Get Mystery Box with random crypto!

ABX

የቴሌግራም ቻናል አርማ muhammedseidabx — ABX A
የቴሌግራም ቻናል አርማ muhammedseidabx — ABX
የሰርጥ አድራሻ: @muhammedseidabx
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 8.70K
የሰርጥ መግለጫ

ወደ ቤታችሁ እንኳን መጣችሁ!!

Ratings & Reviews

2.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 62

2021-02-12 04:14:16 ማስታወሻ -
ሌሊት ላይ ከእንቅልፉ ለተነሳ ሰው
*
ከዑባደህ ኢብኑ አስሷሚት (ረ.ዐ.) እንደተወራው ነቢዩ (ሰ.ዐ.ወ.) እንዲህ ብለዋል፡-
‹ሌሊት ከእንቅልፉ ነቅቶ ‹ላ ኢላሀ ኢልለላህ ወሕደሁ ላ ሸሪከ ለሁ፤ ለሁ-ልሙልኩ ወለሁ-ልሐምዱ ወሁወ ዐላ ኩልሊ ሸይኢን ቀዲር፡፡ ወልሐምዱ ሊልላህ፣ ወሱብሓነላህ፣ ወላ ኢላሀ ኢልለላህ፣ ወሏሁ አክበር፣ ወላ ሐውለ ወላ ቁውወተ ኢልላ ቢልላህ፡፡› ያለና
ከዚያም ‹አልላሁምመ-ግፊር ሊ/አላህ ሆይ ማረኝ፡፡› ያለ ወይም ሌላ ዱዓ ያደረገ እንደሆነ አላህ ለዱዓኡ ምላሽ ይሠጠዋል፡፡ ዉዱእ ቢያደርግም ሶላቱ ተቀባይነት አለው፡፡›  (ቡኻሪ ዘግበውታል፡፡)
ትርጉሙ -/ከአላህ በስተቀር ሌላ አምላክ የለም፡፡ አንድ ነው፡፡ አጋር የለወም፡፡ ንግሥና ለሱ ነው፡፡ ምስጋና ለሱ ነው፡፡ እሱ በሁሉም ነገር ላይ ቻይ ነው፡፡ ምስጋና ለአላህ ነው፣ ጥራት ይገባው፣ ከርሱ በቀር ሌላ አምላክ የለም፣ አላህ ትልቅ ነው፣ በአላህ እንጂ ብልሃትም ሆነ ሀይል የለም፡፡/
****
ከዓኢሻ (ረ.ዐ.) እንደተወራው የአላህ መልእክተኛ ሰ.ዐ.ወ ሌሊት ላይ ከእንቅልፋቸው ሲነቁ
‹ላ ኢላሀ ኢልላ አንተ ሱብሓነከ-ልላሁምመ አስተግፊሩከ ሊዘንቢ ወአስአሉከ ረሕመተከ፡፡ አልላሁምመ ዚድኒ ዒልመን፣ ወላ ቱዚግ ቀልቢ በዕደ ኢዝ ሀደይተኒ ወሀብ ሊ ሚን ለዱንከ ረሕመተን ኢንነከ አንተ-ልወሃብ፡፡› ይሉ ነበር፡፡ ብላለች፡፡ (አቢ ዳውድ ዘግበውታል፡፡)

ትርጉሙ -/ካንተ በስተቀር ሌላ አምላክ የለም፡፡ ጥራት ይገባህ፡፡ አላህ ሆይ! ለወንጀሌ ምህረትህን እለምናለሁ፡፡ እዝነትህንም እለምናለሁ፡፡ አላህ ሆይ! ዕውቀትን ጨምርልኝ፡፡ ከመራሀኝ በኋላም ቀልቤን ለጥመት አትዳርጋት፡፡ ካንተ ዘንድ የሆነ እዝነትም ስጠኝ፡፡ አንተ እጅግ ለጋስ ነህና፡፡›
***
   ከአቢ ሁረይራ ረ.ዐ እንደተወራው የአላህ መልእክተኛ (ሰ.ዐ.ወ) እንዲህ ሲሉ ሰማሁ አለ ‹ኃያሉና የተከበረው አላህ ለሙስሊም ባሪያ ሌሊት ነፍሱን የመለሠለት እንደሆነ ተስቢሕ ካደረገና /ሱብሓነላህ በማለት አላህን ካወደሰ/  ከሱም ምህረትን ከጠየቀ አላህ ዱዓኡን ይቀበለዋል፡፡› (ኢብኑ አስሱንኒይ ዘግበውታል፡፡)
****
በኢማም ማሊክ አል ሙወጦእ ውስጥ በሶላት መጽሐፍ በዱዓእ ምዕራፍ መጨረሻ ላይ እንደተላለፈው አቢ አድ-ደርዳእ ረ.ዐ በመሃል ለሊት በመነሣት
‹ናመቲ-ልዑዩኑ፣ ወጋረቲ-ንኑጁሙ፣ ወአንተ ሐይዩን ቀይዩም፡፡› እንደሚል ደርሷቸዋል፡፡
ትርጉሙ -/ዐይኖች ተኙ፡፡ ከዋክብቶች ገቡ፡፡ አንተ ግን ህያው እና የሁሉ ነገር አስተናባሪ ነህ፡፡/

