Get Mystery Box with random crypto!

ABX

የቴሌግራም ቻናል አርማ muhammedseidabx — ABX A
የቴሌግራም ቻናል አርማ muhammedseidabx — ABX
የሰርጥ አድራሻ: @muhammedseidabx
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 8.70K
የሰርጥ መግለጫ

ወደ ቤታችሁ እንኳን መጣችሁ!!

Ratings & Reviews

2.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 60

2021-03-05 18:23:43 ወዳጆች
ሊንኩን በመንካት ከመጀመሪያው ጀምሮ የነበሩ ፕሮግራሞቻችንን ያገኛሉ ።
"የፍቅር በረከት መጽሐፍን" በትረካ


https://youtube.com/playlist?list=PLBH1axabDryVd-eX5kv5YFJX8vvE9bGTM
1.6K views15:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-03-05 07:13:54  
 አማኞች እገዛን ከአላህ ሱ.ወ እንጅ ከማንም አንፈልግ፡፡ ህይወታችንን ለመምራትም በሱ እንጅ አንረዳ፡፡ ከዚያ በመለስ እራሣችንን ለመምራት ብቃት ይኑረን፡፡ ሾፌር እንደሌለው መኪና አንሁን፡፡ መንገድ እየመረጥን የአላህን ህግ እያከበርን በጥንቃቄ እንጓዝ፡፡ ቁልቁለቱ እንዳያዳልጠን እንጠንቀቅ፡፡ ዳገቱን በፅናትና በድፍረት እንሻገር፡፡ የተደላደሉ ቦታዎችን እንደ ዕድል እንጠቀም፡፡ መሰናክሎችንና ወጣ ገባ  መንገዶችን በጥንቃቄና በስልት እንለፍ፡፡
አንዴ ወደ አላህ መንገድ ከገባን ከመንገዱ እንዳንወጣ፡፡ ከመንገድ ዳርና ዳር ቆመው የሚጣሩትንም እንዳንሠማ፡፡ እንደክም ይሆናል ደክሜያለሁ ብለን ግን  አንቁም፡፡ ነዳጅ ስንጨርስ እንደገና እንሙላ፡፡ ሕይወት እልህ አስጨራሽ ጉዞ ናትና በእልህ  እንጨርሣት፡፡ ቀናት በሠው ልጅ ህይወት ውስጥ አንድ አይደሉም አንዴ ይፈካሉ ሌላ ጊዜ ይፈዛሉና ህይወታችንን እናድስ፡፡   

http://t.me/MuhammedSeidABX
 
  
1.6K views04:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-03-05 07:13:54 ሕይወትህን አድስ
(2)
በሙሐመድ ሰዒድ
ልብ ላላሉ ልቦች መጽሐፍ
**********
የምን መድከም ! የምን ማዘን ! የምን ተስፋ መቁረጥ ! አላህ ሱብሓነሁ ወተዓላ እንዲህ እያለን
وَلَا تَهِنُوا وَلَا تَحْزَنُوا وَأَنتُمُ الْأَعْلَوْنَ إِن كُنتُم مُّؤْمِنِينَ ﴿١٣٩﴾  
 ‹ አትድከሙ አትዘኑ የበላዮች ትሆናላችሁ እውነተኛ አማኝ እንደሆናችሁ ´› (3፡139) ብሎናልና ፡፡
 
አዎን .. ለህይወት ፈተናዎች እጅ መስጠት አያስፈልግም፡፡ ሲያጡ ብዙም አለመከፋት ፤ ሲከስሩ አለመደናገጥና አለመርበትበት ፤ ቢመቱ አለመጉበጥ አለመልፈስፈስ ያስፈልጋል፡፡

ሞተዋል እየተባልን አልሞትንም ከሆነ መልሳችን ፤ ትንሽ ናቸው ስንባል ብዙ እንደሆንን ካሣየን ፤ ስለድክመታችን ሲነገር ጥንካሬያችንን ካስመሰከርን .. ኢንሻአላህ ውጤት አለን፡፡ አዎን ቢኢዝኒላህ ውጤት አለን፡፡
 
ሙእሚን ለስኬት እንጅ ለውድቀት እጅ አይሰጥም፡፡ በኸይር እንጅ በመጥፎ ነገር እራሱን አያበስርም፡፡ በጥንካሬ እንጅ በድክመት ውስጡን አያሳምንም፡፡
 
