Get Mystery Box with random crypto!

NiSiR Int. Broadcasting Co. (Official Telegram Channel)

የቴሌግራም ቻናል አርማ nisirbroadcasting — NiSiR Int. Broadcasting Co. (Official Telegram Channel) N
የቴሌግራም ቻናል አርማ nisirbroadcasting — NiSiR Int. Broadcasting Co. (Official Telegram Channel)
የሰርጥ አድራሻ: @nisirbroadcasting
ምድቦች: ዜና
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 14.71K
የሰርጥ መግለጫ

NISIR International Broadcasting Co. is an impartial and independent media agency operates as television; radio; social media & multimedia production.
Facebook: https://www.facebook.com/NISIR-International-Broadcasting-Corporation-105276671420707

Ratings & Reviews

3.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 242

2022-09-05 08:52:12
ሰላም የጥይት መቆም ብቻ አይደለም፤
****ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ****

ንሥር ብ
ሮድካስት
ነሃሴ 30/2014

ሰላም የጥይት መቆም ብቻ አይደለም፤ ሰላም መገንባት አለበት። ብዙ ሥራ አለብን። የችግሮቻችን መንስኤ ላይ መግባባትና መልሶ እንዳይደገም ማድረግ አለብን።

እኛ እንደ ሃገር የምንጨቃጨቀው በሐሳብ ልዕልና ስለማናምን ነው። ያንን ማድረግ ብንችል ለሰላምና ለአገር እድገት እንጠቅም ነበር ብለዋል።

2015 የሰላም ያድርግልን ሲሉም ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ በመድረኩ መልካም ምኞታችውን አስተላልፈዋል በዐስረኛው የበጎ ሰው ሽልማት መርሃ ግብር በክብር እንግድነት የተገኙት ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ።

ንሥር ብሮድካስት የሁላችንም ድምፅ!

ወቅታዊ ፤ ትኩስ እና የተሟላ መረጃዎችን ለማግኘት
Youtube:https: https://bit.ly/3No0s7x
FaceBook:https://www.facebook.com/Nisirbroadcasting
Telegram:https://t.me/nisirbroadcasting Website: https://nisirbroadcasting.com
Twitter:https://twitter.com/NISIRInternati1
2.3K views05:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-05 06:09:00 አማራነት ስንል ሰው-ነት፣ ህግነት እና ህገመንግስትነት ማለታችን ነው። ይህን ስንል ዐማራ፣ የተጎዳ ሰው ሲያገኝ እኔን ይድፋኝ ብሎ የሰውን ችግር እንደራሱ የሚያይ የሞራል ልዕልና ያለው ህዝብ ነው።

========በታደለ ጥበቡ=======

"እንኳን ሰው ወፍ አለምዳለሁ" የሚል እንግዳ ተቀባይ (hospitable)፣ ለሃይማኖቱ ቀናኢ፣ ሠላማዊ፣ ፍቅር፣ ለጋሽ፣ ቸር፣ አቃፊ፣ አልቦና ጠምቆ የሚያጠጣ፣ አምርቶ አገር የሚቀልብ፣ ፈትሎና ሸምኖ አገር የሚያለብስ በጣም የዳበረ ባህል (rich culture) ያለው ህዝብ ነው። እንኳን ለሀገርና ለወገን ደሙን እያፈሰሰ አጥንቱን እየከሰሰ ላለ ሠራዊት ቀርቶ በዐማራ ባህል መሽቶበት ማረፊያ የጠየቀ እንግዳ ወይም መንገደኛ የእግዚአብሔር እንግዳ ነው። የደከመው ያርፍበታል፣ የተጠማ ይጠጣበታል፣ የተራበ ይበላበታል፣ የታረዘ ይለብስበታል፣ የተከዘ ይጽናናበታል። ከአልጋ ወርዶ፣ እልፍኝ ለቆ እንግዳ መቀበል የዐማራ ህዝብ ማህበራዊ ቅርሱ ነው። ዶናልድ ሌቪን Wax and Gold በተባለው መጽሐፉ ስለ ዐማራ እንግዳ ተቀባይነትና አክባሪነት ሚከተለውን ጽፏል፣

