Get Mystery Box with random crypto!

ABX

የቴሌግራም ቻናል አርማ muhammedseidabx — ABX A
የቴሌግራም ቻናል አርማ muhammedseidabx — ABX
የሰርጥ አድራሻ: @muhammedseidabx
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 8.70K
የሰርጥ መግለጫ

ወደ ቤታችሁ እንኳን መጣችሁ!!

Ratings & Reviews

2.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 59

2021-03-14 18:03:26 አያልፉም ያልናቸው ቀናት ያልፋሉ ። ደስም ይለናል ኢንሻአላህ

http://t.me/MuhammedSeidABX
1.2K viewsedited  15:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-03-13 16:01:20 ኢስቲቃማ  (በዲን ላይ መፅናት)

(4)
ከ”ህልም አለኝ” መጽሐፍ
በሙሐመድ ሰዒድ (ABX)
 ........ * ......
ለምንም ይሁን ለምን ለዓላማ የሚኖርን ሰው ‹ፅናት›አለው ይሉታል ሰዎች፡፡ ከጀነት በላይ ደግሞ ትልቅ ዓላማ የለም፡፡ ጀነት ዓላማው የሆነ ሰው ታላቅ ዓላማ ይዟልና በየትኛዉም ፈተና አይበለጥም፤ ፈፅሞ በሸይጧን አይበለጥም፤ በነፍስያ አይሸነፍም፤ ለእኩይ ስሜት እጅ አይሰጥም፤ በዱኒያና በጥቅሞቿ አይታለልም አይደለልም፡፡

 በአላህ ዲን ላይ የፀናን ሰው ድሎት ይሁን ችግር፤ ረሃብ አሊያም ቸነፈር ከጌታው አያርቁትም፡፡  በዱኒያ ላይ የሕይወት ቆይታ ውስጥ ለውጥ ቢያገኝ ኑሮው ይለወጥ ይሆናል እንጅ በአላህ ላይ አይለወጥም፡፡ በጌታው ይፀናል፡፡ ለቃል ኪዳኑ ይታመናል፡፡ በቃልኪዳንና ቀጠሮው ያምናል፡፡ ፅኑ ነውና ከአላህ (ሱ.ወ) ነጥቆና ነጥሎ የሚወስደው ማንም ምንም ሀይል የለም። ባርነቱ ለጌታው ብቻ ነው፡፡ በዚህ አቋሙም እንደፀና ይኖራል፤ በአመላከከቱም መሬት ይይዛል፤ እውነተኛ መርጋትንም ይረጋል።
እውነተኛ ፅናት ያለው ሰው በየትኛውም ሁኔታና ቦታ አላህ (ሱ.ወ) እንደሚያየው ያውቃል፡፡ እንደሚከታተለውም ይገነዘባል፡፡ ስለሆነም ጌታውን አጥብቆ ይፈራል፡፡ ሰዎች አጠፉ ብሎ አያጠፋም፡፡ ሰዎች ስለጠመሙም አይጠምም፡፡ ከቀናት መለወጥ ጋር አይለወጥም፡፡ ዘመኑ ነዉና ሰው እንደሆነው ልሁን አይልም፡፡ በስኬትና በዕድገትም አይቀየርም። ከአፍሪካ ወደ አሜሪካ ቢሔድ፤ ከድህነት ወደ ባለፀጋነት ቢሸጋገር፤ ከተራነት ወደ ትልቅ ስልጣን ቢንደረደር፤ ከታዋቂና ታላላቅ ሰዎች ጎራ ቢሠለፍ፤ ለሱ ምንጊዜም ቢሆን አላህ (ሱ.ወ) ነው ጌታው፡፡ አሁንም በጌታው ይፀናል፡፡ ወደዚህች ዓለም ለምን እንደመጣ ጠንቅቆ ያውቃል፡፡ በመሆኑም ዲኑን አጥብቆ ይይዛል-- በክራንቻው ነክሦ፤ ከደሙ ጋር አዋህዶ፤ ከነፍስ ከሥጋው ቀላቅሎ… ከነፍሱ ጋር ካልሆነ በቀር ማንም ምንም ከአላህ (ሱ.ወ) አይነጥለውም፡፡ ለሱ አላህ ነው ጌታው፤ ኢስላም ነው መንገዱ፤ ቁርኣን ነው መመሪያው፤ሙሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) የአላህ መልዕክተኛ የርሱ ነቢዩ ናቸው።