ወዳጄ ሆይ ! ኢማንህ ሲወድቅ ወድቋል ተስፋ የለውም ብለህ አርቀህ ቆፍረህ አትቅበረው፡፡ ጥረትህ ሲበላሽ ‹ አልቆልኛል ዋጋ የለኝም  ዳግም አላንሰራራም › ብለህ አትዘረር፡፡ ችግር ሲያገኝህ የማገገም እድሌ አክትሟል ብለህ አትሸበር ፡፡ ዱዓእ የማድረግ ስሜትህ ሲጠፋ ከቶ ሊመለስ እንደማይችል ገምተህ እጅህን አጣጥፈህ አትቀመጥ ፡፡
 
 ህይወት አንድ ብቻ አይደለችም ዓይነት አላት፡፡ ዓለም ጎዳና ብቻ አይደለችም ጎዳናዎችም ናት፡፡ ዞር ብለህ ሌላ ስልት ይዘህ ፣ ሌላ ሰው ሆነህ አምርረህ ከተመለስክባት ታሸንፋታለህ፡፡ እሷ ድክመትህን እጅ መስጠትህን  ካወቀች ትገድልሃለች፡፡ እንስም ማንነትህን በጥንካሬህ አሣያት፡፡
 
 
ሕይወት ለውጥን ትፈልጋለች ፣ መታደስንም ትሻለች ፡፡ ሌላው ቀርቶ በድሎትና ሀሴት ውስጥ ብቻ እንኳ በትዕግስት ለረጅም ጊዜ መሰንበቱ ይከብዳታል፡፡ ማር ሲበዛ ይመራታል ቅባትም ከልክ ሲያልፍ ያቅለሸልሻታል፡፡ እናም ነገሮች ሐላልና መልካም እስከሆኑ ድረስ የፍላጎቷን ልንጠብቅላት ይገባል፡፡
 
ኢማን ይጨምራል ይቀንሳል፡፡ ሙድ ይመጣል ይሔዳል፡፡ ሞራል ብቅ ይላል ይጠፋል፡፡ በሁኔታዎች ውስጥ እራሱን ያልቀያየረና በነገሮችም ውስጥ መስመሩን ወስኖ ምርጥ ምርጡን ያልያዘ ሰው የስኬት ጊዜው እሩቅ ነው፡፡ ለአካሔዱና ለጉዞው የተሻለውን መንገድ መጥረግ ትቶ በአንድ ዓለምና ሁኔታ ውስጥ መኖር የመረጠን ሰው ኑሮ ትርጉም አልባ ህይወትም የቁም እስር ዱኒያም የዘላለም ከርቸሌ ትሆንበታለች፡፡
 
 የችግር ዓይነቶች ከወዲህ ወዲያ ቢቀራመቱህ ፤ ፈተናዎች በዚህ በዚያ ቢያዋክቡህ ፤ ችግሮች ከፊት ከኋላ ቢከቡህ ቆም ብለህ ጆሮ የምትሰጥበት ጊዜ እንዳይኖርህ፡፡ ወደፊት እንጅ ወደ ኋላ አትመልከት፡፡ ለመራመድ  አታመንታ፡፡

ሀሳብ ተከታትሎ ቢሰፍርብህ ፤ ጭንቀት አሳድዶ ቢወርርህ ወዲያ በልና አሽቀንጥራቸው፡፡ ማንነቱን አሣልፎ በቀላሉ እጅ የሚሰጥ ሰው አትሁን ፤ የዕድል በሩ እያለለህም ሽንፈትን በፀጋ አትቀበል፡፡
 
 ህይወት እኛ እንዳረግናት ናት ፤ እናስተካክላታለን እናበላሻታለን ፤ እናጣፍጣታለን እናመርራታለን ።

ብልህ ሰው በሞተ ነገር ላይ ነፍስ ይዘራል፡፡ ከምንም ተነስቶም ለቁም ነገር ይበቃል፡፡ ደካማ ግን በእጁ የገባውን አጋጣሚ እንኳ አይጠቀምም፡፡ ዕድልን እንድትፈልገዉ እንጂ ዕድልን ለመፈለግ  ዝግጁ አይደለም፡፡ ስለሆነም በገዛ እጁ ጥፍጥናን ወደ ምሬት ይለውጣል ፤ ደስታን ወደ ሐዘን ይቀይራል ፡፡