ምንጭ ፡ አል-አዝካር አን-ነወዊ
ትርጉም፡ በሙሐመድ ሰዒድ
ነጃሺ መፃሕፍት መደብር

http://t.me/MuhammedSeidABX
1.3K viewsedited  01:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-11 08:59:39

1.1K views05:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-10 13:10:49 አልሃኩም አት-ተካሡር
በብዛት መፎካካር (ጌታቸሁን ከመገዛት) አዘናጋችሁ
**************
ኢብኑ ከሢር እንዳብራሩት 'የሰው ልጅ ምቾትና ዕብሪት የተሞላባቸው ፉክክሮች የመጪውን ዓለም መጀመሪያ ተደርጎ የሚቆጠረውን መቃብርን ያስረሳሉ። ይህም ሰዎች በሞት አማካይነት ወደዚያ ወደሚጠሉት ጉድጓድ እስኪገቡ ድረስ በዝንጋቴ ላይ እንደሚዘወተሩ ያሳያል።' ብለዋል ።


ኢማም አሕመድ ዐብደላህ ኢብን አል-ሻኪር (ረ.ዐ) እንዲህ ማለቱን ዘግበዋል “የአላህ መልዕክተኛ (ሰ.ዐ.ወ) 'አልሃኩም አት ተካሡር ”ን እያነበቡ መጣሁ፤ ከዚያ በኋላ እንዲህ አሉ፡-
“ የአደም ልጅ ገንዘቤ ገንዘቤ ይላል። ከተመገበዉና ከጨረሰው፣ ለብሶ ካሳለቀው፣ ወይም በምጽዋት  ከሰጠዉና ተቀማጭ ከሆነለት ውጭ ምንም የሌለው  ሲሆን።”

የአላህ መልዕክተኛ (ሰ.ዐ.ወ) የሚከተለውን ሲናገሩ ሰማሁ በማለት አነስ ኢብኑ ማሊክ (ረ.ዐ) አስተላልፈዋል፡-
“ የአደም ልጅ ዕድሜው እያረጀ ሲሄድ ሁለት ነገሮች አይለዩትም፤ እነርሱም ዱኒያን መውደድና፣ ረዥም ዕድሜ ለመኖር መመኘት ናቸው።"

አል- ሓፊዝ ኢብን ዐሳኪር የአል-አሕነፍ ኢብን ቀይስን የሕይወት ታሪክ ሲጽፉ እንዲህ ብለዋል፡- “አንድ ጊዜ አሕነፍ አንድ ሰው ዲርሃም ይዞ ያያል። “ይህ ዲርሃም የማን ነው? አለ። የያዘው ሰው “የኔ ነው” አለው። አል-አሕነፍ በመልካም ነገር የአላህን ምንዳ በመሻት ካወጣኸው ያንተ ነው ካለው በኋላ፡-
 በመልካም ነገር ላይ ስታወጣው፣
  ሀብትህ  ቀላል ይሆናል ጣጣው
 ጨምድደህ በመያዝ ከሳሳህ
ያሳርህ ሰበብ ይሆናል የመከራህ ።
በማለት የአንድን ሰው ግጥም አነበበ።
“ተከልከሉ ወደፊት (ውጤቱን ታውቃላችሁ ከዚያም ተከልከሉ ወደፊት ታውቃላችሁ።) (አት ተካሡር 3-5) የሚሉትን አያዎች አስመልክቶ አል-ሐሰን አል በስሪ (አላህ ይዘንላቸውና) “ይህ ተደጋጋሚ ዛቻ ነው” ብለዋል።
  
በሶሒህ የሚከተለው ተላልፏል፡-
ዑመር ኢብን አል-ኸጧብ (ረ.ዐ) ወደ አላህ መልዕክተኛ (ሰ.ዐ›ወ) ሲገቡ ባለቤቶቻቸው አናደዋቸው በአንድ ክፍል ውስጥ ጋደም ብለው አገኙዋቸው። የተጋደሙበት ምንም ዓይነት ምንጣፍ ያልተደረገበት ባዶ ሰሌን ላይ ነበር። በቤቱ ውስጥ ከዘንባባ ቅጠል የተሠራ ትራስ በስተቀር አንዳች ቁሳቁስ አልነበረም። ዑመር (ረ.ዐ) ይህን ሁኔታ ሲያዩ ማልቀስ ጀመሩ። የአላህ መልዕክተኛ (ሰ.ዐ.ወ) “ለምን ታላቅሳለህ ዑመር ሆይ!” አሏቸው። ዑመር (ረ.ዐ)እንዲህ አሉ፡- “ የአለህ መልዕከተኛ ሆይ! ኪስራና ቄሳር እጅግ ባለፀጎች ሲሆኑ የዚህችን ዓለም ፀጋዎች ተስጥተው ይምባሻበሻሉ። እርስዎ ግን አላህ ከፍጡራኑ ሁሉ አስበልጦ የመረጠዎት ሆኖ ሳለ ይህን የመሠለ ሕይወት ይገፋሉ።” ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) እንዲህ አሉ “የኸጣብ ልጅ ሆይ! መጪው ዓለም ከቅርቢቱ ዓለም እንደሚበልጥ ትጠራጠራለህን? እነዚህ ሰዎች (የበጎ) ሥራዎቻቸውን ምንዳ በዚህች ዓለም ላይ እየተሰጡ ነው።”

