Get Mystery Box with random crypto!

ABX

የቴሌግራም ቻናል አርማ muhammedseidabx — ABX A
የቴሌግራም ቻናል አርማ muhammedseidabx — ABX
የሰርጥ አድራሻ: @muhammedseidabx
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 8.70K
የሰርጥ መግለጫ

ወደ ቤታችሁ እንኳን መጣችሁ!!

Ratings & Reviews

2.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 63

2021-02-05 21:53:51 በሃሳብ አልጋ ላይ መገላበጥ
ችግር እይፈታም።
ባይሆን ከአልጋ ወርዶ

ዉዱእ አድርጎ ለሶላት መቅረብ ፣ ሁለት ረከዓ ሰግዶ ለዚክር መቀመጥ ፣ ቁርአንን ከፍቶ ማየት፣ እጅን ዘርግቶ መማፀን፣ ሰው በሌለበት እንባን መዝራት፣ ከአላህ ጋር ማንሾካሾክ፣ የሆድ የሆድን ከሱ ጋር ማውራት ... ብዙ ችግር ይፈታል ።

ለሰው ከመንገር ይልቅ ለአላህ መንገር ያረጋጋል።

ችግራችሁ ሳይፈታ ሌሊቱ አይንጋ
ያ ረብ!


http://t.me/MuhammedSeidABX
2.5K viewsedited  18:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-05 14:21:41 ከሰላሳ ዓመት በኋላ ያገኘኝ ጓደኛዬ "አሁንም እዚያው ነህ?" አለኝ።

"በዚሁ አካባቢ ለረጅም ጊዜ መገኘትህ፣ ከዲን ድባብ አለመራቅህ፣ የፅናትህ ሚስጢሩ ምንድነው ?" ብሎ ጠየቀኝ።
"አይምሰልህ ፅናት አይደለም ።" አልኩት ።
"ፅናት አይደለም ተስፋ አለመቁረጥ ነው። ጥንካሬ አይደለም የሞት ሞት መፍጨርጨር ነው። .....
" ፅዱ ለብሼ ካንተ ከመራቅ ቡትቶ ለብሼ ካንተ ጋር መኖርን እመርጣለሁ ጌታዬ።"

ያ ረብ!

http://t.me/MuhammedSeidABX
1.7K viewsedited  11:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-05 10:56:00 የመጀመርያው ባልሽ ይሻልሻል ...

በቀደምለት አንዲት ዘመዴ ጋ ደወልኩኝ፤ ከሰላምታ በኋላ “ተመለስኩ እኮ!” አለችኝ ዜናዉን ለመንገር አንደቸኮለ ሰው፡፡ ወደ ቀድሞ ባሏ መሆኑ ነው፡፡ ሐቂቃ በጣም ደስ አለኝ፡፡ እፎይታ ተሰማኝ፡፡ አልሐምዱ ሊላህ የአንድ ሰው ሀሳብ ተቃለለልኝ። አረ እንኳንም ተመለሰች፡፡ ሐራም አሳዳጅ ተኩላዎች በዝተዋልና እሷ ተመልሳ ተሰተረች፤ ሌሎችንም ከፈተና ጠበቀች፡፡

እስልምና ፍቺን እየጠላው ነው የፈቀደው፡፡ ፍቺን በሦስት የማድረጉ ሚስጢርም ትዳርን ከመፍረስ ለማዳን ነው፡፡ ተጣማሪዎች አጠቃላይ ነገሮችን ካዩና ከገመገሙ በኋላ ቁጭ ብለው እንዲነጋገሩና እንዲማለሱ ዕድል ለመስጠት፡፡
ካገቡ፤ በተለይ ከልጆች መምጣት በኋላ መፋታት ህመሙ ከራስ አልፎ ለልጆች ይተርፋል፡፡ ያ ከመሆኑ በፊት የቻሉትን ያህል መታገሉና መስዋእትነት መክፈሉ ነው የሚበጀው፡፡ ከዚህ አንፃር ከወላጆቻችን ብዙ ልንማር ይገባል፡፡
አንዳንዴ ከትዳር ይልቅ ብቸኝነት ዉስጥ ትልቅ ሰላም ያለ መስሎን ለመፋታት እናስብ ይሆናል፡፡ አሊያም የተሻለ ሰው ልናገባ እንደምንችል ሊሰማን ይችላል፡፡
ግና ብቸኝነት በተለይ በዚህ ዘመን እኛ እንደምናስበው ከትዳር የተሻለ አይደለም፡፡ ከወዲያ ወዲህ ፈተናው ብዙ ነው፡፡ መፍታት ብልግና የሚመስሏቸው ብዙ ናቸው፡፡ ቢከፋም ከነክፋቱና ጭቅጭቁ የትዳር ሕይወት ይሻላል፤ አውቀዉም ይሁን ባለማወቅ ያመከኑት ጎጆ አንድ ቀን ይናፍቃል፡፡ የልጅ ጫጫታ፣ የቤት ሙቀቱ፣ እንግዳው፣ ቤተዘመዱ፣ ጓደኛው፣ ትዝታው ይቀሰቀስና ሆድ ያስብሳል፡፡ ትዳር መጥፎ ቢሆን እንኳ በጣም መጥፎ ከሆነው ብቸኝነት ይሻላል ፡፡