ሞቻለሁ አትበል ተስፋ አትቁረጥ ሩሕህን መልስ፡፡ በህይወት አለህ ጠንከር በል አትለሣለስ፡፡ አልደርስም አትበል ትደርሳለህ፡፡ አላልፍም አትበል ታልፋለህ፡፡ አላህ ለምርጫና ለውሣኔ ነፃ አድርጎ ፈጥሮህ ሳለ ለምን ባርነትን ትመርጣለህ ! ፡፡
 
ምድር ሰፊ ናት እይታህን አስፋ አትጨናነቅ፡፡‹ ኢንሻአላህ/ በአላህ ፈቃድ › በል ሁሉንም ነገር በብቃት ትወጣለህ፡፡ መንገድ ቢዘጋ መንገዶች አሉ፡፡ ምርጫ አያልቅም አማራጮች ሞልተዋል፡፡
‹እንችላለን› የሚሉ በአላህ ፍቃድ ይችላሉ፡፡ ‹እናሣካለን› የሚሉ ኢንሻአላህ ያሣካሉ፡፡ በአላህ ላይ እርግጠኛነትህ  (የቂንህ) ይጨምር፡፡ መመካትህም በሱ ይሁን፡፡ በሀሳቦች መሐል አትዋልል፡፡ በሁለት ልብም አትጓዝ ፡፡‹ አገባለሁ › በልና ኳሷን ወደ ጎሉ ምታ ትገባለች፡፡ ‹አሸንፋለሁ› በልና በሙሉ ልብ ወደ ውድድሩ ግባ ታሸንፋለህ፡፡ ‹አልፋለሁ› በሚል ሙሉ ሀሣብ ከፈተናው ክፍል ግባ ታልፋለህ፡፡ ‹እደርሳለሁ› በልና ጉዞህን ጀምር ፡፡ ‹እጨርሳለሁ ውጥንህን ቀጥል፡፡ ሁለት ሃሣብ ካንዱም ያሳጣል ፤ ሁለት አባራሪ አንዱንም ያጣል፡፡
 
 ጭንቀት የሰውን ትኩረትን ይበትናል፡፡ የሀሳብ ክምችት  የሰውን ልጅ አያሠራም፡፡ አለመረጋጋት ለምንም ውጤት አያበቃም፡፡ አጉል ፍራቻና ስጋት ወደፊት አያራምድም፡፡ ከፈራህ ወይንም እርጋታ ካጣህ አትጀምርም አትቀጥልም አታጋምስም አትጨርስም፡፡
 
  በሙእሚን ቤት ለዱኒያ ፈተናዎች መታጠፍ እንጅ መሰበር የለም፡፡ ብሩህ ተስፋና መልካም ጥርጣሬ እንጅ ተስፋ አልባ ጉዞ አይኖርም፡፡ ማንሠራራት እንጅ መሞት አይታሰብም፡፡

በዚህ መልኩ ይህችን ህይወት እንኖራለን፡፡የዱንያ መንገድ አልጋ ባልጋ እንዳልሆነ እናውቃለን፡፡ በድሎትም ይሁን በችግር ውስጥ ፈተና አለ፡፡ እናም እጃችንን ሰብስበን ሱሪያችን ከፍ አርገን እንፋለማለን፡፡ በፊልሚያ ሜዳ የሚገኘው ድል ጣፋጭ ነው፡፡ በድካም የሚጨበጥ ነገር እርካታ ነው፡፡ ለዚሁ ነው አላህ ሱ.ወ. ለሽልማት ያንን ውድ ሀገር ጀነትን ያህል ፀጋ ያዘጋጀው፡፡
 
ሥራ መፍታትና ረጃጅም ክፍቶተች አላስፈላጊ ነገርን ያሳስባሉ፡፡ ነፍስያና ሸይጣንም የሰውን ልጅ ሊያስቱበት ይህንኑ ዕድል ይጠቀማሉ፡፡ ክፍተቶችን በሥራ ማራቅ ያስፈልጋል፡፡ ማንኛውም ሐላል ስራ ጥሩ ኒያ ከታከለበት ኢባዳ ነውና አጅር አለው፡፡ ሥራ መንፈስን ያድሳል ሀሳብንም ይቀንሳል፡፡
 
