥ) ከድር ሰይድ (ምክትል አዛዥ) እና
መሰረት ጫኔ (ሃብት አፈላላጊ)
521 views20:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 22:55:25
ህገወጥ ስብሰባ በባህር ዳር ይላል ደብዳቤው
*************

ለሚመለከተው ይድረስ ብለዋል

ጉዳዩ - ህገወጥ ስብሰባን ይመለከታል

በርዕሱ እንደተጠቀሰዉ ራሱን የኢት / እስ / ጉ / ጠ / ም / ቤት ብሎ የሰየመው ቡድን በህገወጥ መንገድ ለነሃሴ 26/2014 ዓ.ም በባህርዳር ከተማ h ተለዩ ቦታዎች ሰዎችን በመጥራት ህገወጥ ስብስባ በማድረግ የክልሉን አስ / ጉ / / ም / ቤት መፈንቅለ መጅሊስ ለማድረግ ዕቅድ መያዙን ተገንዝበናል ፡፡ በመሆኑም የሚካሄደው ስብሰባ የክልሉ እስ ጉ ከ ም / ቤት የማያውቀው እና የማይቀበለው በመሆነ እንዲሁም ክልላችን ያለበትን ነባራዊ ሁኔታ እንደ መልካም አጋጣሚ በመጠቀም ግጭት እና ሁከት እንዲነሳ ጽኑ ፍላጎት ያለው መሆኑን በተግባር እያሳየ ሲሆን የክልሉ መንግስት ጉዳዩ ሃይማኖታዊ ብቻ ላይሆን ሃገራዊ ትርጉም በመስጠት ይህ ስብሰባ እንዳይካሄድ እየገለጽን ሆኖም ይህ ቡድን በራሱ መንገድ ስበሰባውን በማካሄድ ለሚፈጠረው ችግር የክልሉ እስ / ጉ / h / ም / ቤት ኃላፊነት የማይወስድ መሆኑን ከወዲሁ በአክብሮት እንገልጻለን ፡፡
ግልባጭ፦
-ለባህርዳር ከተማ አስ / ንቲባ
-ለባህርዳር ከተማ አስ/ሰ / ህ ጉዳዮ
- ለባህርዳር ከተማ አስፖሊስ መምሪ
-ለም / ቤታችን ኘፊዝዳንት-
- ለም ቤታችን ለዋና ፀሀፈ
ባህር ዳር
588 views19:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 22:16:22 ንሥር እለታዊ ዜና _ Aug 31/2022

928 views19:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