  አቡ ሰዒድ አል-ኹድሪ(ረ.ዐ) እንዲህ ሲሉ አስተላልፈዋል፡- “የአላህ መልዕክተኛ (ሰ.ዐ.ወ) ሚንበር ላይ ተቀመጡ። እኛም በዙሪያቸው ተቀመጥን። እንዲህ አሉ፡- ከኔ(ሕልፈት) በኋላ የምፈራላችሁ የሚከፈትላችሁን የዚህችን ዓለም ተድላና ውበት(ጌጥ) ነው።” (ቡኻሪና ሙስሊም)
  
የአላህ መልዕክተኛ(ሰ.ዐ›ወ) ኃያሉ አላህ እንዲህ ብሏል በማለት መናገራቸውን አቡ ሁረይራ (ረ.ዐ) አስተላልፈዋል፡-
 “የአደም ልጅ ሆይ! እኔን በማምለክ ራስህን ብታስጠምድ ልብህን (በሃብት) በመሙላት ከድህነት አወጣሃለሁ። ካልሆነ ግን ልብህን (ደረትህን) በዓለማዊ ጉዳዮች በመሙላት ድህነት እንዳይለቅህ አደርጋለሁ።”

ዘይድ ኢብኑ ሣቢት(ረ.ዐ) የአላህ መልዕክተኛ (ሰ.ዐ›ወ) የሚከተለውን ሐዲሥ አል-ቁድስ ሲናገሩ ሰማሁ አሉ፡-
“ግቡ (ትኩረቱ) ሁሉ ለዚህች ዓለም ሕይወት የሆነ ሰው  ጉዳዩን ሁሉ በመበታተን ድህነቱን በሁለቱ ዓይኖቹ መሃል አደርግበታለሁ። እኔ የወሰንኩለትን እንጅ አንዳች አያገኝም። ግቡ(ትኩረቱ) ሁሉ የመጪው ዓለም ጉዳዮች የሆነ ሰው ሃብቱን ሁሉ በልቡ ውስጥ አደርግለታለሁ። ይህች ዓለም (ዱኒያ) ወዳም ሆነ ተገዳ ትመጣለታለች።” 

   አቡ ሁረይራ(ረ.ዐ) እንዳስተላለፉት የአላህ መልዕክተኛ (ሰ.ዐ.ወ) እንዲህ ብለዋል፡-“ ከእናንተ (በሃብት) ዝቅ ወዳለው ሰው ተመልከቱ። ከፍ ወዳለው አትመልከቱ። ይህን ማድረጋችሁ የአላህን ፀጋዎችና ውለታዎች አሳንሳችሁ እንዳታዩ ይረዳችኋልና።”

አቡ ሁረይራ (ረ.ዐ) እንዳስተላለፉት የአላህ መልዕክተኛ(ሰ.ዐ.ወ) እንዲህ ብለዋል፡-
“የዲናር የዲርሃምና የውብ አልባሳት ባሪያ ከሰረ። ሲሰጥ(ሲያገኝ) ይደሰታል። ካልተሰጠ(ካጣ) ደግሞ ይከፋዋል።”

ምንጭ ፦ ወደ አላህ ሽሹ መጽሐፍ
በአሕመድ ሑሴን (አቡ ቢላል)
ነጃሺ መፃሕፍት መደብር
1.3K views10:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-10 05:52:52 ማታ ሰምቻቸው አሊያም በዉስጤ ይዣቸው ተጋድሜ ሌሊት ጭምር ከእንቅልፍ የሚያነቁኝ ትክክል አይደሉም ብዬ የማስባቸው የብዙሃን ሰዎች ሀሳቦች አሉ፡፡

“የተፈታች ሴት ለሁለተኛነት እንጂ ለአንደኛነት አትገባም፡፡” ይለኛል ይሄ …፡፡

በ “ፈታለች” ሥም ክብሯን ሊቀንስ፣ ዋጋዋን ሊቆርጥ፣ ደረጃዋን ሊያወርድ፣ ጥራቷን ሊያደበዝዝ፣ በርካሽ ሊያገኛት፣ እንደ ሰከንድ ሃንድ ዕቃ ሊያያት ያስባል፡፡ ወይኔ ሰውየው ...

አስታውስ -
የ40 ዓመቷ ምርጧ እመቤት ኸዲጃ ለ25 ዓመቱ ሰው ታላቁ ወጣት ነቢይ የመጀመርያ ሚስታቸው ነበረች፡፡ ከርሳቸው በፊት አግብታ የፈታች ናት፤ ልጅም ነበራት።
ጠየቀቻቸውና ተጋቡ። አብዝተው ወደዷት፡፡ “ፍቅሯን ተሠጠሁኝ፡፡” ሲሉም የፍቅራቸዉን ጥግ ገለፁ፡፡ እስክትሞት ድረስም ሌላ አላገቡም፡፡ ካለፈች በኋላ ትዝታዋ ከዉስጣቸው አልጠፋም፡፡

ሰው የሚመዘነው በሰዉነቱ ሰው ነው፡፡ ሁለተኛ ደረጃ የለዉም፡፡ መውረድ እንጂ መውለድ አያወርድም፡፡ በአንድ ትዳር አለመዝለቅ በሌላ አለመዝለቅን አያመለክትም፡፡ መልካምነት በመልካም ሥነምግባር ይገለፃል፤ ዲን ያላት ዲን ከሌላት ይመረጣል፡፡ ዲን እና ስብዕና ከሙቀት እና ዉበት በላይ ብዙ ዘመን ያሻግራል፡፡
እንደው በሁሉ ነገር ነፍሲ ነፍሲ ባንል ምን አለበት !