"በዐማራ ዘንድ የእግዜር እንግዳን ተቀብሎ ከራስ በላይ አስተናግዶ ማሳደር የተለመደ ማኅበራዊ መገለጫ ነው። የእግዜር እንግዳ ሲመጣ እግሩን ይታጠባል፤ ቡና ይጠጣል፤ ጠላ ይጠጣል፤ ጥሩ ምግብ ይበላል፤ በባለቤቶቹ መኝታ ላይ ተነጥፎለት እስከመተኛት መስተንግዶ ይደረግለታል። እሱ ብቻ ሳይሆን የጭነት ወይም የኮርቻ ከብት ይዞ እንደሆን እንክብካቤን ያገኛሉ። እንግዳ ወዳድ በመሆናቸው 'ብሉ እንጅ፤ ጠጡ እንጅ' የሚሉ አገላለጾችን ይጠቀማሉ። ይሄ መስተንግዶ ለዘመድ፣ ለወዳጅ ለጓደኛ ለማንኛውም ሰው ሊደረግ የሚችል ነው። (Wax and Gold፣ 246)

ዐማሮች እጅግ በጣም እንግዳ ወዳድ በመሆናቸው ሲያስተናግዱ እንግዳ በልቶ የጠገበ፤ ጠጥቶ የረካ ስለማይመስላቸው በፈገግታ፣ በትህትና፣ በፍቅርና በአክብሮት "አፈር ስሆን፣ ብሉ እንጅ፣ ጠጡ እንጅ" የሚል አገላለጽ ይጠቀማሉ። ይህም የመንፈሳዊ ሥልጣኔ (moral civilization) መገለጫ ነው።

የዛሬ ዓመት የሀገር መከላከያ ሠራዊት ከትግራይ ሲወጣ የዐማራ ሕዝብ እጅ እየነሳ፣ እያጎረሰ፣ እየዳበሰ፣ ሲቀበላቸው እንባቸውን መቆጣጠር አቅቷቸው ሲያለቅሱ አይተናል።

ዐማራ ጀግናን ማጀገን ያውቅበታል እና ክብር ለሚገባው ክብር ሰጥቷል፡፡ ፍቅር ለሚገባው ፍቅር አሳይቷል፡፡ በመከራውም ቀን አብሮት ሊዘልቅ ቃሉን አጽንቷል፡፡ ዐማራ በልኩ ተገኘ። ደግነቱን አሳዬ፡፡ ጀግናው ወታደርም ስለ ፍቅር አንጀቱ ተላወሰ፡፡ እንባ ከዓይኖቹ አፈሰሰ፡፡

በወቅቱ አንድ የመከላከያ ሠራዊት አባል በውስጥ መስመር እንዲህ የሚል መልእክት ነበር የላከልኝ፤

"የደቡብ ተወላጅ ነኝ። በትግራይ ምድር ለግዳጅ ከ6 ወር በላይ ቆይቻለሁ። በእነዚህ ወራቶች ራሱ ህዝቡ ወግቶናል፣ በውሃ እና በምግብ ላይ መርዝ እየጨመሩ ገድለውናል። በተሳሳተ መንገድ እየመሩ አስከብበውናል። ከዛ ሁሉ ከባድ ትግል ወጥተን ወደ አማራ ክልል ስንገባ ህዝቡ በነቂስ ወጥቶ በመንገድ ዳር ቆሞ እያጨበጨበ ተቀበለን። ምሳ ወይንም ቁርስ ልንበላ በወረድንበት ሁሉ ህዝቡ በየቤቱ እንጀራ እያዋጣ ነው የመገበን። በትግራይ ምድር ከባዱን ፈተና ያሳለፉ የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት አባላት ውስጣቸው ተነክቶ ሲያለቅሱ አይቻለሁ። በርግጥ ቢያለቅሱ አይገርምም። ከኋላው ሲወጋ የነበረ ሠራዊት፣ እንኳን ደህና መጣችሁ፣ አፈር ስሆን፣ በሞቴ ብሉልኝ ጠጡልኝ
ሲባል ባያለቅስ ነበር የሚገርመው። ባጠቃላይ የዐማራ ህዝብ ላደረገልን አቀባበል፣ ግብዣና ላሳየን ፍቅር እኔና ጓደኞቼ ማመስገን እንፈልጋለን። ይሄን መልእክት አደራ አድርስልን"