እቤት ለብቻ ሲሆኑ ሸይጣን ነው የሚከበው፤ እሱ ደግሞ ጥሩ ነገር አያሳስብም፤ በተለይ በምሽት ሰዓታት፡፡ ሹሹክታና አካላዊ መዳበስን ጨምሮ ብዙ ነገርን ያስናፍቃል፡፡ ያም እሳቤ ሐራም ላይ ሊጥል ይችላል፡፡ ልጆች ላላት ሴት “ከባሏ ጋር ናት” መባሉ በራሱ ግዙፍ ምስል አለው፡፡ በተቃራኒው ሲሆን ደግሞ አሉታዊነቱ ይጎላል፡፡

ሌላው ካሁኑ ባሌ/ሚስቴ የማይሻል አይኖርም በሚል ፍቺን የሚመርጥም ይኖራል፡፡ እርግጥ ነው የአላህ ረሕመት ሰፊ ነው፡፡ ግና ለምን እንደሆነ አላውቅም ከዚህ አንፃር ያጋጠመኝ ተሞክሮ በአብዛኛው አሉታዊ ነው፡፡ ብዙዎች በዚህ እሳቤ አዲሱ ባልዲ ዉሃ መያዙን ሳያውቁ የመጀመርያዉን ኦሪጅናሉን አውጥተው ጥለዋል፡፡ በርበሬ ነቅለው ቃሪያ ተክለዋል፡፡ የመጀመርያው ባሌ በስንት ጣዕሙ ! የሚሉ ዛሬም ድረስ ብዙ አሉ፡፡
የተሻለ ይኖራል የማለት እሳቤ የሰው ልጅ ሁሉ የሰው ልጅ መሆኑን ከመዘንጋት የመጣ ይመስለኛል፡፡ ሰው “ሰው” የሚሆነው ስለተማረ፣ ስለቀራ፣ ኡስታዝ/ ዳዒ ስለሆነ፣ ታዋቂ ስለሆነ አይደለም፡፡ ሰዉን “ሰው” አድርጎ የሚፈጥረው አላህ ነው፡፡ መልካም ባህሪን የሚያጎናፅፈዉም ጀሉሉ ነው፡፡ “አፈጣጠሬን ያሳመርክ አላህ ሆይ ባህሪዬንም አሳምር” ይላሉ ነቢያችን እንኳ፡፡
አሁንም ቢሆን ያ የልጆችሽ አባት፣ ያ የመጀመርያው ባልሽ የሚሻልሽ መሰለኝ፡፡ ልጅ ከሆነ በሂደት ይበስላል፣ ጃሂል ከሆነ ቀስ ብሎ ያውቃል፣ ሞኝ ከሆነ ልብ ይገዛል ኢንሻአላህ ፡፡ እናም እልህና ፉክክሩን ተዉና ብትማለሱ ነው የሚሻላችሁ ጓደኞቼ፡፡

ዛሬ ዓለም እንኳን ለብቻ ከሰው ጋርም ከብዳለች፡፡ ለብቻ ማደርን ነብያችንም አልመከሩም፤ የሌሊት ብቸኝነት ጓዙ ብዙ ነው፡፡ ብዙ ነገር ያሳስባል፣ ጣሪያ ላይ አፍጦ ያሳድራል፡፡
መለያየት ቀድሞ ላይ ምናባቱ ብለው በድፍረት እንደሚወስኑት አይደለም ወዳጄ፡፡