አሏሁል ሙስተዓን፡፡

http://t.me/MuhammedSeidABX
1.2K views02:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-09 19:13:51 ዕድሜው ገፋ፣
አጥንቱ ደከመ፣
ፀጉሩ በሽበት ተንቀለቀለ፣
ሚስቱም መሃን ነበረች።
እንዲህም ሆኖ ዘከርያ ከአምላኩ ተስፋ አልቆረጠም ።
'አንተን ለምኜማ ዕድለቢስ አልሆንም። ልጅ ስጠኝ፣ ብቻዬን አታስቀረኝ ...' አለ።
የማይሆን በሚመስል ጉዳይ ላይ ዱዓ አደረገ።
አብዝቶ ተማፀነ፣ ያ ረብ! አለ።
ፈጣሪው ሰማው፣
ዱዓው ምላሽ አገኘ፣
በየሕያ ተበሰረ።

ኢማን ሲኖር፣ የቂን ሲኖር... ሁሉም ነገር ቅርብ ነው።
ትዳር፣ ልጅ፣ ሀብት፣ ... ለአላህ ሲነግሩት እሩቅ አይደለም ።
እንዴት ያ ረብ! ማለት ያቅታችኋል!?
ኢማናችሁ ከልብ ይሁን። የቂናችሁ ከፍ ይበል። እሱ ተለምኖ የከለከለው የለም።

ችግራችሁ ሁሉ ተፈቶ ይደር
ያ ረብ!

http://t.me/MuhammedSeidABX
1.3K views16:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-09 10:21:49 ዱዓ ያስፈልገዋል

(ክፍል ሁለት)
ከአላህ ጋር መጽሐፍ
(ABX)

በርግጥም ከዱዓ በላይ ምን አለ!!፡፡ የሰማይ ቤት ወሬ እያነፈነፈች የምትኖር ትመስላለች ታለም፡፡ የሆነ መጥፎ ነገር ሊከሠት እንደሆነ ከሰማች አሊያም ወሬ ያመጡላት እንደሆነ ያንን ክፉ ወሬ በዱዓ ልትቆጣጠረው ትፎክራለች፤ “ቆይ ለሱም ዱዓ አለለት!” ትላለች፡፡ በዱዓ ትተማመናለች፡፡ በዱዓ ትዝታለች፡፡
እጅግ በዱዓ አድራጊነታቸው ከምገረምባቸው ከተሞች መካከል አንዷ ጎንደር ናት፡፡ ትላልቅ ዑለሞች ይገኙባታል፡፡ ጎንደር የበረካ አገር ነው፡፡ የበረከቱ ሚስጢር ዱዓ ይመስለኛል፡፡ ሙስሊሞቿ በደግነታቸው አይታሙም፡፡ በየምክንያቱ ሶደቃ ያበዛሉ፡፡ ብሉልን ጠጡልን ይላሉ፡፡ ገርነት፣ መውደድ የሕዝቡ ባህሪ ነው፡፡ ከዚህም ባለፈ በዱዓቸው ይታወቃሉ፡፡ በዱዓቸው ይተማመናሉ፡፡ የሆነ ነገር መከሠቱን ከሰሙ፣ አሊያም ሊከሠት እንደሆነ መረጃው ከደረሣቸው፣ በየመስጊዱ ይጣራሉ፣ ለዱዓ ይነግራሉ ያስነግራሉ፡፡ ዱዓ እንዲያደርጉ ያሳውቃሉ፡፡

ጠላት እያሴረባቸው መሆኑን ካወቁ፣ አገር በበላእ ሊታመስ እንደሆነ ምልክቱ ከመጣላቸው፤ መረጃዉም ከደረሣቸው ዝም ብለው እጃቸዉን አጣጥፈው አይቀመጡም፤ ተመቻችተው እንቅልፍ አይተኙም፡፡ ሁሉን መጥፎ ነገር ማስቆምና መመለስ ወደሚችለው ወደ አምላካቸው አቤት ይላሉ፡፡ ሌቱን በዱዓ ያነጋሉ፤ ቀኑን በፆም ያሳልፋሉ፣ ወደ አላህ (ሱ.ወ.) ይዋደቃሉ፤ ወደ ፈጣሪያቸው ይማፀናሉ፡፡
በበላእ ሰሞንም ሆነ አንዳች አሳሳቢ ነገር ሲያጋጥም እንደየበላው ሁኔታና ደረጃ ቀናትና ወራት ድረስ ሊዘልቅ የሚችል የዱዓ አዋጅ ይታወጃል፡፡ የዱዓ ሳምንትና የዱዓ ወር ይፀድቃል፡፡ ከዚያም ዱዓው በጥብቅ እና ከልብ ይደረጋል፡፡ የሚገርመው ምላሹም አይዘገይም፡፡ ዱዓው እየተደረገ ሳለ የተመደቡለት ቀናቶች ሳይጠናቀቁ፣ ብዙም ሳይቆይ የድል ብሥራት ይመጣል፡፡ ሊቀሰቀስ የነበረው በላእ ይከሽፋል፤ የተነሳው በላእ መንገድ ላይ ይቀራል፡፡ የታሰበ  የጥፋት ድግስ ይከስማል፡፡  ጠላት መንገድ ላይ “እርሱ በርሱ” ተባላ የሚል ወሬ ይሰማል፡፡
እንዲህም ሆኖ በላው ተመለሰ ብለው ዱዓቸዉን አያቆሙም፤ እጃቸዉን አያወርዱም፡፡ እስከመጨረሻው በዱዓ ይፋለሙታል፡፡ በዚህ መልኩ ስጋት ይወገዳል፡፡ ፍርሃት ይነሳል፡፡ ሽብር ይገፈፋል፡፡ ዉጤት ካገኙበት በኋላም ይደሠታሉ፤ አምላካቸዉን አብዝተው ያመሰግናሉ፡፡