ዐማራ ዛሬም ለወገን ጦር ደጀንነቱን አጠናክሮ ቀጥሎበታል። ሩሲያዊው እስክንድር ቡላቶቪች እንዳለው "ዐማራን እግዚአብሔር ይሁነው"
2.5K viewsedited  03:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-05 06:08:56
2.2K views03:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-05 05:46:09
ከደሴ ከተማ አስተዳደር የተላለፈ ውሳኔ

ንሥር ብሮድካስ
ነሃሴ 30/2014

ከደሴ ከተማ አስተዳደር የፀጥታ ምክር ቤት የተላለፈ ተጨማሪ ውሳኔ ።

ደሴ - ነሀሴ 29/2014 ዓ.ም ( ደሴ ኮሚኒዩኬሽን )

የደሴ ከተማ አስተዳደር ነሀሴ 22/2014 ዓ.ም በከተማው ልዩ ልዩ  ክልከላዎችን በማስቀመጥ የተቀመጡ ህጎችን እያስተገበረ ይገኛል።

እነዚህ ህጎች እንደተጠበቁ ሆነው በተጨማሪ ከነሀሴ 30/2014 ዓ.ም ጀምሮ ተግባራዊ የሚሆኑ ተጨማሪ ክልከላዎችን ያስቀመጥን መሆኑ ታውቆ ህዝቡ ተባባሪ እንድሆን እንጠይቃለን።

1ኛ- የመከላከያ አባል ሳይሆን የመከላከያን የደንብ ልብስ መልበስ ፣ የአማራ ልዩ ኃይል አባል ሳይሆን የልዩ ኃይሉን የደንብ ልብስ ለብሶ በከተማው ውስጥ መንቀሳቀስ ፈፅሞ የተከለከለ ነው ።  የመከላከያም ሆነ የአማራ ልዩ ሀይል አባል ሳይሆን  የደንብ ልብሱን ለብሶ ሲንቀሳቀስ የተገኘ በህግ ተጠያቂ ይሆናል ።

2ኛ - ከደሴ ከተማ አስተዳደር  የፀጥታ መዋቅር ውጭ  ተፈናቃይ በመሆን የመጥታችሁ በከተማው በየትኛውም ቦታ  የጦር መሳሪያ ይዞ መንቀሳቀስ በፍጹም የተከለከለ ነው ፡፡ 

3ኛ- ሀሰተኛ ወሬ በመልቀቅ የጥምር ጦሩን ስም ማጠልሸት ፈፅሞ የተከለከለ ሲሆን ይህን ተላልፎ የተገኘ  በህግ ተጠያቂ ይሆናል ።

ለዚህም የከተማው ማህበረሰብ አሉባልታዎችን በተለያዩ ተቋማት በማሰራጨት ህዝቡን ለማደናገጥ ወይም ጥላቻ ለማሳደር የሚሰሩ ኃይሎችን ለፀጥታ ሀይሉ  ጥቆማ እንዲያደርጉ  እናሳስባለን፡፡

4ኛ- ፀጉረ ልውጥ የሆነ ሰው በምናገኝበት ሰአት ማህበረሰባችን  በአቅራቢያው ለሚገኝ የፀጥታ አካል የመጠቆምና የማቅረብ ኃላፊነት ይኖርበታል  ።

5ኛ- በከተማችን የሚገኝ ማንኛውም የመንግስት እና የግል ታጣቂ  በመንግስት አደረጃጀት ውስጥ በመካተት በየደረጃው ያለ የፀጥታ አካላት በሚሰጠው ስምሪት አካባቢውን የመጠበቅ ኃላፊነትና ግዴታ አለበት ።

