Get Mystery Box with random crypto!

Muktarovich Ousmanova

የቴሌግራም ቻናል አርማ muktarovichousmanova — Muktarovich Ousmanova
ርዕሶች ከሰርጥ:
Fastmereja
የሰርጥ አድራሻ: @muktarovichousmanova
ምድቦች: ፖለቲካ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 63.74K
የሰርጥ መግለጫ

Ethiopia forever

Ratings & Reviews

2.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 9

2024-03-21 10:57:44
በትግራይ ፤ የወንድ የዘር ፈሳሽ (ስፐርም) ለሚለግሱ ሰዎች 10ሺ ብር ስጦታ ይሰጣል ተባለ

'አዶ' በሚል ስም እሚታወቅ አንድ የግል የህክምና ማዕከል በተፈጥሮአዊ መንገድ ፅንስ ለመቋጠር ላልቻሉት ልጅ እእዲኖራቸው ለማድረግ እየሰራሁት ነው ባለው ስራ ሴት እንስቶች 'እንቁላል' ወንዶች ደግሞ 'የዘር ፍሬ (ስፐርም) እንዲለግሱ ጥሪውን አቅርቧል።

በትግራይ ክልል መቀለ ከተማ መቀመጫውን ያደረገው 'አዶ' የእናቶች፣ ሕጻናት እና የነቃ ሕይወት ሕክምና ማዕከል ይህንን ሕክምና ለመስጠት ዝግጅት የጀመረው ከትግራይ ጦርነት በፊት እንደሆነና ህክምናውን ለመጀመር የተደረገው ጥረት በጦርነቱ ምክንያት ቢቋረጥም ጦርነቱ ሲጠናቀቅ ግን ሂደቱ መቀጠሉን ይገለፃል።

ማዕከሉ በአሁኑ ሰዓት ታድያ ለስራው አስፈላጊ የሆኑ ቅድመ ዝግጅቶች በመከወን ስፐርም እና እንቁላል ለመለገስ ፈቃደኛ የሆኑ ሰዎችን እየጠበቀ ነውም መባሉን ዳጉ ጆርናል ታዝቧል።

የወንድ ዘር ለጋሾች የዘር ፍሬያቸው መጠን ከ 1.5 ሚ/ሊ በላይ መሆን አለበት፣በአንድ ሚ/ሊ ስፐርም ውስጥ ከ15 ሚሊዮን በላይ የወንድ የዘር ህዋስ (sperm cells) መኖር አለበት በተጨማሪም ለጋሾች ለኤችአይቪ፣ ለሄፐታይተስ ቫይረስ እና ሌሎች ተላላፊ በሽታዎች ምርመራ ማድረግ አለባቸውም ብለዋል።

እንቁላል ለሚለግሱ ሴቶች የእድሜ ገደብ እንዳለና እንቁላል ለመለገስ ብቁ የሆኑ ሴቶች በ 20 እና 30 አመት መካከል ናቸው በተጨማሪም ሴት ለጋሾች ቀደም ብለው የወለዱ መሆን አለባቸው ይላሉ ዶ/ር ሳምሶን። ይህ መስፈርት የተቀመጠው ለምን እንደሆነ ሲገልጹም “[የወለዱ ሴቶች] እንቁላሎቻቸው ተፈትነዋል ብለዋል።

የዘገባው የቢቢሲ አማርኛ ነው
15.7K views07:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-21 09:33:25
በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ሆስፒታል አንዲት እናት በአንድ አካል ሁለት ራስቅል የተያያዙ መንታ ልጆች ተገላግላለች።
15.6K views06:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-20 17:24:57
ስልክዎትን ለመቀየር ወይም አዲስ ለመግዛት አስበዋል ?

  አዳዲስ እንዲሁም በመጠኑ ያገለገሉ ስልኮችን ከተሟላ ዋስትና እና ጥገና ጋር ይዘን ቀርበናል ለበለጠ መረጃ ቻናላችንን ይጎበኙ

https://t.me/sellphone2777

0929008292

inbox @bina27

አድራሻ- ቦሌ ከሸገር ህንፃ አጠገብ

ክፍለ ሀገር ላላቸሁ ደንበኞችቻችንም በ DHL መላክ ጀምረናል
17.3K views14:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-20 16:50:46
ንግድ ባንክ በሲስተም ችግር ወቅት በህገወጥ መንገድ ገንዘብ ያወጣችሁ ሰዎች በአንድ ሳምንት ውስጥ ካልመለሳችሁ ክስ መሰርታለሁ ብሏል
17.4K viewsedited  13:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-19 21:31:02
እውቁ የሰርጀሪ ህክምና ባለሙያ ዶክተር በሀይሉ ሀይሉ እሁድ ጠዋት አዲስ አበባ ውስጥ የጠዋት ሩጫ በማድረግ ላይ ሳሉ ግድያ እንደተፈፀመባቸው ታውቋል።