ትዳር ሲፈርስ ይከፋኛል፡፡ በተለይ የተፋቱ ሴቶች ጉዳይ እጅጉን ያሳስበኛል፡፡ የአንድ ቤት መፍረስ ጉዳቱ ለማኅበረሰብና ለሀገር ሁሉ ነው ብዬ አስባለሁ፡፡ ባልና ሚስት ሲለያዩ አልወድም፡፡ እንኳን ተፋተው ተራርቀው ሊኖሩ ታክሱ ዉስጥ እንኳን ለጥቂት ደቂቃዎች ተለያይተው እንዳይቀመጡ እጨነቅላቸዋለሁ፡፡
የአላህ መልዕክተኛ ያለምክንያት አይደለም፤ ባላቸው የሞተባቸዉን ሴቶች መንከባከብ ትልቅ ምንዳ እንዳለው የሚነግሩን፡፡ ብቸኝነት ከወንዱ ይልቅ ለሴት ልጅ ይከብዳል፡፡
አምላኬ ሆይ በእዝነትህ የተጎዱትን ሁሉ አስብ፡፡

http://t.me/MuhammedSeidABX
1.7K views07:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-04 16:35:54 ስለ አደብ ከተባሉት
‹‹ጊዜን በአደብ ያልያዘ ሰው፣ ጊዜው የተጠላ ይሆናል፡፡›› (ሱፍያን አሥ-ሠውሪ)
‹‹በአደብ የበላይነት ይገኛል -(ግለሰቡ) የበታች እንኳ ቢሆን፤ ልዕልና ያገኛል -የተዋረደ እንኳ ቢሆን፤ ደረጃ ያገኛል -የተገፋ እንኳ ቢሆን፤ ቅርበት ክብረት ያገኛል -አጥንተ ሰባራ እንኳ ቢሆን፡፡ መኳንንትነትን ያገኛል -የተናቀ እንኳ ቢሆን፡፡›
አንድ ፈላስፋ አደበ-ቢስ የሆነ መልከ መልካም ልጅ ተመለከተና እንዲህ አለ፡- ‹‹መሠረት ቢኖረው ኖሮ እንዴት የሚያምር ቤት ነበር!?››
እንዲህ ይባል ነበር፡- ‹‹ከነዚህ ከሦስቱ ጋር ባይተዋርነት አይኖርም፤ጥርጣሬን ከማራቅ፣ ሰውን ካለማስቸገር እና ከመልካም ሥነ-ምግባር (ከአደብ)፡፡››
አንዳንድ ፈላስፋዎች እንዲህ ይሉ ነበር፡- ‹‹አደብ የአዕምሯዊ ብቃት ማሳደጊያ ነው፡፡ አዕምሮ በሌላ በምንም የማያገኘውን ሕያውነት የሚያገኝበት ክትባቱና ቀለቡ ነው፡፡
‹‹አደብን ምን ያህል ይፈልጉታል?›› ሲቀርብላቸው፣ “ሌላ ልጅ የሌላትና አንድዬ ልጇ የጠፋባት እናት (ልጇን) የምትፈልገውን ያህል›› (ኢማሙ ሻፊዒይ)
‹‹ለስሜት ህዋሶቻችን ብርታት ከምናገኝባቸው እህልና ውሃ ይልቅ፣ የአዕምሮዎቻችን ጤናማነትና መልካምነት ምንጭ የሆነው አደብ የበለጠ ያስፈለገናል፡፡›› (ኢብን አል-ሙቀፈዕ)
‹‹ወገን ለሌለው ሰው፣ አደብ ወገኑ ነው፡፡››
‹‹ልቅና በአዕምሯዊ ልዕልና እና በአደብ እንጂ በደምና በአጥንት አይደለም፡፡ ምክንያቱም አደበ ክፉ የሆነ ሰው ዝምድናውን ያጣል፣ አዕምሯዊ ብቃቱ ያነሰበት ሰው ሥረ-መሰረቱን ይስታል፡፡››
‹‹በሥራ ውስጥ አደብ መኖሩ፣ ሥራው ተቀባይነት ለማግኘቱ ምልክት ነው፡፡›› ያሉም አሉ፡፡
ጥበበኞች እንዲህ ይላሉ፡- ‹‹አደብ አቻ የለሽ ጌጥ ነው፡፡ ጨዋነት የጎደለው ሰው አደብ አይኖረውም፤ አደብ የለሽ ሰው ጨዋነት የለውም፡፡››

ምንጭ - የአደብ አስፈላጊነት መጽሐፍ
ትርጉም ፡ ዐብዱልከሪም ታጁ
ነጃሺ መፃሕፍት መደብር
 
https://t.me/NejashiPP
1.6K views13:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-04 08:56:32 እባክዎ የ ዩ ቲዩብ ቻናሉን ያስተዋዉቁ
ያጋሩ

ከ ዩ ቲዩብ አድራሻውም ገብተው ይመልከቱ ።

http://t.me/MuhammedSeidABX
1.6K views05:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-04 08:54:39

1.5K views05:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-04 07:00:43 “እሺ ካልኩት በኋላ ሸሸ ...