6ኛ-  ማንኛውም አካል ከመንግስት አደረጃጀት ውጭ ለጦርነቱ በሚል ገንዘብ መሰብሰብ ፈፅሞ የተከለከለ ሲሆን ከመንግስት ዕውቅና ውጭ የገንዘብ ድጋፍ የሚያደርግ አካል ሊኖር አይገባም ። ሆኖም መንግስት ወጣቱንም ፣ ባለሀብቱን ፣ መንግስት ሰራተኞችና አመራሮችን ወዘተ በማሳተፍ የራሱን የመንግስት አደረጃጀት ተጠቅሞ ለጥምር ጦሩ የሎጅስቲክ ድጋፍ በዓይነትም ሆነ በገንዘብ በህጋዊ ደረሰኝ ከህዝቡ እየሰበሰበ ጥምር ጦሩ ውስጥ እየተሳተፈ ለሚገኝ ማንኛውም ኃይል ይጠቀምበት ዘንድ ያስረክባል ። 

7ኛ- በማንኛውም ሰዓት ታርጋ ቁጥር የሌለው ተሽከርካሪ ከተማ ውስጥ ሲንቀሳቀስ ከተገኘ በቁጥጥር ስር ውሎ ህጋዊ እርምጃ ይወሰድበታል ።      
                           
የደሴ ከተማ አስተዳደር  የፀጥታ ምክር ቤት

ነሐሴ 29 ቀን 2014 ዓ.ም.

ደሴ

ንሥር ብሮድካስት የሁላችንም ድምፅ!

ወቅታዊ ፤ ትኩስ እና የተሟላ መረጃዎችን ለማግኘት
Youtube:https:  https://bit.ly/3No0s7x
FaceBook:https://www.facebook.com/Nisirbroadcasting
Telegram:https://t.me/nisirbroadcasting Website: https://nisirbroadcasting.com
Twitter:https://twitter.com/NISIRInternati1
2.2K views02:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-05 05:42:09
ንሥር ብሮድካስት
ነሃሴ 30/2014 ዜና

በአፍሪካ ቀንድ የአሜሪካ ልዩ መልዕክተኛ ማይክ ሐመር ነገ እሁድ ወደ ኢትዮጵያ እንደሚጓዙ የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት አስታወቀ። አምባሳደር ማይክ ሐመር ከነሐሴ 29 ቀን 2014 እስከ መስከረም 5 ቀን 2015 ድረስ በኢትዮጵያ በሚያደርጉት ቆይታ "በአፋጣኝ ግጭት እንዲቆም እና የሰላም ንግግር እንዲጀመር ግፊት ያደርጋሉ" ተብሏል።
የፕሬዝደንት ጆ ባይደን አስተዳደር በትላንትናው ዕለት “ኤርትራ ወደ ግጭቱ ተመልሳ መግባቷን" አውግዟል። የዋይት ሃውስ ቃል አቀባይ ካሪን ጄን ፒየር አሜሪካ "ህወሓት ከትግራይ ውጪ የሚፈጽመውን ማጥቃት እና የኢትዮጵያ መንግስትን የአየር ድብደባ” እንደምታወግዝ ለጋዜጠኞች ተናግረዋል።
የኢትዮጵያ መንግሥት እና ህወሓት በደረሱበት ለሰብዓዊነት ተኩስ የማቆም ሥምምነት ለአምስት ወራት ጋብ ብሎ የቆየው ውጊያ እንደገና የተቀሰቀሰው ባለፈው ነሐሴ 18 ቀን 2014 ነበር። አሜሪካ እና የአውሮፓ ኅብረትን ጨምሮ ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ሁለቱ ወገኖች ውጊያውን አቁመው ድርድር እንዲጀምሩ ተደጋጋሚ ጥሪዎች በማቅረብ ላይ ይገኛል። "ለግጭቱ ወታደራዊ መፍትሔ የለውም" ያሉት የዋይት ሐውስ ቃል አቀባይ ካሪን ጄን ፒየር "ሁሉም ወገኖች እንዲታቀቡ እና እንዲያረግቡ" ጥሪ አስተላልፈዋል።
አምባሳደር ማይክ ሐመር በአዲስ አበባ ቆይታቸው የኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ኅብረት ባለሥልጣናትን ያገኛሉ። ልዩ ልዑኩ ከኢትዮጵያ ክልሎች ከተውጣጡ ተወካዮች ጋር እንደሚመካከሩም የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት አስታውቋል። ዘገባው የ DW ነው::

ንሥር ብሮድካስት የሁላችንም ድምፅ!