 
 ለዱኒያና ለአጠቃላይ ተፅዕኖዎቿ አንሸነፍ፡፡ ‹የቀደር ጉዳይ ነው › ብለንም ከእውነተኛው ሞት በፊት ሺህ ጊዜ አንሙት፡፡ ብዙዎች የወረቀት ላይ አንበሳን ይሸሻሉ፡፡ አሻንጉሊትንና አርቲፊሻል ነገሮችን ይፈራሉ፡፡ ለሰባራ ሽጉጥ እጅ ይሰጣሉ፡፡ ሰውነታቸው ስለቀዘቀዘ ብቻ ሞተናል ብለው ከመንቀሣቀስ እጅ እግራቸውን ያሰሩ ፤ ሳይመቱ የሚወድቁ ፤ በማስጠንቀቂያ የሚበረግጉ ፤ ጩሀት  ሁሉ ወደነሱ የሚመስላቸው ብዙ ናቸው፡፡
 
 
አማራጮች እያሉ በአንድ ሁኔታ ውስጥ ብቻ እራስን ማሰር ሞኝነት ነው፡፡ ምድር ሰፊ ናትና ተነስ ተንቀሳቀስ ፣ ሒድ ተመለስ ፤ ሙድህን ፈልግ ህይወትህን አድስ፡፡
‹ደብሮኛል› ብሎ ለረጅም ሰዓት ተጠቅልሎ የሚተኛን ሰው አንደኛ ነገር ድብርቱ አይለቀውም ሁለት - ጊዜ ቆሞ አይጠብቀውም  ሶስት - በድርጊቱ ኪሳራ እንጅ ትርፍ የለውም፡፡ አንዴ ወንጀል ውስጥ ወድቄያለሁና ተስፋ የለኝም ብሎ እዚያው የሚንቦጫረቅ ሰው አንደኛ- ለውስጡ ሰላምን አያገኝም ሁለት - ሀጢዓቱ አይቀንስለትም ሶሰተኛ - አላህም አይታረቀውም ፡፡

http://t.me/MuhammedSeidABX
1.4K viewsedited  04:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-03-04 20:59:11
1.2K views17:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-03-04 20:57:53 ህይወታችንን እናድስ
*************
 ምንጭ ፦ ልብ ላላሉ ልቦች መጽሐፍ
ሙሐመድ ሰዒድ

አላህ ሱብሓነሁ ወተዓላ እንዲህ ይላል -
وَقَالُوا الْحَمْدُ لِلَّهِ الَّذِي أَذْهَبَ عَنَّا الْحَزَنَ ۖ إِنَّ رَبَّنَا لَغَفُورٌ شَكُورٌ ﴿٣٤﴾ الَّذِي أَحَلَّنَا دَارَ الْمُقَامَةِ مِن فَضْلِهِ لَا يَمَسُّنَا فِيهَا نَصَبٌ وَلَا يَمَسُّنَا فِيهَا لُغُوبٌ
‹ ምስጋና ለአላህ ይሁን ለዚያ ሐዘንን ላስወገደልን (አምላክ)፡፡ ጌታችን በርግጥ መሐሪ አዛኝም ነው፡፡ እርሱ በችሮታው ዘላለማዊ ከሆነችው አገር ያሠፈረን (አምላክ) ነው፡፡ ከውስጧ ችግርም ሆነ ድካም ፈፅሞ አያገኘንም - ይላሉ› (35፡34-35)
خَالِدِينَ فِيهَا لَا يَبْغُونَ عَنْهَا حِوَلًا ﴿١٠٨﴾
‹ በውስጧ ዝንተዓለም ይኖራሉ ለውጥን (ዝውውርን) ፈፅሞ አይሹም ፡፡› (18፡108)
 
