Get Mystery Box with random crypto!

ከደሴ ከተማ አስተዳደር የተላለፈ ውሳኔ ንሥር ብሮድካስ ነሃሴ 30/2014 ከደሴ ከተማ አስተዳደ | NiSiR Int. Broadcasting Co. (Official Telegram Channel)

ከደሴ ከተማ አስተዳደር የተላለፈ ውሳኔ

ንሥር ብሮድካስ
ነሃሴ 30/2014

ከደሴ ከተማ አስተዳደር የፀጥታ ምክር ቤት የተላለፈ ተጨማሪ ውሳኔ ።

ደሴ - ነሀሴ 29/2014 ዓ.ም ( ደሴ ኮሚኒዩኬሽን )

የደሴ ከተማ አስተዳደር ነሀሴ 22/2014 ዓ.ም በከተማው ልዩ ልዩ  ክልከላዎችን በማስቀመጥ የተቀመጡ ህጎችን እያስተገበረ ይገኛል።

እነዚህ ህጎች እንደተጠበቁ ሆነው በተጨማሪ ከነሀሴ 30/2014 ዓ.ም ጀምሮ ተግባራዊ የሚሆኑ ተጨማሪ ክልከላዎችን ያስቀመጥን መሆኑ ታውቆ ህዝቡ ተባባሪ እንድሆን እንጠይቃለን።

1ኛ- የመከላከያ አባል ሳይሆን የመከላከያን የደንብ ልብስ መልበስ ፣ የአማራ ልዩ ኃይል አባል ሳይሆን የልዩ ኃይሉን የደንብ ልብስ ለብሶ በከተማው ውስጥ መንቀሳቀስ ፈፅሞ የተከለከለ ነው ።  የመከላከያም ሆነ የአማራ ልዩ ሀይል አባል ሳይሆን  የደንብ ልብሱን ለብሶ ሲንቀሳቀስ የተገኘ በህግ ተጠያቂ ይሆናል ።

2ኛ - ከደሴ ከተማ አስተዳደር  የፀጥታ መዋቅር ውጭ  ተፈናቃይ በመሆን የመጥታችሁ በከተማው በየትኛውም ቦታ  የጦር መሳሪያ ይዞ መንቀሳቀስ በፍጹም የተከለከለ ነው ፡፡ 

3ኛ- ሀሰተኛ ወሬ በመልቀቅ የጥምር ጦሩን ስም ማጠልሸት ፈፅሞ የተከለከለ ሲሆን ይህን ተላልፎ የተገኘ  በህግ ተጠያቂ ይሆናል ።

ለዚህም የከተማው ማህበረሰብ አሉባልታዎችን በተለያዩ ተቋማት በማሰራጨት ህዝቡን ለማደናገጥ ወይም ጥላቻ ለማሳደር የሚሰሩ ኃይሎችን ለፀጥታ ሀይሉ  ጥቆማ እንዲያደርጉ  እናሳስባለን፡፡

4ኛ- ፀጉረ ልውጥ የሆነ ሰው በምናገኝበት ሰአት ማህበረሰባችን  በአቅራቢያው ለሚገኝ የፀጥታ አካል የመጠቆምና የማቅረብ ኃላፊነት ይኖርበታል  ።

5ኛ- በከተማችን የሚገኝ ማንኛውም የመንግስት እና የግል ታጣቂ  በመንግስት አደረጃጀት ውስጥ በመካተት በየደረጃው ያለ የፀጥታ አካላት በሚሰጠው ስምሪት አካባቢውን የመጠበቅ ኃላፊነትና ግዴታ አለበት ።

6ኛ-  ማንኛውም አካል ከመንግስት አደረጃጀት ውጭ ለጦርነቱ በሚል ገንዘብ መሰብሰብ ፈፅሞ የተከለከለ ሲሆን ከመንግስት ዕውቅና ውጭ የገንዘብ ድጋፍ የሚያደርግ አካል ሊኖር አይገባም ። ሆኖም መንግስት ወጣቱንም ፣ ባለሀብቱን ፣ መንግስት ሰራተኞችና አመራሮችን ወዘተ በማሳተፍ የራሱን የመንግስት አደረጃጀት ተጠቅሞ ለጥምር ጦሩ የሎጅስቲክ ድጋፍ በዓይነትም ሆነ በገንዘብ በህጋዊ ደረሰኝ ከህዝቡ እየሰበሰበ ጥምር ጦሩ ውስጥ እየተሳተፈ ለሚገኝ ማንኛውም ኃይል ይጠቀምበት ዘንድ ያስረክባል ። 

7ኛ- በማንኛውም ሰዓት ታርጋ ቁጥር የሌለው ተሽከርካሪ ከተማ ውስጥ ሲንቀሳቀስ ከተገኘ በቁጥጥር ስር ውሎ ህጋዊ እርምጃ ይወሰድበታል ።      
                           
የደሴ ከተማ አስተዳደር  የፀጥታ ምክር ቤት

ነሐሴ 29 ቀን 2014 ዓ.ም.

ደሴ

ንሥር ብሮድካስት የሁላችንም ድምፅ!

ወቅታዊ ፤ ትኩስ እና የተሟላ መረጃዎችን ለማግኘት
Youtube:https:  https://bit.ly/3No0s7x
FaceBook:https://www.facebook.com/Nisirbroadcasting
Telegram:https://t.me/nisirbroadcasting Website: https://nisirbroadcasting.com
Twitter:https://twitter.com/NISIRInternati1