ወቅታዊ ፤ ትኩስ እና የተሟላ መረጃዎችን ለማግኘት
Youtube:https: https://bit.ly/3No0s7x
FaceBook:https://www.facebook.com/Nisirbroadcasting
Telegram:https://t.me/nisirbroadcasting Website: https://nisirbroadcasting.com
Twitter:https://twitter.com/NISIRInternati1
2.3K views02:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-04 21:01:49
***^Complicated****

*የዚህ ጦርነት ድራማ መቼ ይሆን የሚያቆመው?
*ህውሃት ስትሸኝ ሁሉም ከሚንደረደር መጀመሪያስ ለምን አያስቆሙትም ነበር?

*ጥርት ያለ ቁመና የሌለው የፌደራል መንግስትስ እስከመቼ ነው በአማራና የአፋርን ህዝብ የሚደራደር?

* በጥቂትቡድኖች ድራማ ለምን ወገኖቻችን የህይወት መስዋትነት ይከፍላሉ?

*አፋርና አማራ በጦርነት መድቀቅ የሚያስከትለው የወደፊት ውጥንቅጥስ ሃገር እንደ ሃገር እንድትቀጥል ያስችላልን?

*የአማራ ህዝብስ ከእንቅልፍ መቼ ነው የሚነቃ?
ከእንቅልፍ መቼ ነው የሚነቃ?

****************
ነሃሴ 29/2014 ዜና

በአፍሪካ ቀንድ የአሜሪካ ልዩ መልዕክተኛ ማይክ ሐመር ነገ እሁድ ወደ ኢትዮጵያ እንደሚጓዙ የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት አስታወቀ። አምባሳደር ማይክ ሐመር ከነሐሴ 29 ቀን 2014 እስከ መስከረም 5 ቀን 2015 ድረስ በኢትዮጵያ በሚያደርጉት ቆይታ "በአፋጣኝ ግጭት እንዲቆም እና የሰላም ንግግር እንዲጀመር ግፊት ያደርጋሉ" ተብሏል።
የፕሬዝደንት ጆ ባይደን አስተዳደር በትላንትናው ዕለት “ኤርትራ ወደ ግጭቱ ተመልሳ መግባቷን" አውግዟል። የዋይት ሃውስ ቃል አቀባይ ካሪን ጄን ፒየር አሜሪካ "ህወሓት ከትግራይ ውጪ የሚፈጽመውን ማጥቃት እና የኢትዮጵያ መንግስትን የአየር ድብደባ” እንደምታወግዝ ለጋዜጠኞች ተናግረዋል።
የኢትዮጵያ መንግሥት እና ህወሓት በደረሱበት ለሰብዓዊነት ተኩስ የማቆም ሥምምነት ለአምስት ወራት ጋብ ብሎ የቆየው ውጊያ እንደገና የተቀሰቀሰው ባለፈው ነሐሴ 18 ቀን 2014 ነበር። አሜሪካ እና የአውሮፓ ኅብረትን ጨምሮ ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ሁለቱ ወገኖች ውጊያውን አቁመው ድርድር እንዲጀምሩ ተደጋጋሚ ጥሪዎች በማቅረብ ላይ ይገኛል። "ለግጭቱ ወታደራዊ መፍትሔ የለውም" ያሉት የዋይት ሐውስ ቃል አቀባይ ካሪን ጄን ፒየር "ሁሉም ወገኖች እንዲታቀቡ እና እንዲያረግቡ" ጥሪ አስተላልፈዋል።
አምባሳደር ማይክ ሐመር በአዲስ አበባ ቆይታቸው የኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ኅብረት ባለሥልጣናትን ያገኛሉ። ልዩ ልዑኩ ከኢትዮጵያ ክልሎች ከተውጣጡ ተወካዮች ጋር እንደሚመካከሩም የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት አስታውቋል። ዘገባው የ DW ነው::
905 viewsedited  18:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-04 18:42:39 ንሥር እለታዊ ዜና _Sep 4/2022

1.7K views15:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-04 12:39:06
ከንሥር እንግዳ-የውጭ ባንኮች
ነሐሴ 29/2014
****************