ይህ አምላካችን አላህ ሰብሓነሁ ወተዓላ ጀነትንና  የጀነት ሰዎችን ሁኔታ የገለፀበት የቁርኣን አንቀፅ ነው፡፡ በርግጥም ያ አገር ሁሉ ነገሩ የተሟላ ነው፡፡ ፀጋው ፈፅሞ አይሰለችም፡፡ ድሎቱ መቼም ቢሆን አያረጅም፡፡ ጣዕሙ ሁሌም አያልፍበትም፡፡ ድካም የለ ፤ ሐዘን የለ ፤ ድብርት የለ ፤ ሀሣብ ጭንቀት የለ፡፡ ደስታ ፣ እርካታ፣  ፍፁም የሆነ ለመግለፅ የከበደ ድሎትና ራሃ ብቻ፡፡
 ያለንባት ሀገር ዱኒያ ግን በተቃራኒው ናት፡፡ ሙሉ አይደለችም ጎዶሎ ናት ፤ ዕድሜዋ ወሠን አለው ፤ ደስታዋ የተገደበ ነው ፤ እርካታዋ ያልቃል ፤ ቀለሟ ይፈዛል ፤ መልኳ ይደበዝዛል ፤ ጣዕሟ ይሠለቻል ፤ ድሎቷ ያበቃል ፤ ውበቷ ይረግፋል ፤  ጥፍጥናዋ እጅ እጅ ይላል፡፡
 
በዚህች ዓለም ውስጥ ፍፁም የሆነ ደስታና እርካታ አይታሰብም፡፡ ለረጅምና ተከታታይ ለሆኑ ቀናት ያለ ትልቅም ሆነ ትንሽ ችግር አይዘለቅባትም፡፡ በሽታ ፣ ሐዘን፣ መከራ .. እንዲሁም ሌሎች ትላልቅ ሙሲባዎች እንዳሉ ሆነው ስንፍና ፣ ድብርት ፣ መዘናጋት ፣ ሀሳብ ፣ ጭንቀት ፣ ሙድ/ጥሩ ስሜት ማጣት/ና የመሣሰሉት ደግሞ የሰው ልጅ በዚህች ምድር ሣለ ሙሉ ደስታና ጤናማ ኑሮን እንዳይመራ ዕለት ተዕለት የሚፈታተኑት ጊዜውንና ዕድሜውን በአግባቡ እንዳይጠቀም የሚሻሙት ነገሮች ናቸው፡፡
 
ያወቀበትና ብልህ የሆነ ሰው በአላህ ታግዞ በጥረቱና በብልጠቱ እነኚህን አስቸጋሪ መሠናክሎች ገፍትሮ በማባረር አሉታዊ ውጤታቸውን መቀነስም ሆነ በማስቀረት ቀላል የማይባሉ ተጨማሪ ደስታዎችን ሊያገኝ ይችላል፡፡
 
ይህች ዓለም እስካለች ድረስ ሙሲባዎች ሁሌም እንዳሉ ናቸው፡፡ ይህች ዓለም ሠርተን ጥረን ግረን የምናልፍባትና ለውጤት የምንበቃባት እንጅ እጃችንን አጣጥፈን ተዓምር የምንጠብቅባት አይደለችም፡፡  አላህ ሱብሓነሁ ወተዓላ
يَا أَيُّهَا الْإِنسَانُ إِنَّكَ كَادِحٌ إِلَىٰ رَبِّكَ كَدْحًا فَمُلَاقِيهِ ﴿٦﴾
‹የሠው ልጅ ሆይ ! ወደ ጌታህ ትለፋለህ ትደክማለህ (በመጨረሻም) ትገናኘዋለህ › (84፡6) ይለናል ፡፡
 
የሰው ልጅ የዱኒያ ላይ መሠናክሎችን በቀናት ማለፍና በዕድሜ መግፋት የተወሠኑትን ወደ ኋላ ጥሎአቻው ይሔድ ይሆናል፡፡ ሆኖም ግን እስከለተ ሞታችን አብረው የሚዘልቁ አሉ፡፡ እልህ አጋብተውን መጨረሻችን ‹ ሽንፈት ወይንስ ድል ውድቀት ወይንስ ስኬት › የሚለውን ለማየት የተፈጠሩም ይመስላሉ፡፡
تَبَارَكَ الَّذِي بِيَدِهِ الْمُلْكُ وَهُوَ عَلَىٰ كُلِّ شَيْءٍ قَدِيرٌ ﴿١﴾ الَّذِي خَلَقَ الْمَوْتَ وَالْحَيَاةَ لِيَبْلُوَكُمْ أَيُّكُمْ أَحْسَنُ عَمَلًا ۚ وَهُوَ الْعَزِيزُ الْغَفُورُ
‹ ያ ንግስና በእጁ የሆነው (ጌታ) ችሮታው በዛ እሱ በሁሉ ነገር ላይ ቻይ ነው፡፡ እሱ ያ ማንኛችሁ ይበልጥ መልካም እንደሚሠራ ሊፈትናችሁ ሞትንና ህይወትን የፈጠረ ነው ፡፡ › (67፡1-2)
 