“ጎንደር በዱዓ ነው” የሚል መፈክር ሁሌ እሰማለሁ፡፡ አዎ ጎንደር በዱዓ ነው፡፡ በሚደረጉ ተደጋጋሚ ዱዓዎች ብዙ ዙር በላዎች በዱዓ ሲከሽፉ አይቻለሁ፡፡ 'ያዝልን!' ሲሉ ይይዝላቸዋል፣ 'አንሳልን!' ሲሉ ያነሳላቸዋል፣ 'እንዳያየን እንዳይሰማን አድርገው' ሲሉም ያደርግላቸዋል፡፡
በርግጥም የጎንደር ሙስሊም በዱዓ ነው፡፡ የአገሬው ሰው ሰው አይነካም፡፡ የነኩትንም በዱዓው ብቻ ነው ልክ የሚያስገባው፡፡ እንክትክቱን የሚያወጣው፡፡ የአገሬው አማኝ ከአላህ ጋር ነው፡፡ አላህም ከነርሱ ጋር ነው፡፡

ዱዓ ከመሣርያዎች ሁሉ የሚበልጥ ትልቅ መሣርያ እንደሆነ አምናለሁ፡፡ አላህ ከሠጠን ፀጋዎች ሁሉ ዱዓ ትልቁ ፀጋ ነው ብዬ አስባለሁ፡፡ ግና ይህንን መሣርያ አባክነነዋል፡፡ በአግባቡ አልተጠቀምንበትም፡፡ በትክክልም ሥራ ላይ አላዋልነዉም፡፡ እስቲ ምን ያህሎቻችን ነን ቢያንስ ከሶላት በኋላ ትዕግስት አድርገንና ጊዜ ወስደን ለአምስት ደቂቃ ያህል ዱዓ የምናደርግ? ለራሣችን ጥቅም መሰሰታችን ያሳዝናል፡፡

የታሰረ ማለትስ እጁ ከዱዓ የታሠረ ነው፡፡ የተነፈገ ማለትስ ዱዓ ከማድረግ የተነፈገ ነው፡፡ በርግጥ አላህ በልብ ያሰቡትንም ይሠጣል፡፡ ግና አላህ ባርያው እጁን አንስቶ ሰለምነው ይወዳል፡፡
ዱዓ ምድር ከሰማይ የምትገናኝበት ገመድ ነው፡፡ ባሮች ከአምላካቸው ጋር የሚተሳሰሩበት ሠንሠለት ነው፡፡ እጃችንን ካላነሳን፣ በምላሳችን ካልተማፀንን ግንኙነቱ ይቋረጣል፡፡ ብዙ ነገር መተው እንችላለን፡፡ ዱዓ ግን ፈጽሞ አንተው፡፡ ከዱዓ አንዘናጋ፡፡ በዱዓ ሕያው እንሆናለን፡፡ በዱዓ የተመኘነዉን እናገኛለን፤ ያለምነዉን  እናሳካለን፤ የጠፋብንን እናገኛለን፣ የጎደለብንን እንሞላለን፡፡
ዱዓን ሲቸግረን ብቻ አይደለም ማድረግ ያለብን፡፡ ሲጨንቀን ብቻ አይደለም ወደ አላህ መሮጥ ያለብን፡፡ በዱዓ የሌለንን ብቻ ሳይሆን ያለንንም፣ ያልገባንን ብቻ ሳይሆንን የገባንን፣ የማንችለዉን ብቻ ሳይሆን የምንችለዉን ሁሉ ከአላህ እንጠይቃለን፡፡ ያለንን እንዲባርክልን፣ ያጣነዉን እንዲለግሰን፣ ያለቀብንን እንዲተካልን እንማፀናለን፡፡
በዱዓ ስላለንበት ሁኔታ ሁሉ ለፈጣሪያችን እንገልፃለን፡፡ ከፍታና ዝቅታችንን፣ መውደቅ መነሳታችንን ሁሉ እናሳስብበታለን፡፡
ዱዓ ለሰው ብቻ አይደለም ለሁሉም ነው፡፡ ለሰው ለእንሠሣም ነው፡፡ ለትዳርም ለብቸኝነትም ነው፡፡ ለአገርም ለዓለምም ነው፡፡  
ዱዓ ጥቅሙ ሰፊ ነው፡፡ ዱዓ የሚደረገዉም ለራስ ነው፡፡ ሌሎች ስላላደረጉ ዱዓ አላደርግም አይባልም፡፡ ሌሎች ግድየለሽ ስለሆኑ ግድየለሽ መሆን አይገባም፡፡ ዓለም እንዲህ ችግሯ በዝቶ፣ ሁኔታዋ ከፍቶ፣ ሰላሟና ፍቅሯ ጠፍቶ .. ባለበት ሁኔታ የኔ ዱዓ ምን ሊለውጥ ብሎ ማጣጣልም ሆነ ተስፋ መቁረጥ ልክ አይደለም፣ ተገቢም አይደለም፡፡ ችግሮች እንዲህ በገዘፈ መልኩ ሊከማቹ የቻሉት በኛው ጥፋትና ቸልተኝነት ነው፡፡ እኔም፣ አንተም፣ አንቺም “ብቻዬን ጩኼ ምን ላመጣ!” ብለን እጃችንን አጣጥፈን በመቀመጣችን ነው፡፡ እኛ ካልጮኽን ሌላ የሚጮኽ ከየት ይምጣ ታዲያ፡፡