መንግስት ሊበራል ነኝ ለማለት እየሄደበት ያለው ውሳኔ በፍፁም ኢኮኖሚውን ሊያሳድገው አይችልም።

በመሰረታዊነት የሃገር ውስጥ የፋይናንስ ተቋማት ተወስነው የሚገኙት አንድ ቦታ ላይ ብቻ መሆኑ የፋይናንስ ተደራሺነቱን ኢፍትሃዊ አድርጎታል።

በመሆኑም የውጭ ባንኮች በዚህ ደረጃ ሃገር ውስጥ ገብተው እንድሰሩ ፍቃድ ከመስጠት ይልቅ የሃገር ውስጥ ባንኮችን በስርዓቱ መደገፍ እና ከፓለቲካ እና ከ ባለ አክሲዮኖች ጣልቃ ገብነት እንዲወጡ በማድረግ በሙያቸው አስተማማኝ የዕውቀት ክህሎት ላይ ትኩረት አድርጎ መስራት ጠቃሚ ነበር።

ነገር ግን መንግስት ከዶላር እጥረት እና ከውጭ እዳ ስረዛ ጋር በተያያዘ ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ተቋማት ተፅዕኖ ስላሳደሩ ብቻ ይህንን ውሳኔ መስጠት በሃገሪቱ ኢኮኖሚ ላይ ተፅዕኖ የሚያሳድር ነው።


ስለሆነም የፋይናንስ ተቋማት ችግራችን መነሻው አብዛኛው ማህበረሰባችን በቂ ግንዛቤ የሌለው መሆኑ እና አሁንም ቢሆን የቁጠባ ሁኔታዎች በባህላዊ መንገድ እየተመሩ በመሆኑ ነው።
ይህንን ሁኔታ በጥልቀት ማስገንዘብ የፋይናንስ ተቋማት ድርሻ ቢሆንም አንዳንድ የፋይናንስ ሴክተር አዋቂዎችም መዋቅራቸውን ዘር እና ሃይማኖት እየሆነ መምጣቱ የፋይናንስ ተቋማቱን ወጥ ዕድገት የሚቀለብሰው ሆኗል።

ስለሆነም የሚኒስትሮች ም/ቤት ውሳኔ ጊዚያዊ ችግርችን ከመቅረፍ አኳያ ጠቃሚ ሊሆን ይችላል።
ነገር ግን ኢኮኖሚውን ከማሳደግ አንፃር ተጨማሪ ስጋት ነው።

የውጭ ባንኮችን ጫና በተመለከተ ኬንያን፣ኮንጎን፣ማሊን እንደ ምሳሌ መወሰድ ይቻላል።

በፈረንሳይ ባንኮች ኢኮኖሚዋን እየተዘረፈች ያለችው ኮንጎ አሁንም ዕጅግ ድሃ ማህበረሰብን ይዛለች።
በዚህም የውስጥ ፓለቲካዋ ሳይቀር በፈረንሳይ ባለሀብቶች ጫና ውስጥ ትገኛለች።
ኬንያም በእንግሊዝ ካምፓኒዎች እና ባንኮች የሃገር ውስጥ ጫና እየተደረገባት ነው።
የአሜሪካ ጣልቃ ገብነትም እንድሁ የኬንያን የሃገር ውስጥ ኢኮኖሚ እና የውስጥ ደህንነት እየተፈታተናት ነው።

ስለዚህ ኢትዮጵያም ማህበራዊ ተግዳሮቷን ለመፍታት ከመሰል እንቅስቃሴዎች ብትቆጠብ ጥሩ ነው።
ውሳኔዋንም ከፕራይቬታዜሺን አንፃር ቢሆንም ከህዝቧ ሰላም እና ከውስጥ ደህንነቷ አንፃር ራሷን ብትመረምር አዋጭ ሃሳብ ነው የሚል ግምት አለኝ።

የውጭ ተቋማት እንደ ኢትዮጵያ ያሉ ብዙ ብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች በሚኖሩባት ሃገር ውስጥ ከፓለቲካ ጣልቃ ገብነታቸው እና ከውጭ ድፕሎማሲያቸው አንፃር ጠቃሚ አይደለም።