ዛሬ በዱኒያም ሆነ ነገ በአኺራ አጠቃላይ የሁለቱን ዓለም ስኬት የምንፈልግ ከሆነ እኔም ሆንኩ አንተ አንቺ የእስልምናን ጉዳይ ቀለል አድርገን እንዳንመለከት እመክራለሁ፡፡ በዲን ላይም ፅናት ይኖረን ዘንድ እማፀናለሁ፡፡ ብንፀና የምንጠቀመው እኛው ነን፡፡ ብንንሸራተትም ተጎጂዎቹ ራሣችን ነን። ደግሞም ልብ እንበል …
ትራስ ተንተርሦ ጀነት አይታሠብም፡፡ ከውድ ነገርም በቀላሉ አይደረስም፡፡ ዓለማችን መንፈሳዊነትን በሚያስቱ ከኢማንም በሚያዘናጉ በርካታ ነገሮች ተሞልታለች፡፡ ጀነት ዙሪያዋ አስደሣች ባልሆኑ ነገሮች ታጥራለች፡፡መንገዷ  ልፋትን ይጠይቃል፡፡ ውጣ ውረዱ ብዙ ፈተናና መሰናክሉም ከባድ ነው፡፡ ዛሬን ካላለቀሱ የነገ ሣቅ አይታሰብም። መከራ ችግሮችን የመቋቋም፤ ፈተና መሰናክሎችን የማለፍ እጅግ የበረታና የፀና አቋም ካለን ግን በመጨረሻም ከሲራጥ ማዶ የምናገኘው ነገር ቢኖር ጀነት ነው። አዎን ኢንሻአላህ ጀነት... ጀነት ደግሞ እንደ ዱኒያ ጠፊ ሣትሆን ቋሚ አገር ነች፡፡ ስኬቱም ዘላለማዊ።

“እነዚያ «ጌታችን አላህ ነው» ያሉ. ከዚያም ቀጥ ያሉ፡- «አትፍሩ፤ አትዘኑም፤ በዚያችም ተስፋ ቃል ትደረግላችሁ በነበራችሁት ገነት ተበሰሩ፤» በማለት በነሱ ላይ መላእክት ይወርዳሉ፡፡ «እኛ በቅርቢቱም ሕይወት. በመጨረሻይቱም ረዳቶቻችሁ ነን! ለናንተም በርሷ ውስጥ ነፍሶቻችሁ የሚሹት ሁሉ አልላችሁ፤ ለናንተም በርሷ ውስጥ የምትፈልጉት ሁሉ አልላችሁ፤ «መሓሪ አዛኝ ከኾነው አላህ መስተንግዶ ሲኾን፤» (ይባላሉ)፡፡”  (ፋሲለት፡ 30-32)

ወረት አስቀያሚ ፀባይ ነው። በዲን ላይ መፅናትን (ኢስቲቃማን) የመሰለ ትልቅ አቋምና ዕድል የለም፡፡ አደራችንን- ለአምላካችን ተለዋዋጭ ፊትና ባህሪ አናሳይ፡፡ በረመዳን ስንሰግድ ከርመን ከረመዳን ውጭ አናቋርጥ፡፡ዛሬ ጀምረን ነገ አንሠላች፡፡ ሰዎች በብርታትና ፅናታችን እስኪያውቁን ድረስም ለአኺራችን እንልፋ። መልካም ነገር ብናቋርጥ እንኳን አስታውሰን ተመልሰን ወደ መስመሩ እንምጣ፡፡

የሰው ልጅ ወጥ በሆነ ባህሪ የማይረጋ ቅጠ-ቢስ መሆኑን ያወቁት ታላቁ ነቢዩ በርካታ ዱዓዎችን አስተምረውናል። ከነዚህም ‘ያሙቀሊበ-ል-ቁሉቢ ሰቢት ቀልቢ አላ ዲኒክ’ የሚለው ዋንኛው ነው፡፡ ትርጉሙም  ‘ቀልብን የምትገለባብጥ የሆንክ ጌታ ሆይ! ቀልቤን በዲንህ ላይ አፅናልኝ’ ማለት ነው።
በፅናት አቻ የማይገኝላቸው ታላቁ ነቢይ ሙሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) ይህንን ዱዓዕ  በተደጋጋሚ ያደርጉ ነበር። የኢስቲቃማ ችግር ያለብን እኛ ግን እጅጉን ተዘናግተናል። ይህን ዱዓዕ ዘወትር ማድረግ ለተቁነጥናጭ ልብ ሁሉ መድሀኒት ነው፡፡ ላልሰከነች ነፍስም እርጋታ።

በርግጥ መንገዶች ብዙ ናቸው፡፡ ትክክለኛውና ብቸኛው ግን አንድ ሲሆን እሱም- የአላህ (ሱ.ወ) እና የረሱል (ሰ.ዐ.ወ) መንገድ ነው። የአላህ (ሱ.ወ)ና የረሱሉ (ሰ.ዐ.ወ) ያልሆነ መንገድ ሁሉ ቀና ቢመስልም ጠማማ ነው፡፡ ብርሃን አይምሰለን ጨለማ ነው። መሪዎቹና አጃቢዎቹም ሸይጧን፣ እኩይ ስሜት፣ ደመነፍስና ክፉ ሰዎች ናቸው፡፡ ተከታዮቹም ጃሒሎች። እናም ዋስትና በሌለውና ማስረጃውም ሀሠት በሆነ መንገድ እንራመድ፡፡ መጨረሻው ገደል ነውና። በየዕለቱ ውሏችንን እንገምግም፡፡ ለአላህ (ሱ.ወ) ብቻ እንጂ ይህ ለስሜታችን ይህ ለሸይጣን ብለን የምንከፋፍለው ቀን አይኑረን፡፡ እግራችን ከአላህና ከረሰሉ መንገድ እንዳይንሸራተት ነቃ እንበል፡፡ የራቅን እንደሆነ እንመለስ፡፡ የተጠጋን ከሆነ ደግሞ ይበልጥ እንቅረብ።