ዱዓ ማድረግ ሁሌም ከአላህ ጋር የመሆን ምልክት ነው፡፡ ዱዓ እናድርግ - ከአላህ ጋር እንሁን፤ ወደ አላህ እንቅረብ፡፡
ዱዓ ያልቻልነዉን ነገር ሁሉን ነገር ለሚችል ጌታ ማሳሰብ ነው፡፡ ማሰብም፣ ማሳሰብም ዱዓ ነው፡፡
ዛሬ ላይ ዱዓ የማያስፈልገው ነገር ምን አለ ወዳጆቼ!!
አዎ ሁሉም ነገር ዱዓ ያስፈልገዋል፡፡

http://t.me/MuhammedSeidABX
1.3K views07:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-07 12:39:42 "ዱዓ ያስፈልገዋል "

ከአላህ ጋር መጽሐፍ
(ABX)

(ክፍል አንድ)

“እስቲ ዱዓ አድርጉ” ትል ነበር እታለም አላህ ይዘንላትና፡፡ ዉድ እናት ነበረች፡፡ ምን ያረጋል ታድያ እሷም ሞተች፡፡ ሌሎች ሰዎች እንደሞቱት ሁሉ ሞተች፡፡ ከሰው በልጦ ከሰው እኩል መሞት ያሳዝናል፡፡ ሌሎች በተቀበሩበት አፈርም ተቀበረች፡፡ ከሰው ልዩ ተሁኖ በሰው አቀባበር መቀበር ቅር ይላል፡፡ አላህ መቃብሯን ብርሃን፤ መቀመጫዋን ጀነት ያድርገው፡፡

ታለም አፌን ከፍቼ የማዳምጣት አስታዋሽ እናቴ ነበረች፡፡ ወንድ ይሁን ሴት ትልቅ ሰው አጠገብ መቀመጥ ትርፉ ብዙ ነው፡፡ በተለይ የአላህ ሰው ሲሆን፡፡ ትልቅ ሰው ትልቅ የሕይወት ካዝና ነው፡፡ ምድር ላይ ካሳለፈው ረጅም ሕይወቱ ዱንያን ለመጋፈጥ ስንቅና ትጥቅ የሚሆንህን ብዙ ነገር ያካፍልሃል፡፡

 ሞት ለሁሉ እኩል የሆነ ክስተት ነው፡፡  ጥሩ ነው ብሎ ዱንያ ላይ የተወውም ሆነ የሚተወው አንድም ሰው የለም፡፡ ሞት ምርጦች የተባሉትን ሁሉ ጨክኖ ወስዷል፡፡ ምርጡን መርጦ የሚተው ቢሆን ኖሮ ተወዳጃችን የአላህ መልዕክተኛ (ሰ.ዐ.ወ.) በቀሩልን ነበር፡፡ ምድር ላይ የደረሱብን መከራዎች ሁሉ ከርሣቸው ሞት አንፃር ምንም ናቸው፡፡ በርሣቸው ሞት በርግጥም ብዙ ተጎድተናል፡፡

አላህን የማያወሳ፣ ነገሮችን የማያስተነትን፣ ዝምብሎ የሚኖር ፋዛዛ ሰው አትወድም ታለም፡፡ “ኤዲያ የማይረባ!” ትለዋለች፡፡ “የዱዓ ሰው ናት” ይላታል የሰፈሩ ሰው ሁላ፡፡ መጥፎ ሰው ስታይ፣ መጥፎ ነገር ስታይ፣ መጥፎ አስተሳሰብ ስታይ፣ መጥፎ መሪ ስታይ፣ መጥፎ ባለሥልጣን ስታይ፣ መጥፎ ትውልድ ስታይ፣ መጥፎ ህልም ስታይ፣ መጥፎ ሁኔታ ስታይ … ሌላ ምንም ነገር አትናገርም፡፡ “እስቲ ዱዓ አድርጉ” ትላለች ተጨንቃ ተጠብባ፤ ይኸው ብቻ ነው ጥያቄዋ፡፡
እርጥብ ናት፡፡ ቀልቧ እርጥብ ነው፡፡ እጇ እርጥብ ነው፣ ሐያቷ እርጥብ ነው፣ ንግግሯ እርጥብ ነው፡፡
መከራ ወረደ፣ አሊያም ሊወርድ ነው በተባለ ጊዜ ሁሉ ጊዜ ሳትወስድ ፈጠን ብላ ዱዓ ታደርጋለች፣ ዱዓ ታስደርጋለች፡፡ ለዱዓ የምትሰስተው ነገር የለም፡፡ ለዱዓ ብላ ታርዳለች፣ ለዱዓ ብላ ዳቦ ትደፋለች፣ ለዱዓ ብላ ሶደቃ ታደርጋለች፡፡