"እሺ ካልኩት በኋላ ሸሸ፤ እኔም ምነው እሽ ባላልኩት ብዬ እፍረት ተሰማኝ፡፡”
ስትላት ሰማሁ በቀደም አንዲት ለጓደኛዋ፡፡ ቸኮልኩ መሠለኝ ... አለቻት ዐይን ዐይኗን እያየች።

እሺ ያለችው ለትዳር ነበር፡፡ ጠየቃት፤ በፊትም ታስበው ነበርና ከትንሽ ማንገራገር እሺ አለችው፡፡

ከዚያ ጠፋ፤ ሸሸ፣ ከዐይኗ ራቀ ። ምን ታድርግ? ደዉላ ምነው ጠፋህ አትለው ነገር፤ ተስማምቻለሁ እኮ ያንን ዕቃ አትወስድም ወይ አትለው ነገር …፡፡
እሱ ሲጠፋ መልሶ አሳፈራት፤ ተሸማቀቀች፤ ደበራት፣ እንደመበሳጨትም አደረጋት፡፡ የምሩን ነው ወይስ ሊፈትነኝ ነው የጠየቀኝ ብላም ራሷኝ ጠየቀች፡፡ የሰው ዉስጡ አይታወቅ ነገር፡፡

ትዳር አንዳንዴ ከንግድ ጋር ይመሳሰላል ። አንዱ ደህና ዋጋ ሰጥቶ ሲጠፋባችሁ ምን ይሰማችኋል ? ይመለስ ይሆን ብሎ በር በሩን እንደማየት። ማሰብ ፣ ተስፋ አለመቁረጥ ...

በርግጥ በወቅቱ ያኔ ትንሽ ላግደርድረው ብላም አስባ ነበር፤ ግና በዚያው ቢቀርስ ብላ ፈራች፤ ይሄ ስትናፍቀው የነበረ መልካም ጥያቄ ላይደገም ይችላል ብላ ሰጋች፡፡ መልካም አክሲዮን አይገፋም። ትዳር ሐላል አክሲዮን ። እስከ አኺራና ጀነት አብሮ የመዝለቅ እሳቤ።

እናም ተስገብግባ እሺ አለችው፡፡
ደግ አደረግሽ።
ቢሆን ባይሆን ፣ ቢመለስ ባይመለስ፣ ቢመጣ ቢቀር ...እሱ የጀሊሉ ዉሳኔ ነው። አንች ግን እንኳን ለሐላል ጓጋሽ።

ለሐላል ነገር መስገብገብ እኮ ጥፋት አይደለም፡፡ እንደዉም የሚበረታታ ነው።

እሺ ስላልሽው ምን አሳፈረሽ! ምንስ ያጠፋሽው ነገር አለ!፡፡ አዎ ምንም የተሳሳትሽው ነገር የለምና አትፈሪ፡፡

እርግጥ ነው በሰው ልብ መጫወት የሚፈልጉ አንዳንድ ሰዎች አሉ። ሰዉን እንደ ገበያ ዕቃ ያያሉ፤
ካስለፈለፉ በኋላ በዉስጣቸው በሰው የሚስቁ፣ እሺ አለችኝ ብሎ ለማስወራት የሚመጡም አሉ።

አንዳንዶች ፈሪ ናቸው። ቶሎ እሺ ስለተባሉ ብቻ ምርጫ ላይ ተሳስቼ ይሆን? ቸኩዬ ይሆን? ብለው የሚደነግጡና አሉ።
አንዳንዶች ደግሞ ለማግባት ወስነው አይመጡም፤ እሺ ከተባሉ በኋላም አጀላቸው የተቃረበ ይመስል የሚርበተበቱም አሉ፤
እሺ አልባልም ብለው አስበው ጠይቀው እሺ ሲባሉ ድራሻቸው የሚጠፋም አሉ፤
ፍላጎት ሳይኖራቸው ከአንገት በላይ ሰዉን የሚያወሩም አሉ፡፡