ትንሽ ትልቁን፤ ብዙ ጥቂቱን፤ ቀልድ ቁምነገሩን የሚፅፉ ከመፃፍም የማይደክሙና የማይሠለቹ ፀሀፊ መላኢካዎች አሉብን። ካጠፋን ቶሎ እንቶብት፡፡ ክፋትን በመልካምነት እናስከትል፡፡ ትክክለኛ ኢስቲቃማ ይኑረን፡፡ ‹ወረት› የሚባለውን ባህሪ እናስወግድ፡፡ ዒባዳችን የመጣል የማንሳት የፋሽን ዓይነት እንዳይሆን።
ደግሞም ወንድሜ አደራህን፡፡ እህቴ አደራሽን... “እንደ እገሌ እንዳትሆኑ፡፡ የሌይል (የለሊት) ሶላት ይሰግድ ነበር ተወ፡፡” ሰኞ እና ሀሙስን ይፆም ነበር አቋረጠ።’ ይህ ነቢያችን (ሰ.ዐ.ወ) ለአንድ ሰሐባቸው የመከሩት ነው።

ወዳጄ ሆይ! ኢስቲቃማ ይኑርህ- ዕድልህ አልለየምና፡፡ እጣ ፈንታህን አላወቅክምና። መቸም ቢሆን አትድከም፡፡ አልቻልኩም አልሆነልኝም አትበል፡፡ አትዘናጋ አትስነፍ፡፡ ለአላህ (ሱ.ወ) ያለህ ፍራቻም ተከታታይነት ይኑረው።
ጌታህን በማምለክና በመታዘዙ በርታ፡፡
‹እስከመቼ› ብሎ ለጠየቀ ደግሞ አላህ (ሱ.ወ) በቅዱስ ቃሉ እንዲህ ይላል።
 
“ሞትህ እስኪመጣ ድረስ ጌታህን አምልከው፡፡” (አል-ሒጅር፡ 99)

‹ጌታዬ ሆይ! አንተን በማውሣት፣ በማመስገንና አምልኮህን በማሣመሩ እርዳኝ፡፡› ከአላህ መልእክተኛ (ሰ.ዐ.ወ) ዱዓዖች መካከል፡፡
 
 
http://t.me/MuhammedSeidABX
538 viewsedited  13:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-03-11 19:59:37 ኢስቲቃማ  (በዲን ላይ መፅናት)

(3)
ከ”ህልም አለኝ” መጽሐፍ
በሙሐመድ ሰዒድ (ABX)
 
ወንድሞቼና እህቶቼ! ኢስቲቃማ ለማጣታችን ምክኒያቱ ይህ መሰለኝ...
በዲኑ በር ላይ ቆምን እንጂ ወደ ውስጡ አልገባንም፤
ኢማንን አሸተትነው እንጂ ከውስጣችን ገብቶ አላጣጣምንም፤
ቁርኣንን  አነበነብነው እንጂ ትርጉሙን አላወቅንም፤
ብናውቅም በጥልቀት አላስተነተንንም፥
ለሃይማኖቱ አስተማሪና መካሪ ጆሯችንን አስመታን እንጅ ልብ አልሰጠንም፤
የእስልምናን ውበት አደነቅን እንጅ አልተገበርንም።

ለዚህም ነው ደህና ተጉዘን የሆነ ቦታ ላይ ስንደርስ የምንደክመውና ነገሮች የሚበላሹብን፡፡

ሥራዎች የሚለኩት በአጨራረስ ብቃት መሆኑን መዘንጋታችን ሌላው ችግራችን ነው።
ነገሮችን ለከርሞ ብሎ ማዘግየት ተጨማሪ ክፍተታችን ነው፡፡

በእድሜ ገፍተን ሣለ ሁሌም ገና ወጣት እንደሆንንና ወደ ፊትም ሰፊ ጊዜ እንዳለን እናስባለን፡፡
ወጣቱ  ከጋብቻ  በኋላ፤ 
ኮረዳዋ ቤት ከያዘች፤
ነጋዴው ሀብታም  ከሆነ፤
ተማሪው ትምህርቱን ከጨረሰ፤
ተመራቂው ሥራ ከያዘ፤
ሥራ የያዘው ቤት ከሠራ፤
ስደተኛው አገር ከገባ ...በኋላ
በሙሉ ልቡ ወደ ዲኑ እንደሚዞርና እንደሚፀና ለሙስሊሙና ለኢስላም እንደሚተጋ፤ ለመንፈሳዊ ህይወቱም እንደሚሠራ ቃል ይገባል፡፡ ለዚህም ይቀጥራል ይምላል፡፡