በመሰረታዊነት የሃገሪቱ ኢኮኖሚ አለማደግ እና የሰላም እጦት ዋነኛ ምክንያት የውጭ ተቋማት እና የምዕራባውያን ፓለቲካዊ ጣልቃ ገብነት ነው።

በምስራቅ አፍሪካ የተሻለ ጅኦ ፓለቲካዊ እንቅስቃሴ ያላትን ሃገር ድሃ እና ዜጎቿ እርስ በዕርሳቸው እንድታኮሱ ያደረጉ ሃይሎችን ፍላጎት ለማሟላት ሲባል የውጭ ባንኮች እንድገቡ መፍቀድ የምዕራባውያንን ሃሳብ እና የውስጥ ጣልቃ ገብነታቸውን በቀጥታ ይሁንታ መስጠት ነው።

መንግስት በጊዚያዊ ችግሮች እየተሺመደመደ የውስጥ ሰላሙን እና የሃገሪቱን አንድነት ለመብተን ከሚሰሩ ሃይሎች ያልተናነሰ ውሳኔውን አሳርፏል።

የኢኮኖሚስት ባለሙያዎች ጊዚያዊ ችግሩን ሳይሆን የውስጥ ጣልቃገብነቱን ጫና ጭምር ቢያጤኑት መልካም ነው እላለሁ።
2.8K views09:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-04 11:08:03 ሰበር ዜና የምስራቅ አምሐራ ፍኖና የቤተ አምሐራ ፋኖ በአንድ ላይ ለመስራትና ለመታገል በግንባር ላይ ውይይት አደረጉ።

989 views08:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-04 09:49:14
አቶ ስንታየሁ ቸኮል ለ4ኛ ጊዜ መታፈናቸው ተሰማ

ንሥር ብሮድካስ
ነሃሴ 28/2014

የባልደራስ ለእውነተኛ ዲሞክራሲ ፓርቲ የድርጅት ጉዳይ ኃላፊና የስራ አስፈፃሚ አባል የሆኑት አቶ ስንታየሁ ቸኮል በትናንትናው ዕለት መርማሪ ፖሊስ ይግባኝ ማለቱን ተከትሎ ጠቅላይ ሰበር ሰሚ ችሎት መቅረባቸው ይታወሳል።

በመሆኑም ሰበር ሰሚ ችሎቱ አቶ ስንታየሁ ቸኮል በ10ሺህ ብር ዋስትና ከፍለው እንዲወጡ የስር ፍ/ቤቱ የሰጠውን ብይን በትናንትናው ዕለት በማፅናት እንዲፈቱ ወሰኗል።

ይሁን ዕንጅ የሀገሪቱ የመጨረሻው ፍ/ቤት ለሰጠው ብይን "አንገዛም" በማለት የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን(የኦህዴድ ብልፅግና የአፈና ቡድን) ትናንት ምሽት ከዕስር ቤት ለአራተኛ ጊዜ አፍነው ወደ ካዛንችስ 6ኛ ፖሊስ ጣቢያ ወስደውታል። ዛሬም በአካባቢው የመጀመሪያ ፍ/ቤት በተመሳሳይ ክስ አቅርበው እያንገላቱት ይገኛል።

አቶ ስንታየሁ ቸኮል ከባህርዳር ማረሚያ ቤት ጀምሮ እስከ አዲስ አበባ ድረስ ሶስት ጊዜ በፍ/ቤቶች ነፃ ቢባልም ተረኛው ስርዓት ግን አሁንም በኃይል አፍኖ ለአራተኛ ጊዜ አስሮታል።

አቶ ስንታየሁ ቸኮል አስካሁን ድረስ ለአራት ወራት የታሰረ ሲሆን በጠቅላላው 140 ሺህ ብር ለዋስትና ከፍሏል።

ንሥር ብሮድካስት የሁላችንም ድምፅ!

ወቅታዊ ፤ ትኩስ እና የተሟላ መረጃዎችን ለማግኘት
Youtube:https:  https://bit.ly/3No0s7x
FaceBook:https://www.facebook.com/Nisirbroadcasting
Telegram:https://t.me/nisirbroadcasting Website: https://nisirbroadcasting.com
Twitter:https://twitter.com/NISIRInternati1
1.5K views06:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