   እንደዛሬው ሰው ደረቅ አይደለችም ታለምዬ፡፡ ያለ ትርጉም የምትኖር አይደለችም፡፡ ሁሉን ነገር ታስተዉላለች፤ በጥልቀት አርቃ ታያለች፣ ሁሉን ሚስጢር ለማንበብና ለመፍታት ትጥራለች፣ ለመተንተን ትታገላለች፡፡ ነገሮችን አናንቃ የተለየ ትርጉም ሳትሠጠው የምታልፍ አይደለችም፡፡ በሀሳብም በተግባርም ሁሌም ከአላህ ጋር ናት፡፡ ለአላህ አብዝታ ያደረች ናት፡፡ ሁለመናዋ ከፈጣሪዋ ጋር የተሳሰረ በመሆኑ በሁሉ ነገር ዉስጥ የአላህን ሥራ በጥልቀት ታያለች፡፡ በዉስጠ ልቦናዋ ትመለከታለች፡፡

ጥሩ ነገሮች የተለወጡ እንደሆነ፣ ንፁህ የነበረው አየር ከደፈረሰ፣ ኑሮ ከተወደደ፣ ዝምድና ከተቆረጠ፣ መልካም ሁኔታዎች የተቀያየሩ ጊዜ፣ ክረምቱ ሲደርቅ፣ በጋው ሲዘንብ፣ ብርዱ ሲከፋ፣ ሐሩሩ ሲከብድ፣ ሰላሙ ሲጠፋ፣ ጥላቻው ሲንሠራፋ … የሆነ ነገር እንዳለ  ትጠረጥራለች፤ በጉዳዩ ዉስጥ የሰማዩ ባለቤት እጅ እንዳለበት ታስባለች፡፡ “ አረ ዱዓ አድርጉ!” ብላ ታሳስባለች፡፡
በሰው ልጅ ላይ የሚዘንቡ የምድር ላይ መከራዎች ሁሉ የሰው ልጅ የክፋት ዉጤቶች እንደሆኑ ታምናለች፡፡ “እንደው ምን ታረገን ይሆን ጌትዬዋ!” ትላለች፡፡ ብቻዋን ታወራለች፣ ብቻዋን ትማፀናለች፡፡ “አረ እናንተ ሰዎች ይሄ ነገር ዱዓ ያስፈልገዋል!” ትላለች፡፡ “ዱዓ እናድርግ” ብላ ታስታውሳለች፡፡ ድንገት ብድግ ትላለች፤ ፈጠን ብላ ሸይኾችን አስጠርታ ዱዓ ታደርጋለች፤ አላህን ይፈራሉ ብላ ለምታስባቸው ደጋጎች ሁሉ  ስለ ጉዳዩ ታሳስባለች፡፡

ዱዓ፣ ዱዓ፣ ዱዓ … ነው የሌት ተቀን ዉትወታዋ፡፡ ያለ ዱዓ መኖር፣ ያለ ዱዓ መቆም፣ ያለ ዱዓ መውጣት፣ ያለ ዱዓ መግባት፣ ያለ ዱዓ መተኛት መነሳት ይከብዳታል ለሷ …

ዱዓ ምርኩዟ ነው፣ ዱዓ መደገፊያዋ ነው፣ ዱዓ ወንጭፏ ነው፣ ዱዓ በትሯ ነው፣ ዱዓ ሰይፏ ነው፣ ዱዓ ጦሯ ነው፣ ዱዓ ጋሻዋ ነው፡፡

እታለም የአምላኳ ጥገኛ ናት፡፡ ያለሱ መጠጊያ ምሽግም የላት፡፡ የሁልጊዜዋ ወሬዋ ከሱ ጋር ነው፡፡  ሹክሹክታዋ ወደሱ ነው፡፡ ምላሷ ከዚክር አያርፍም፤ ጣቶቿ ከሙሰቢሐ አይለዩም፡፡ ዕድሜዋ ቢገፋም ሰኞና ሐሙስ ትፆማለች፣ የዱሓና የለይል ሶላት ትሰግዳች፣ የሆነ ልዩ ቀን፣ ልዩ ፆም ካለ አስታውሱኝ ትላለች፡፡

እንዲሁ ዝምብላ ነገሮችን ችላ የምትልና የምትዳፈር አይደለችም ታለም፡፡ ትፈራለች፡፡ አላህን በጣም ትፈራለች፡፡ ድንገት ሁኔታዎች ልዉጥዉጥ ሲሉ ትደነግጣለች፡፡ ከሁሉም ቀድማ ፊቷን ወደ አላህ ታዞራለች፡፡ ዚክር ታበዛለች፡፡ ትመፀዉታለች፡፡ ኢስቲግፋር ታዘወትራለች፡፡ ከዱዓ በላይ ምን አለ! ብላ ትጠይቃለች፡፡


ምንጭ ፡ 'ከአላህ ጋር' መጽሐፍ
በሙሐመድ ሰዒድ

ክፍል ሁለት ይቀጥላል

http://t.me/MuhammedSeidABX
1.5K views09:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-07 06:47:08 ሲትርህን፣
ዉዴታህን፣
ምህረትህን፣
እዝነትህን፣
ጀነትህን

ለመንኩህ ያ ረብ!