አያልቅበቱና አይቻለው የለ አምላክ አላህ (ሱ.ወ) ግን የባሮቹን ሀሣብና ፍላጎት ይሞላል፡፡
ለሁሉም እንደየሀሣቡና ምኞቱ በሰጠ ጊዜ ሰው ምንጊዜም ሰው ነውና ቃሉን ያጥፋል፤ የተናገረውንም ይረሣል፡፡
በዚህም አጀንዳውና ሀሣቡ ሌላ ይሆናል፡፡ ወጣቱና ኮረዳዋ ስለ ትዳር፤ ያገቡት የቤትና የልጅ ጉዳይ፤ ትምህርት የጨረሰው የሥራ ጉዳይ፣ ሥራ የያዘው የዕድገት ጉዳይ፣ አገር የገባው የማረፊያ ነገር ሀሳቡ ይሆናል፡፡
አላህ (ሱ.ወ) እንዲህ አለ፡-
الإسراء: ٣٤
“በኪዳናችሁም ሙሉ፡፡ ኪዳን የሚጠየቁበት ነውና፡፡” (አል-ኢስራእ፡ 34)
 
ወዳጆቼ!
ሕይወት ውሳኔ ናትና የሰው ልጅ መወሠን ካልቻለ መቸም ቢሆን ሰው አይሆንም፡፡
ውሣኔውም ዛሬ እንጅ ነገ መሆን የለበትም፡፡

የሰው ልጅ ምክንያት መደርደር ልማድና ባህሪው ነው፡፡ እንዲህ እንዲያ እያለም አንድም ቀን በሁለት እግሩ ሳይቆም፤
በሸሪዓው ሣያድር፤
በዲኑ ሣይረጋ … አጅሬው ሞት ከተፍ ይልና የዱኒያ ላይ ቆይታው ያበቃል፡፡
ያኔ ታዲያ ረጅም ቁጭት አይፈይድም፡፡
መፀፀቱም ዋጋ የለውም፡፡
በመሆኑም አሁን መሥራት ነው መላው።

የሰውን ልጅ ፈጥኖ ቃል በመግባቱ ማንም የሚስተካከለው የለም፡፡ በመሙላቱ ላይ ግን ሲበዛ ስስታም ነው። (ይሰመርበት)***

ኢስቲቃማ /በዲንመፅናት/ ማለት…
ካመኑ በኋላ አለመጠራጠር፤
ከያዙ በኋላ አለመልቀቅ፤
ሣይዘናጉ መበርታት፤
ሣይንሸራተቱ መርጋት፤
ወደ ኋላ ሣይመለከቱ መጓዝ .....
አላህን (ሱ.ወ) እስከሚገናኙበት ቀን ድረስም ከአምልኮው አለመታከትና አለመስነፍ ነው፡፡

ኢስቲቃማ ያለው ሰው ሁሌም በጌታው ፍላጎትና ፈቃድ ይፀናል፡፡
ችግር አይፈታውም፤
መከራ አይረታውም፤
ሀሴት አያሸንፈውም።

የኢስቲቃማ ባለቤት በሐዘን ወቅት ፅኑ ነው፡፡
በደስታ ዘመንም ፅኑ ነው፡፡
በእምነት በአመላከከቱ ይፀናል፤
በፆም በሰላት ይፀናል፤
መቸም ቢሆን ዓላማውን አይስትም፤
ከግቡ አይንሸራተትም።


ክፍል 4 ይቀጥላል

ባረከላሁ ፊኩም


 http://t.me/MuhammedSeidABX
986 views16:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-03-10 21:09:56 ኢስቲቃማ  (በዲን ላይ መፅናት)

(2)
ከ”ህልም አለኝ” መጽሐፍ
በሙሐመድ ሰዒድ (ABX)
 
ከሰው ሁሉ በተለይ በዚህ ዘመን እጅግ ምርጥና የተሻለው - በእጁ የገባውን ውድ ነገር በተለይም ኢማንና የአላህን ፍራቻ የመሳሰሉትን ድንቅ ሀብቶች ከእጁ እንዳይወጡ የሚታገለውና የሚፍጨረጨረው ነው። ያለንበት ጊዜ ባለን ኢማን ላይ ለመጨመር ቀርቶ በእጅ ያለን ይዞ መቀጠሉ ከብዷል፡፡ ብዙ አግበስብሶ አንዱን እንኳን ለመያዝ ከመቸገር በጥቂቷ በርትቶና ረግቶ በትንሿ ሥራ ላይም አላህ (ሱ.ወ) እንዲባርክልን ለምኖ እስከ ህልፈተ ሕይወት ድረስ ሳይሰለቹ መፅናቱ አዋጭ መንገድ ሣይሆን አይቀርም፡፡ እጅግ ተመራጩ ኢባዳም /አምልኮ/ ቢያንስ እንኳ የዘወተሩበት ነውና። አላህ (ሱ.ወ) እንዲህ አለ፡-

    الأحقاف: ١٣
“እነዚያ፡- «ጌታችን አላህ ነው» ያሉ፥ ከዚያም ቀጥ ያሉ. በነርሱ ላይ ፍርሃት የለባቸውም፡፡ እነርሱም አያዝኑም፡፡”  (አል-አሕቃፍ፡ 13)
 