ዝርዝር መረጃውን ከፖሊስ እንጠብቃለን።

ነፍስ ይማር፣ ዶክተር።
Elias Meseret
19.8K views18:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-19 06:58:37
ለቸኮለ ማለዳ! ማክሰኞ መጋቢት 10/2016 ዓ፣ም የዋዜማ ዕለታዊ ዜናዎች

1፤ በጋምቤላ ከተማ ሰሞኑን በጸጥታ ስጋት ሳቢያ የነዋሪዎች የዕለት'ተለት እንቅስቃሴ መገደቡንና ውጥረት መስፈኑን ዋዜማ ከምንጮች ሰምታለች። በከተማዋ ውጥረት የተፈጠረው፣ አንድ የከተማዋ ትራፊክ ፖሊስ አባል ባልታወቁ ታጣቂዎች መገደላቸውን ተከትሎ እንደኾነ ምንጮች ተናግረዋል። በከተማዋ ትናንት አንዳንድ የንግድ ተቋማት ተዘግተው እንደነበርም ለማወቅ ተችሏል።

2፤ የጣና በለስ ስኳር ፋብሪካ በተያዘው ዓመት ምንም ስኳር አለማምረቱን የመንግሥት ዜና ምንጮች ዘግበዋል። ፋብሪካው ስኳር ያላመረተው፣ የኤሌክትሪክ ኃይል ምንጩ የኾነው የቁንዝላ ኃይል ማመንጫ ከአንድ ዓመት ተኩል በላይ ብልሽት ስለገጠመውና በፋብሪካው ላይ የማሽን አቅርቦት እጥረት በመፈጠሩ እንደኾነ ዘገባዎቹ አመልክተዋል። ፋብሪካው ዘንድሮ 183 ሺህ ኩንታል ስኳር እንዲያመርት ታቅዶ የነበረ ሲኾን፣ ከጅምሩ ሲገነባ ግን በቀን 12 ሺህ ቶን ስኳር የማምረት አቅም እንዳለው ተገልጦ ነበር።

3፤ በአሜሪካ ውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት የስነ ሕዝብ፣ ስደትና ፍልሰት ረዳት ሚንስትር ጁሌይታ ኖይስ ትናንት አዲስ አበባ ገብተዋል። ኖይስ፣ ትናንት ከተመድ የሰብዓዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ቢሮ ሃላፊ ራሚዝ አላክባሮቭ እና ከሌሎች የተመድ ሃላፊዎች ጋር ተመድ ለተረጂዎች በሚያቀርባቸው ሰብዓዊ ድጋፎች ዙሪያ መወያየታቸውን በ"ኤክስ" ገጻቸው ገልጸዋል። ረዳት ሚንስትሯ ዛሬና ነገ ከኢትዮጵያ መንግሥት ባለሥልጣናትና ዓለማቀፍ አጋሮች ጋር ስደተኖችን በሦስተኛ አገራት በማስፈር፣ በሰብዓዊ ዕርዳታ፣ ረድዔት ሠራተኞችን ከጥቃት በመጠበቅና ኢትዮጵያ ባለፈው ታኅሳስ ጀኔቫ ላይ በገባቻቸው የስደተኞች ቃል ኪዳኖች ዙሪያ ይወያያሉ።

[ዋዜማ]
20.3K views03:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-18 18:06:32
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሳይበር ጥቃት እንዳልደረሰበት ተገለፀ፡፡
• ባንኩ ጠንካራ የሳይበር ደህንነት ስርዓት አለው ተብሏል፡፡
******

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ መጋቢት 7 ቀን 2016 ዓ.ም በቅርንጫፍ እና በዲጂታል የባንክ አገልግልቶቹ ላይ ለተወሰኑ ሰዓታት የአገልግሎት መቋረጥ ማጋጠሙ ይታወቃል፡፡

ይህን በማስመልከት በዛሬው እለት ጋዜጣዊ መግለጫ የሰጡት የባንኩ ፕሬዚዳንት አቶ አቤ ሳኖ ባንኩ ምንም አይነት የሳይበር ጥቃት እንዳልደረሰበት ገልፀዋል፡፡

ባንኩ ላይ የተለያዩ የሳይበር ጥቃት ሙከራዎች በየጊዜው እንደሚደረጉ እና ባንኩ ባለው እጅግ ጠንካራ የሳይበር ደህንነት ስርዓት እንደሚመከቱ የገልፁት አቶ አቤ አሁን የተፈጠረው ችግር በሲቢኢ ብር እና በሞባይል ባንኪንግ አገልግሎቶች ላይ ተደርጎ በነበረ አዲስ የሲስተም ማሻሻያ ትግበራ ክፍተት መሆኑን ገልፀዋል፡፡

ባንኩ የዲጂታል አገልግሎቶቹን ይበልጥ በማዘመን እና ለደንበኞች ይበልጥ ምቹ ለማድረግ በየጊዜው ማሻሻያዎችን ይተገብራል ያሉት አቶ አቤ፣ አሁን የተፈጠረውን ችግር በማጣራት ላይ መሆኑን ገልፀዋል፡፡