 የጀመሩትን ለመጨረስ ፤ በያዙት ፀንተው ለመዝለቅና ከዓላማ ለመድረስ ሁሌም በጎ ለመሥራት ወጥ የሆነ ስሜት ላይ ብንኖር ነገሮች እንዴት ባማሩ ነበር፡፡ አንብቦ ለመረዳት ፣ በተቅዋ ለመሞላት ፣ በኢማን  ለመፋፋት ፣ ለጥሩ ሰላት ፣ ለሰደቃና ለጾም… ሁሌም ወጥ የሆነ ነሻጣ በኖረን እንዴት ደስ ባለን ! ዋ እንዴታ ! ፡፡ነገር ግን የመድከም ፣ የመደበት ፣ የመዘናጋትና የነገርን ዋጋ ያለማወቅ የመሰላቸት ችግር አለብን፡፡ ወር ብንሰራ   ወር እናርፋለን፡፡ ሳምንት ብናጠና ሳምንት ይደክመናል፡፡ አንድ ቀን ብንገነባ በሌላኛው ቀን  እናፈርሣለን፡፡ በድክመታችንና ግልጽ ባልሆኑ ምክኒያቶች ጭምር የጣድነዉን ስናወርድ ፤ አጥብቀን የያዝነውን ስንለቅ ፤ የሞላነውን ስናጎድል እንታያለን ፡፡ ነሻጣ ድብርት ፣ መጨመር መቀነስ ፣ መዘናጋት መንቃት ፣ ከፍ ዝቅ ፣ ኢማን ኒፋቅ ፣ ፅድቅ ሀጢዓት … እንዲህ ነው ህይወታችን ኑሮአችንና ባህሪያችን፡፡
 
የሰው ልጅ በጎ ነው ያለውንና አጥብቆ የተመኘውን ነገር ይዞ የፍላጎቱንና የሀሳቡን ሞልቶ እስከዘላለሙ መጓዝ ይቸግረዋል ይከብደዋልም፡፡ " ቀልብን ገለባባጭ የሆንክ ጌታ ሆይ! ቀልቤን በዲንህ ላይ አፅናልኝ " ይላሉ ታላቁ ነቢይ ሰለላሁ ዐለይህ ወሰለም፡፡ ይህ የታላቁ ነቢይ ሰለላሁ ዐለይህ ወሰለም የዘወትር ዱዓዕ ለኛ ሁሌም ዘወትርም በእስትንፋሣችን ልክ ያስፈልገናል፡፡
 
 ፈተናዋ የቱን ያህል ቢበዛም ይህች የቅርቢቱ ዓለም ከብዶኛል አልቻልኩም ተብሎ እጅ ሊሰጡላትና ሊንበረከኩላት የምትገባ አገር አይደለችም፡፡ ከደጋግ ትጉሃን የአላህ ባሮች ጋር አብሮ ለመራመድ ፣ በመልካም ሥራ ከቀደሙት ላለመራቅ ፣ ከወራጅ ቀጠና ላለመገኘት ብሎም ወድቆ ላለመቅረት ለኛ መጨረሻችንን  ላላወቅንና የመሞቻ ቀናችን ላልተነገረን ሰዎች ኮስተር ቆፍጠን በማለት ልብ ምቷን እስካላቆመችና ነፍስም አለሁኝ እስካለች ድረስ ሳይታክቱ ሳይደክሙ አንድ እራስን ለማስተካከል ያሰቡትን አይነት ሰው ሆኖ ለመገኘት ሁሌም ትግል ጥረት ልፋት ግድ ይላል ፡፡

http://t.me/MuhammedSeidABX
1.3K views17:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-03-03 21:52:28 አዳምጡት

http://t.me/MuhammedSeidABX
1.3K views18:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-03-03 21:51:52