አልሐምዱሊላህ …… ዲናችን ገር ነው፡፡ በሸሪዓ መንገድ ሲኖሩ መካከለኛነትን የመረጡትም የስኬት ባለቤቶች እነርሱ ናቸው፡፡፡ በራሳቸው ላይ የሚያካብዱትም ሆኑ ሌሎችንም የሚያጨናንቁት ግን የመሸነፊያ ጊዜያቸው እሩቅ አይሆንም።
አዎን ዲናችን ገር ነው፡፡ ዲን ከያዙት መርጣችሁ ሣይሆን ሁለመናዬን ያዙኝ ይላል፡፡ በከፊል ሣይሆን ጠቅልላችሁ ውስጤ ግቡ ሲል ይጠይቃል። የዲን ሥራም የትርፍ ጊዜ ሥራ አይደለም፡፡ ባይሆን ወደዚህች ዓለም ብቅ ካሉበት ጊዜ ጀምሮ እስከ እስትንፋስ ማብቂያ ድረስ የሚሠሩትና የሚተገብሩት ትልቅ አላማና የጉዳዮችም ሁሉ ቁንጮ ነው።
አላህ (ሱ.ወ) እንዲህ አለ፡-
الحشر: ١٨ - ١٩
“እላንተ ያመናችሁ ሆይ! አላህን ፍሩ፤ ማንኛይቱም ነፍስ ለነገ ያስቀደመችውን ትመልከት፤ አላህንም ፍሩ፤ አላህ በምትሠ ሩት ሁሉ ውስጠ ዐዋቂ ነው፡፡ እንደነዚያም አላህን እንደ ረሱትና ነፍሶቻቸውን እንዳስረሳቸው (ሰዎች) አትኹኑ፡፡ እነዚያ እነሱ አመጸኞቹ ናቸው፡፡”   (አል-ሐሽር፡ 18-19)
ቀደምት ሶሓቦች በዲን ውስጥ የስምሪት አቅጣጫቸውና ተልእኮአቸው ዘርፈ ብዙ ነበር፡፡ እስልምናን ከምንም አንስተው በሁለት እግሩ ይቆም ዘንድ በፅኑ ታግለዋል። ከትግሉ በኋላም በሁሉም ሁኔታዎች ውስጥ ምርጥ ፅናትን ተላብሰዋል፡፡ በመጋዝ ለሁለት ቢከፍሏቸውም፤ በቁም በሕይወትም ሣሉ ሥጋቸውን ቢተለትሏቸውም፤ ከነህይወታቸው በፈላ ዘይት ቢቀቅሏቸውም፤ መልሳቸው ‘ከኢማናችን  ፍንክች አንልም’ የሚል ነበር። ይህ ከፅናትም በላይ የሆነ መስዋእትነት ነው።

እኛ ግን በዲን ላይ ትግል አላስፈለገንም፡፡ ፈተናም ብዙ አልገጠመንም፡፡ አላህ (ሱ.ወ) ሽቶልን ከእናት አባቶቻችን በስጦታ መልክ የወረስነውን ዲን እንድንፀናበት ብቻ ነው የተፈለገው፡፡ ቢሆንም አልቻልንም፡፡ ለምን አልቻልንም ከተባለ ሰበባችን ብዙ ነው፡፡ ሥራችን ሁሉ የልጅ የዕቃ ዕቃ ጨዋታ ዓይነት ይመስላል- ጧት የያዝነውን ኢማን ከሰዓት እንለቃለን፡፡ ትናንት የጀመርነውን ሱና ዛሬ እንተዋለን፡፡ ሣምንት ማመን ሣምንት መክፈር ይመስላል ባህሪያችን።

በዲን ላይ መፅናት /ኢስቲቃማ/ እጅግ ምርጥ ባህሪ ቢሆንም አብዛኞቻችን ግን አልታደልነውም፡፡ በያዙት ነገር ላይ በተለይ ሱናዊ ነገሮች ላይ አለመፅናትን ፋሽን አድርገን የያዝን ይመስላል።

ወዳጆቼ! በዲኑ መንገድ ላይ ነገራችን ሁሉ የሆይ ሆይ የወረትና የፋሽን ዓይነት መሆን የለበትም። ከማድረጋችን በፊት የውስጣችንን ፅናት ልክ ልናውቅ ይገባል፡፡ ከያዝን በኋላ ደግሞ የቻልነዉን ያህል መበርታት፣ መፅናትና መርጋት ይጠበቅብናል፡፡ ያዝ ለቀቅ ዓይነት ባህሪ በእስልምናችን አይወደስም፡፡ ለመያዝም ጥድፊያ ለመልቀቅም ጥድፊያ አይመከርም። ይህ ዓይነቱ ድርጊት በአላህ (ሱ.ወ) ዘንድ ያስተዛዝበናል፡፡ ሰዎችንም ያስጠቁምብናል፡፡ የእስልምናንም ሆነ ዲኑን በትክክል የያዙትን ሰዎች ማስጠቆርና ስም ማጥፋት ይሆንብናል።

ይቀጥላል ....
 