የሁሉን ልብ የሚያውቀው ጀሊሉ ነው። ፍርዱንም ለሱ መተው ነው ። እሱ ለያንዳንዱ የንያውን ይሠጣል ።
ቁምነገሩ ቁምነገረኛ ነው ብለው ላሰቡት ሰው ልብንና እጅን መሰጠት ነው። ለትክክለኛ ጥያቄ ትክክለኛ ምላሽ መስጠት ጥፋት አይደለም፤
ሐላልን መናፈቅ አያሳፍርም፤
ለምን ታፍሪያለሽ እሱ ከመልካም አክሲዩን የቀረው ይፈር፡፡

ተልቁ ችግራችን በምን ማፈር እንዳለብንና እንደሌለብን አለማወቃችን ነው ።

ሐላል ፍለጋ ላይ ማፈር ብሎ የለም።

http://t.me/MuhammedSeidABX
1.6K views04:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-03 18:06:40 አስፈሪው ነገር አሁንም አዳዲስ አደገኛ ገዳይ ቫይረስ መምጣቱ አይደለም።
አስፈሪው ነገር የተጠቂ እና የሟቾች ቁጥር መብዛቱ አይደለም ።

አስፈሪው ነገር በማስክ ሕይወትን መግፋት አይደለም ።

አስፈሪው ነገር

፨ ኃጢአተኞች ጉዳዮን እንደማንቂያ ደወል አለማየታቸው ነው።

፨ ወንጀለኞች ጥፋታቸውን አምነው ወደ አላህ አልተመለሱም።

፨ ሶላት የተዉት ደንግጠው ወደ መስጊድ አልገቡም።

፨ ቁርአንን የረሱት ከተሰቀለበት አላወረዱም።

፨ ሒጃብ የጣሉት አስተካክለው በሥርዓቱ አልለበሱም።

፨ ሐራም ነጋዴዎች ከሐራም ንግዳቸው አልተነቀሉም።

፨ ቂመኞች ቂማቸዉን ለአላህ ብለው ይቅር አላሉም።

፨ የተጣሉት በኩርፍያቸው ቀጥለዋል ።
፨ መካሪና ተመካሪው በጥፋት እኩል ሆነዋል።
፨ ዓሊሞች በዱንያ ጥቅም ተታለዋል።
፨ እውነተኛ አላህን ፈሪዎች ተመናምንዋል።
፨ ከቁርአን ፊደሉ ብቻ ፈጧል።
፨ እስልምና ስሙ ብቻ ቀርቷል።
፨ ዘካ በኢስላም ዉስጥ ተዘንግቷል።
፨ በረመዷን ወር የማይፆሙ ብዙ አሉ።
፨ ገንዘብ እያላቸው ሐጅ የማይሄዱ በርካቶች ናቸው።
፨ ኸምር በየደጃፉ ፉጠጣል።
፨ ዝሙት በየበረንዳው ይፈፀማል ።
፨ ከቀን ወደቀን ሁኔታዎች ከፍተዋል።
፨ መልካም ሥነምግባራት ከስመዋል።
፨ ኑሮ ተወዷል፣
፨ ሐያእ ጠፍቷል ።

አላህ ሆይ ሰትረን!
አላህ ሆይ ቀልብ ስጠን!


የዚህ ዓይነቱ ትልቅ በላእና መከራ ካላስተማረን መቼ ልንማር ይሆን?

http://t.me/MuhammedSeidABX
9.9K viewsedited  15:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-02 08:23:31
240 views05:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-02 06:00:04 በምድር ላይ ቆይታዬ ከታዘብኳቸው ነገሮች መካከል አንዱ - በአላህ መንገድ ለፀና ሰው ብዙ ሰዎች ትልቅ አክብሮት እንዳላቸው ነው፡፡
በመንገዱ የፀናን ሰው ጀሊሉ ኑርን ያላብሰዋል፤ ሞገስንም ያጎናፅፈዋል፡፡
በዋጂቡም ሆነ በሱናው መጽናት ዉበት አለው፤ ያስቀናል፡፡ ጎበዝ ዲነኛ ሴትንም ሆነ ወንድን አላህ ያፅናት! ያፅናው ብሎ ዱዓ የማያደርግለት ማን አለ!፡፡
ከምወዳቸው የሚንበር ፕሮግራሞች አንዱ ሐዋ ሾው ነው፤ በርቱ፡፡

http://t.me/MuhammedSeidABX
382 views03:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