ሰባሐል ኸይር

http://t.me/MuhammedSeidABX
1.6K viewsedited  03:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-06 21:22:28

1.3K views18:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-06 19:17:20 አሥር ነገሮች

1-     በምጽፋቸው ነገሮች ብዙ ወዳጆች እንዳተረፍኩ አውቃለሁ፤ ጣቶቼ ብዙ ወዳጆችን አፍርተዉልኛል፡፡ ይወዱኛል እወዳቸዋለሁ፣ ዱዓ ያደርጉልኛል፤ ብናየው ብለው ይናፍቁኛል፤ እኔም እንደዚያው፡፡ ወዳጄ አንተም ከቻልክ ፃፍ፤ ካልቻልክበት ደግሞ ተናገር፤ መልካም በመናገር ዉስጥ ብዙ ትርፍ ነገር አለ፤ በምትወረወረው አንዲት ቃል ቢያንስ አንድ ሰው ሊነቃ፣ የአንድ ሰው ሕይወት ሊስተካከል ይችላል ማን ያውቃል፡፡

2-     ሰዎች ሊያወሩህ እየፈለጉ አትዝጋቸው፣ እየቀረቡህ እየተመኙ አትሽሻቸው፤ አብረዉህ መቀመጥ ሲፈልጉ አትራቃቸው፤ ከኛ ይሻላል ብለው ሲያማክሩህም አትኩራባቸው፣ አሰላሙ ዐለይኩም እያሉ ባላየ አትለፋቸው፡፡

3-     ጌታህ የሠጠህ ዕድሜህ ትልቁ ካፒታልህ ነው፡፡ ይህን ዉድ በጀት በአግባቡ ሥራ ላይ አዉል፣ ስንፍናን ራቅ፣ ረጅም ሰዓት ስልክ አታውራ፣ ብዙ ክፍተት አይኑርህ፤ ሰዓትህን ይበልጥ ጠቃሚ በሆነ ነገር ላይ አዉል፡፡ ጊዜን ማባከን ሙስና ነው፡፡

4-     እንደሮጥክ የዱንያ ፀሐይ አትጥለቅብህ፤ ለቤተሰብህ ጊዜ ይኑርህ፤ ከልጆችህ ጋር ወርደህ ተጫወት፣ መላዉን ቤትህን በዲን አንፅ፣ መሞትህ አይቀርምና ከሞትክ በኋላ ዱዓ የሚያረግልህ መልካም ልጅ ዛሬዉኑ አፍራ፡፡ አላህ ይረዳሃል፡፡

5-     ሚስትህ ጎንህ ናት፤ በሀሳብም በጉልበትም አብራህ ብዙ ደክማለች፣ በሷ ብርታት ቀጥ ብለህ ለመቆም ቻልክ፤ ሀብትህ ናትና ተንከባከባት፤  እንደምትወዳት ንገራት፣ ተመልሰህ ብትፈጠር እንኳን እሷኑ ማግባት እንደምትመኝ አንሾካሹኩላት፡፡

6-     የእይታህን አድማስ አስፋ፣ ከበደል ራቅ፣ ለበደለህ ምክንያት ፈልግለት፣ ላጠፋብህ ጀሊሉ ይዘንለት፡፡ ሥምህን በክፉ ያነሳን የአላህን ይቅርታ ለምንለት፡፡

7-     የሚወራዉን ሁሉ ጆሮ ሠጥተህ አታዳምጥ፤ የሚነፍሰዉን ሁሉ ምክንያቱን ካላወቅኩ አትበል፣ ሰዎች ከበው የሚያዩት ነገር ባዶ፣ የሚቀባበሉት ወሬ ገለባ ሊሆን ይችላል፡፡

8-     ዱንያ እንደው ዐጀብ አላት፡፡ እንዲሁ ምድር ላይ መንቀሳቀስህን አይተው ብቻ የሚጠሉህ አሉ፡፡ ምክንያታቸዉን እነርሱም አያውቁም፡፡ ትልቅ ደረጃ መድረስ ካሰብክ ለምቀኞችህ መልካም ነገር አስብላቸው፡፡

9-     ዱንያ እንደ ቂጣ ናት፡፡ ካልተገላበጡ ታሳርራለች፣ ሐላል እስከሆነ ድረስ ተዝናና፣ ሀሜት እስካልሆነ ድረስ ተጫወት፣  ሕይወትህን በእጅህ አድስ፡፡ 

10-  በአንድዬ ጌታ እምላለሁ እወዳችኋለሁ፡፡
 

http://t.me/MuhammedSeidABX
1.8K views16:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