http://t.me/MuhammedSeidABX
362 views18:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-03-10 21:07:22 http://t.me/MuhammedSeidABX
346 views18:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-03-10 21:07:05

340 views18:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-03-10 14:15:09 ኢስቲቃማ  (በዲን ላይ መፅናት)

(1)
ከ”ህልም አለኝ” መጽሐፍ
በሙሐመድ ሰዒድ (ABX)
 
“እንደታዘዝከውም ቀጥ በል:: ከአንተ ጋር ያመኑትም (ቀጥ ይበሉ)፡፡ ወሰንንም አትለፉ፤ እርሱ የምትሠሩትን ሁሉ ተመልካች ነውና፡፡ (ሁድ፡ 112) ይላል አላህ (ሱ.ወ) ፡፡
በዚህች ታላቅ የቁርኣን አንቀፅ አላህ (ሱ.ወ) መልዕክተኛውን (ሰ.ዐ.ወ) በሃይማኖቱ ላይ፣ በትክክለኛው የአላህ (ሱ.ወ) ጎዳና፣ በአምልኮው እና ወደ አላህ (ሱ.ወ) ጥሪ በማድረጉ ሥራ ላይ ፀንቶ እንዲጓዝ አዘዛቸው። እኛንም አዘዘ፡፡ በርግጥም ትእዛዙ ከባድ ነበር፡፡ በዲን ላይ መፅናት ከባድ ትግልን የሚጠይቅ ነው፡፡
 የጉዳዩን ከባድነት ያወቁት ታላቁ ነቢይ (ሰ.ዐ.ወ) ያለምንም መታከት መሰላቸትና ተስፋ መቁረጥ በርካታ ግፍና በደል እየቀመሱ ዕረፍትም ያስፈልገኛል ሣይሉ 23 ዓመታትን ሙሉ የተሰጣቸውን ታላቅ ሀላፊነት በማድረስና አላህን አሳምሮ በመገዛት ላይ ፀኑ፤ ረጉ፤ መሬት ያዙ፡፡ ከዚህች የቁርአን አንቀፅ መውረድ በኋላ ነቢያችን (ሰ.ዐ.ወ) በበለጠ ሁኔታ ጠንካራና ቆራጥ እንደሆኑና አንድም ቀን ሲስቁ ታይተው እንዳልነበር ይነገራል።
ታላቁ ሰሓባ ዐብዱላህ ኢብኑ ዐባስ (ረ.ዐ)  ‹ከሙሉው ቁርኣን ውስጥ ከዚህች አንቀፅ በበለጠ በአላህ መልዕክተኛ ላይ የወረደ ጠንካራና አስጨናቂ አንቀፅ የለም፡፡›  ሲል ተናግሯል።
ይህ ሁሉ የሚያመለክተን ነገር ቢኖር በዲን ላይ መፅናት (ኢስቲቃማ ማድረግ) ምን ያህል ከባድ እንደሆነ ነው።
ወዳጆቼ! የሰው ልጅ በባህሪው ወላዋይ ነው፡፡ ተኮትኩቶ ያደገበትን ምርጥ ዲናዊ ስብዕና እስከ መጨረሻውና እስከ ህልፈተ ህይወቱ ድረሰ ይዞ የሚዘልቅም ጥቂት ነው፡፡ ልጅነቱን በጥሩ ኢስላማዊ ሥነምግባር  ያድግና፤ በወጣትነቱም ተሻሽሎ ይወጣና ብቻ ከእድሜው እርከኖች አንዱ ላይ ሲደርስ ምክንያቱ ግልፅ ባልሆነ ሁኔታ ሸይጧንና ስሜቱን የሚጋፈጥበት የመከላከያ አቅሙ ወርዶ ኢማኑ የኋላ ማርሽ ይረግጥና አይሆኑ ሆኖ ብትንትኑ ይወጣል፡፡ በተለይ በወጣቱ አካባቢ ይህ ጉዳይ ተባብሷል፡፡
ስንቱ አለ መሰላችሁ - እንደ ሸንበቆ ወጥቶ ወጥቶ እንደ ዱባ የተንከባለለ! በምግባሩ መላኢካን ከመሰለ በኋላ ከሸይጧን ጎራ የተቀላቀለ! ሲመራ ቆይቶ ውራ የሆነ፡፡ … ዐሊ ወደ አሌክስ የተለወጠው፣ መርየም ሜሪ በሉኝ ያለችኝ፣ ረሒማ ሪችን የመረጠችው፣ ጀማል ወደ ጆን ነኝ የመለወጥ ሚስጢሩ በኢማን አቋም መውረድ፤ በዲን ላይ የመፅናት (ኢስቲቃማ) የማጣት ውጤት ነው።
የበኒ ሰዕድ ሰዎች የሚኖሩት በጧኢፍ ነው። ከሀዋዚን ጎሣ የሆኑ ሲሆን በጥቢ የነቢዩ ወንድሞችም ናቸው። ከነርሱ መካከል አንዱ የሆነው ደማም ኢብን ሠዕለባ ግመሉን ተሣፍሮ የአላህ መልእክተኛ (ሰ.ዐ.ወ) ዘንድ መጣ። ግመሉን ከመስጅዱ መግቢያ ላይ አሠረና ወደ ውስጥ ገባ። የአላህ መልእክተኛ (ሰ.ዐ.ወ) ጋደም ብለው ለሶሓቦቻቸው ምክር እየሠጡ ነበር። ሶሓቦቻቸውም ወፎች በጭንቅላታቸዉ ላይ ያሉ ያህል ያለምንም እንቅስቃሴ ፀጥ ብለው ያዳምጧቸዋል። ደማም ገባና ‹የዐብዱልሙጠሊብ ልጅ የታለ ?› በማለት ጠየቀ። የአላህን መልእክተኛ ማለቱ ነው። ያለአንዳች ከልካይ ዱላውን እንደያዘ በሰዎች መካከል ቆራርጦ ወደፊት ተጠጋ። የአላህ መልእክተኛ (ሰ.ዐ.ወ) በሰውየው ሥርኣተ አልበኛነት ሣይቆጡና ሣይሠማቸው ‹አቤት እኔ ነኝ፡፡› አሉት። ሰውየውም ‹እኔ እጠይቅሃለሁ ጥያቄዬንም አጠነክርብሃለሁ።› አላቸው። ‹ደስ ያለህን ነገር ጠይቅ፡፡› አሉት።
‹ሰማይን ከፍ ያደረገው ማነው?› አላቸው፡፡
‹አላህ ነው፡፡› አሉት
‹ምድርንስ የዘረጋው?›
አላህ።
‹ተራራን የቸከለውስ?›
‹አላህ።›
‹እንግዲያውስ ሰማይን ከፍ ባደረገው፤ ምድርን በዘረጋው እና ተራራን በቸከለው (ጌታ) እጠይቅሃለሁ። እውን አላህ ነው ወደኛ መልእክተኛ አድርጎ የላከህ?› አላቸው፡፡
የአላህ መልእክተኛ (ሰ.ዐ.ወ) ተጋድመው ከነበሩበት ተነስተው ቁጭ አሉ፡፡ ፊታቸው ተለዋወጠ።
 ‹አዎን በአላህ ይሁንብኝ!› አሉት።
ደግሞ ጠየቃቸው
‹እውን አላህ ነው በቀንና በለሊት ውስጥ አምስት ሶላቶችን እንድንሠግድ እንድታዘን ያዘዘህ?›
 ‹አዎን በአላህ ይሁንብኝ!› አሉት፡፡
‹እውን አላህ ነው የረመዷንን ወር ፆም እንድንፆም እንድታዘን ያዘዘህ?›
‹አዎን በአላህ ይሁንብኝ!› ‹እውን አላህ ነው ከሀብታችን ዘካን እናወጣ ዘንድ ያዘዘህ?›
‹አዎን በአላህ ይሁንብኝ።› አሉት፡፡
‹በእድሜያችን አንዴ ሐጅ እንድናደርግስ እውን አላህ ነው እንድታዘን ያዘዘህ?›
‹አዎን በአላህ ይሁንብኝ› አሉት።
ሰውየውም በመቀጠል እንዲህ አለ - ‹ከአላህ በስተቀር ሌላ አምላክ የሌለ ስለመሆኑ እመሠክራለሁኝ። አንተም የአላህ መልእክተኛ መሆንህን እንዲሁ። ወላሂ በሰማሁት ነገር ላይ አንዳች ነገር አልጨምርም፤ አልቀንስምም። እኔ ደማም ኢብን ሠዕለባ የበኒ ሰዕድ ኢብን በክር ወንድም ነኝ።› በማለት ወደ ግመሉ ተመለሠ። የአላህ መልእክተኛ (ሰ.ዐ.ወ) በዚህን ጊዜ ፈገግ አሉ። በማስከተልም ‹ወደ ጀነት ሰው መመልከት ደስ ያሠኘው ሰው ወደዚህ ሰውዬ ይመልከት፡፡› አሉ። (ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል)
 
