2023-07-06 21:14:12
የ3 የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሆኑ በመቶዎች የሚቆጠሩ ተማሪዎች ለመውጫ ፈተና ወደ አዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ እንደተመደቡ ከተነገራቸውና ወደዛው ካቀኑ በኃላ ዛሬ አመሻሹን ደግሞ አዲስ አበባ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ የተመደቡ መሆኑና ነገ ጥዋት 1 ሰዓት እንዲደርሱ እንደተናገራቸው ጠቁመዋል።
እነዚህ ተማሪዎች የአልካን፣ የልደታ፣ እና የአፍሪካ የፋርማሲ ተማሪዎች ናቸው።
ተማሪዎቹ ወደ አዳማ እንዲሄዱ ሲነገራቸው እያንዳንዱን ወጪ ምግብ፣ እና ትራንስፖርት ጨምሮ እራሳቸው እንደሚሸፍኑ ተነግሯቸው እንደነበር ለቲክቫህ ጠቁመዋል።
አዳማ እንዲደርሱ የተነገራቸው 8 ሰዓት ላይ ሲሆን እዛ ከደረሱ በኃላ የመለማመጃ ፈተና እንደሚፈተኑ፣ የመፈተኛ ክፍላቸውን እንደሚያውቁ፣ ID እንደሚሰጣቸው ተነግሯቸው ነበር ፤ ነገር ግን እኚህ ሁሉ ተማሪዎች የሚያስፈልጋቸውን እቃዎች ይዘው አዳማ ከደረሱ በኃላ ቦታው መቀየሩንና ነገ ጥዋት አዲስ አበባ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ግቢ እንዲደርሱ እንደተነገራቸው ገልጸዋል።
ተማሪዎቹ እንዲህ ያለው እጅግ በጣም ያልተገባ ድርጊት እንዳሳዘናቸው ቅሬታቸውን ገልጸዋል።
ፈተናው በተቃረበበት በዚህ ወቅት መሰል የተንዛዛ አሰራር በፍፁም ሊኖር እንደማይገባና የሚማለከተው አካል የመፍትሄ እርምጃዎችን እንዲወስድ ድምፃቸውን አሰምተዋል።
በነገው ዕለት ወደ አዲስ አበባ ለመመለስ እንደተዘጋጁ መልዕክት የላኩ ተማሪዎች እዛም ሲደርሱ እንዲህ ያለውን ነገር እንዳይገጥማቸው ስጋት እንዳላቸው ጠቁመዋል።
በዚህ አይነት ሁኔታ በፈተና አወሳሰድ ሂደቱ ላይ ችግሮች ቢያጋጥማቸው ተጠያቂነት ሊኖር እንደሚገባ አመልክተዋል።
የተማሪዎቹን ጥያቄ በተመለከተ የተቋሞቻቸውን ኃላፊዎች ለማግኘት ጥረት ብናደርግም አልተሳካም ምላሽ አለኝ የሚል አካል ምላሹን መስጠት ይችላል።
@News_For_Student
@News_For_Student
2.6K views18:14