አቶ አቤ በቅርንጫፎች እና በዲጂታል የባንኩ አገልግሎቶች ላይ መቋረጥ የገጠመው ሲስተሙ አልሠራ ባለማለቱ ሳይሆን፣ አዲስ ተግባራዊ ተደርጎ በነበረው የሲስተም ማሻሻያ ሳቢያ በተፈጠረ ክፍተት የተደረጉ ህገወጥ የገንዘብ ዝውውሮችን በመለየት ለማገድ መሆኑን ጨምረው ገልፀዋል፡፡

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሳይበር ደህንነት በተለያዩ ዓለም አቀፍ መመዘኛዎች የደህነነት ማረጋገጫ እንዳገኘ አቶ አቤ ገልፀው፣ በዚህ ረገድ ደንበኞች ስጋት ሊገባቸው እንደማይገባ ገልፀዋል፡፡
14.4K views15:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-18 13:20:15
ልዩ የቴሌግራም ቻናል ጥቆማ
መረጃ ለማድረስ እንዲሁም ለመከታተል ቴሌግራም ተመራጭ እየሆነ ነው
ከሁሉም የሀገሪቱ ክፍል ያልተሰሙ እና አዳዲስ መረጃዎችን ለመከታተል ከስር ያለውን ሊንክ ተጭነው join በማድረግ ተከታተሉ።
ብዙ አዳዲስ መረጃዎችን ታገኛላችሁ እንዲሁም በቻናሉ ማስታወቂያ ብታሰሩ እጅግ አዋጪ ነው።
ቻናሉን ለማግኘት ከስር ያለውን ሊንክ ይጫኑ
https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s
https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s
15.6K viewsedited  10:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-17 20:32:35
የሶማሊያው ፕሬዝደንት አስመራ ናቸው። ሁለቱም ከኢትዮጵያ ጋ ተቃቅረዋል። ሰላም ለኢትዮጵያ፣ ሰላም ለምስራቅ አፍሪካ
18.4K views17:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-17 19:37:36
ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የተሰጠ መግለጫ

መጋቢት 7 2016 ዓ.ም በንግድ ባንክ የዲጅታል የባንክ ሥርዓት ላይ ባጋጠመ ችግር ምክንያት የባንኩ መደበኛ አገልግሎቶች ለተወሰኑ ሰዓታት መቋረጣቸዉ ይታወቃል፡፡

እንደሚታወቀው ቀልጣፋና ደህንነቱ የተጠበቀ አገልግሎት ለመስጠት ባንኮች በሥርዓቶቻቸዉ ላይ በየጊዜዉ የደህንነት ፍተሻ እንዲሁም የማሻሻያ ሥራዎችን ያከናዉናሉ፡፡

በሥርዓቶቹ ላይ በሚከናወን ለዉጦችና ፍተሻዎችም የባንኮች አገልግሎት አልፎ አልፎ ሊቋረጥ ይችላል፡፡

በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በትናንትና ዕለት የተከሰተዉ የአገልግሎት መቋረጥ ከዚሁ ጋር የተያያዘ መሆኑን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ለማረጋገጥ ችሏል፡፡
ችግሩ ከተከሰተበት ሰዓት አንስቶ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን የባንኩን እና የደንበኞቹን ደህንነት ለማረጋገጥ ከፍተኛ ክትትል ሲያደርግ ቆይቷል።
በመሆኑም የባንኩ መደበኛ አገልግሎቶች በአጭር ጊዜ ዉስጥ እንዲጀምሩና ባንኩ ወደተለመደው እንቅስቃሴው እንዲመለስ ማድረግ ተችሏል፡፡
በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ላይ የተከሰተዉ የአገልግሎት መቋረጥ ባንኩ በመደበኛነት በሥርዓቶቹ ላይ በሚያደርገዉ ማሻሻያና ፍተሻ ምክንያት የተከሰተ እንጂ የባንኩን፣ የደንበኞቹን እንዲሁም አጠቃላይ የፋይናንስ ሥርዓቱን አደጋ ላይ የሚጥል ክስተት አለመሆኑን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ለማረጋገጥ ችሏል፡፡
በችግሩ ምክንያት የተከሰቱ የደንበኞች መጉላላትን ጨምሮ ሌሎች ጉዳቶችን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ አስፈላጊዉን ምርመራ በማድረግ ወደፊት ለህብረተሰቡ የሚያሳዉቅ መሆኑን ያረጋግጣል፡፡

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የፋይናንስ ተቋማት የሚጠቀሟቸዉን ሥርዓቶች ደህንነታቻዉ የተጠበቀ፣ አስተማማኝ፣ ቀልጣፋና የደንበኞችን ፍላጎት የሚያሟሉ ስለመሆናቸዉ በየጊዜዉ ክትትልና ቁጥጥር ያደርጋል፡፡
18.6K views16:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