ወዳጆቼ! በዚህ ሐዲሥ ነቢያችን (ሰ.ዐ.ወ) የመፅናትን ወሣኝነት ለጠያቂያቸው ነግረውታል፡፡ ሰው ጥቂትም ቢሆን በያዘው መልካም ነገር ላይ መፅናቱ ከፍ ያለ ምንዳ ሊያገኝ እንደሚችል አስተምረውናል፡፡

http://t.me/MuhammedSeidABX


ይቀጥላል ...
655 viewsedited  11:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-03-10 14:12:14
606 views11:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-03-08 21:45:03 ሱብሒ መነሳት ለከበደው
***
የሱብሒ ሶላት ከአምስቱ የግዴታ ሶላቶች አንዷ ናት፡፡ ትልቅ ትሩፋት ያላት ሶላትም ናት፡፡ ግና ለሱብሒ መነሳት አለመቻል የብዙ ሙስሊሞች በተለይ ወጣቶች ችግር ነው፡፡ በዚህም የተነሳ የአላህ መልዕክተኛ (ሰ.ዐ.ወ.) እንዳሉት ከመናፍቃን እንዳንሆን ያሰጋል፡፡ እርሣቸው “በመናፍቃን ላይ ከባባዶቹ ሶላቶች የሱብሒ እና የዒሻ ናቸው፡፡ ….” ብለዋል፡፡