1.3K views18:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-03-02 18:32:32
1.5K views15:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-03-02 18:31:37  ሐያእ
**
ከእስልምና አስተምህሮ ዉስጥ እጅግ ተፈላጊ ነገር ነው፡፡ ነቢያችንም (ሰ.ዐ.ወ.) በዚሁ መልካም ባህሪ ላይ አበረታተዋል፡፡ ምክንያቱም ሐያእ ወደ መልካም ነገር ስለሚገፋፋና ሰዎችንም መጥፎ ነገር ከመሥራት የሚከለክል በመሆኑ ነው፡፡ ሐያእ አንድ ሰው አስቀያሚ ነገር እንዳይሰራ ያግደዋል፡፡ ከሚያስነውረውና በአላህ (ሱ.ወ.) ሆነ በሰዎች ዘንድ ከሚያስወቅሰው ነገርም ይጠብቀዋል፡፡

ሐያእ በርግጥም ውጤቱ መልካም የሆነ ምርጥ ሥነ-ምግባር ስለመሆኑ አያጠራጥርም፡፡ ሐያእ የአላህ (ሱ.ወ.) ፍራቻ መገለጫ ነውና አንድ ሰው መጥፎ ነገር ለመስራት አስቦ የተነሳ እንደሆነ ከድርጊቱ ሊያቆመው የሚችለው ሐያእ ብቻ ነው፡፡ ለምሳሌ፡- አንድ ሰው ለበደለው ሰው ወዲያውኑ በተመሳሳዩ አሊያም በባሰ መልኩ ምላሽ እንዳይሰጥ የሚከለክለው ሐያእ ነው፡፡ አንድ ሰው በለመነው ጊዜም ለመርዳት ወደኋላ እንዳይልና እንዳያመነታ የሚከለክለው ሐያእ ነው፡፡ አንድ ሰው በአንድ ስብስብ ዉስጥ ተቀምጦ እያለ በማይመለከተው ነገር ገብቶ እንዳያወራ የሚገድበውም ሐያእ ነው፡፡ ምላስንም በዘፈቀደ ከመልቀቅ የሚከለክልና ጥንቃቄን ወደመምረጥ የሚያነሳሳ ሐያእ ነው፡፡

ዑለማዎች እንዲህ ብለዋል፡-
“ሐያእ ማለት ሐያት (ሕይወት) ከሚለው ቃል የተወሰደ ነው፡፡ የልብ ሕያውነት ከፍ ባለ ቁጥር የሐያእ ባህሪም ከፍ ይላል፡፡ የሐያእ ማነስ ወይም ሙሉ በሙሉ መጥፋት የልብ አሊያም የመንፈስ መሞት ምልክት ነው፡፡”
ራሳችንን እንገምግም። እኛስ በርግጥ ሐያእ አለን?
ሐያእ ማድረግ ካለብን ነገሮች ሁሉ ሐያእ እናደርጋለን ? ሐያእ አለን ካልን መጠኑ ምን ያህል ነው? ከሌለንስ ሐያእ ያስፈልገናል ወይስ ቢቀርም ምንም የማይጎዳ ባህሪ ነው??


ምንጭ - ሐያእ መጽሐፍ
ትርጉምና ቅንብር - ሙሐመድ ሰዒድ

ነጃሺ ማተሚያ ቤት
ነጃሺ መፃሕፍት መደብር ያግኙታል።

https://t.me/NejashiPP
1.5K views15:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-03-02 18:06:54 ባህር ዳርቻ ላይ ማዕበልንና መስጠምን ፈርቶ ቆሞ ልግባ አልግባ፣ ልሞክር አልሞክር የሚል ሰው ዱንያን ኖሯታል ሊባል አይችልም ።

ዱንያን ኖሯታል የሚባለው ሰው ሕይወትን ከነምናምኗ የተጋፈጣት፣ ፊት ለፊት የሄደባት፣ የሞከራት፣ የደፈራት፣ የዋኛት፣ የተፋለማት ነው።
አትቀመጥ ተነስ፣
አትፍራ ድፈር፣

http://t.me/MuhammedSeidABX
1.4K views15:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