በተለይ በዚህ ዘመን ሱብሒን ላለመነሳትም ምክንያቱ ብዙ ሲሆን ወጣቶች ዘንድ በዋናነት የሚጠቀሰው ሶሻል ሚዲያው ላይ ተጥዶ ማምሸት ነው፡፡ ብዙዎች ምሽቱን ገፍተው ስለሚተኙ ለሱብሒ ሶላት መነሳቱ ከባድ ጀግንነትን የሚጠይቅ ሆኗል፡፡ ሱብሒን በጀማዓ የሰገደ ሰው በርግጥም በራሱም ሆነ በሸይጧን ላይ ትልቅ ድልን የተቀዳጀው ማለት ይቻላል፡፡
በርግጥ ብዙዎች ለሱብሒ ሶላት መነሳትን ቢመኙም፤ ካመለጠቻቸው በኋላ ቢፀፀቱም ቁርጥ ዉሳኔ ለማድረግ ሲቸገሩ ይታያል፡፡ ቀጥሎ ለሱብሒ ሶላት ለመነሳት አጋዥ ምልከታዎችን እነሆ፡-

1- መልካም ኒያን ማሳደር
እነሳለሁ ብሎ መወሰን፤ በአላህ በመመካት ቁርጥ ዉሳኔ ማሳደር፡፡
2- አላህን እውነተኛ ፍራቻ መፍራት
አላህ የሚፈሩትን ባሮቹን ያግዛል፣ በአምልኮዉም ላይ ይረዳቸዋል፡፡
3- ሶላቶችን በትክክል መስገድ
ትክክለኛ ሶላት ከመጥፎ ነገር ትከለክላለች፣ አንዷ ለሌላኛዋ መሳካት ታግዛለች፡፡
4- ከወንጀል መራቅ
ወንጀል መልካም ሥራን ይከለክላል፣ ከበጎ ነገር ይጋርዳል፣ ከኸይር ሥራ ያቆራርጣል፡፡
5- ኢስቲግፋር ማብዛት
ኢስቲግፋር ነገሮችን ያገራል፣ የከበደን ሁሉ ያቀላል፡፡
6- ቀኑን በመልካም ሥራዎች ተጠምዶ መዋል
መልካም ሥራ መልካምን ይወልዳል፤ ወንጀል ግን ወንጀልን ነው የሚያበቅለው፡፡
7- - ምንዳዉንና ትሩፋቱን ማሰብ
ሱብሒን በጀማዓ የሰገደ ቀኑን ሙሉ የአላህ ጥበቃ አለለት።
8- ብዙ አለማምሸት
ነቢዩ ሰ.ዐ.ወ ከዒሻ በኋላ ብዙ አይቆዩም ነበር፡፡
9- ከመተኛት በፊት ሁለት ረከዓ መስገድ
10- ጦሃራ ላይ ሆኖ መተኛት
ንጽሕና አካልና መንፈስን ያቀላል፣ ነሻጣን ይጨምራል፣ ሸይጧንን ያባርራል፡፡
10- ዱዓ ማድረግ
አላህ የከበደንን ሁሉ እንዲያገራልን፣ የምንመኘዉን ሁሉ እንዲያሳካልን፡፡
11- የእንቅልፍ ጊዜ ዚክሮችን አለመርሳት፣ ነቢያዊ ሱናዎችን መፈፀም፡፡
12- ለሌሊት ሶላት መነሳትን መነየት
የሌሊት ሶላት ምንዳዋ ትልቅ፣ ትሩፋቷም ብዙ ነዉና፡፡
13- አልነሳም ብለው ከሰጉ አላርም መሙላት፣ ሌሎች ሰበቦችንም መጠቀም፡፡

https://t.me/NejashiPP
794 views18:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-03-08 15:07:29 ፨ ዘወትር አንድ ጫማ መልበስ ነዉር አይደለም፤
፨ ሁሌም የሚታወቁበት ጃኬት መደረብም ዉርደት ሊሆን አይችልም፣
፨ ዛሬ ላይ ሆነው የድሮዉን የኖኪያ ስልክ መያዝም ዝግመት አይደለም፣
፨ በጊዜ ወደ ቤት ለመግባት መጣደፍም ጥፋት አይደለም፤
፨ ቤተሰብህን ለመደገፍ ብለህ ሥራ ሳትመርጥ መሥራትም ድክመት አይደለም፡፡


ድክመት ማለት ሰዉን ሁሉ እኩል ለማስደሠት ብሎ መውደቅ መነሳት ነው፡፡

“ሰዎችን ሁሉ ማስደሰት ፈጽሞ የማይደረስበት ድካም ነው፡፡” ይላሉ ኢማም አሽ-ሻፊዒ፡፡

በመንገድህ ቀጥል ወዳጄ፡፡



 http://t.me/MuhammedSeidABX
1.1K views12:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