Get Mystery Box with random crypto!

ABX

የቴሌግራም ቻናል አርማ muhammedseidabx — ABX A
የቴሌግራም ቻናል አርማ muhammedseidabx — ABX
የሰርጥ አድራሻ: @muhammedseidabx
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 8.70K
የሰርጥ መግለጫ

ወደ ቤታችሁ እንኳን መጣችሁ!!

Ratings & Reviews

2.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 58

2021-03-24 22:07:14 አውቃለሁ

ለረጅም ዘመን 'አልሐምዱ ሊላህ !' እያሉ ከመፈተን በላይ ብርቱ ፈተና የለም።

ቢሆንም ግን

አሁንም 'አልሐምዱ ሊላህ' በሉ።

መልካም ምሽት

http://t.me/MuhammedSeidABX
339 views19:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-03-24 21:26:00 ሰው ....

***,
ከደረሱን ተረቶች መካከል …

ለአህያ እንዲህ ተባለ -
“ያለ ዕረፍት ከጠዋት እስከ ማታ ትሠራለህ ፤ ትላልቅ ሸክሞችን ትሸከማለህ፣ እንደለፋህ ትኖራለህ፣ በዚህም በምድር ላይ የሀምሳ ዓመት ዕድሜ ተሠጥቶሃል፡፡”

አህያም አለ “በርግጥ አህያ ልሁን፤ ነገርግን ሀምሳ ዓመት ብዙ ነው፤ ሀያ ዓመት ይብቃኝ” ፡፡ ለአህያም የጠየቀው ዕድሜ ተሠጠው፡፡

ለዉሻም እንዲህ ተባለ፡፡
“ ሥራህ የሰዉን ልጅ ቤት መጠበቅ ይሆናል፤ ከሰዎች አትርቅም፣ ከትራፊዉና ከሚጣልልህ ትበላለህ፣ የምድር ላይ ሕይወትህ ይህ ይሆናል፡፡  የሰላሳ ዓመት ዕድሜም ይሠጥሃል፡፡”
ዉሻም “ምድር ላይ የሰላሳ ዓመት ዕድሜ ብዙ ነው፣ አሥራ አምስት ይበቃኛል፡፡” አለ፡፡ የጠየቀው ተሠጠው፡፡

ለዝንጀሮም እንዲህ ተባለ “ከቅርንጫፍ ወደ ቅርንጫፍ እየዘለልክ ሕይወትን ትኖራለህ፣ ሰዎችም አንተን በማየትና ካንተ ጋር በመጫወት ይዝናናሉ፣ በዚህም የሀያ ዓመት ዕድሜ ይሰጥሃል፡፡”

ዝንጀሮም አለ “ ሀያ ዓመት እንኳን ይበዛብኛል፤ አሥር ይሁንልኝ፡፡” አለ፡፡ ያለው ተደረገለት፡፡

ለሰዉም ተባለ - አንተ ከፍጥረታት ሁሉ ብልሁ ነህ፤ በሌሎች ፍጥረታት ላይ አለቃ ትደረጋለህ፤ ምድርን ታንፃለህ፣ ወኪልም ትደረጋለህ፤ ለዚህም በምድር ቆይታህ ሀያ ዓመት ዉሰድ፡፡”

ሰዉም አለ፡፡ “እንደሰው ሀያ ዓመት ያንሰኛል፤ ባይሆን ሌሎች ያልተቀበሉትና የመለሱት ዕድሜ ይሠጠኝ” አለ፡፡
በዚህም አህያ የመለሰው ሰላሳ ዓመት፣ ዉሻ የመለሰው አሥራ አምስት ዓመት፣ ዝንጀሮ የመለሰው አሥር ዓመት ተሠጠዉና  ሰባ አምስት ዓመት ሆነለት፡፡

በዚህም የተነሳ የሰው ልጅ እስኪያገባ ድረስ የመጀመርያዉን ሀያ ዓመቱን እንደራሱ ዕድሜ እንደሰው ይኖራል አሉ፤ ቀጥሎ ያለዉን ሰላሳ ዓመት እንደ አህያ ይሠራል፣ ያለዕረፍት ይለፋል፣ ይደክማል፡፡
ከዚያ ዕድሜው ከፍ ሲልና ሃምሳ ብዙ ጊዜውን እንደ ዉሻ እቤቱ ያሳልፋል፣ ጓሮ ያዘወትራል፣ ግቢዉን ይጠብቃል፣ መብራት ዉሃ ይቆጣጠራል፡፡ የቀረዉን አሥር ዓመት ደግሞ ከልጆቹ ወደ ልጆቹ እንዲሁም ወደ ልጅ ልጆቹ ቤት እየተዘዋወረ ይኖራል፡፡ ህፃናትና በድዱ ይስቃሉ፣ ወጣቶች በወጉ ይጫወታሉ፡፡

ሰው ማለት ይኸው ነው፡፡

http://t.me/MuhammedSeidABX
447 views18:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-03-22 16:47:36 አንድ ሰው ለደጉ ሰው ለኡወይስ አል-ቀርኒ "እስቲ በየጊዜው ዘይረንና ወዳጅነታችን የበለጠ ይጠናከር።" ብሎ ጠየቀው። የደጋጎችን ዚያራ የማይመኝ ማን አለ!

ኡወይስም "ከዚያራው በበለጠ በሩቅ በማደርግልህ ዱዓ ወዳጅነታችንን እያጠናከርኩ ነው። መዘያየርና መገናኘት ሁሌ አይሳኩም፣ ይቆራረረጣሉ። ዱዓ ግን ምንዳው ሁሌም ቀጣይ ነው።" አሉት።
በሌሉበት ለሌላው ዱዓ አድራጊ ሁሌም ዘያሪ ነው።
በዱዓ።

http://t.me/MuhammedSeidABX
866 views13:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-03-21 10:56:30 የሚበልጠዉን ይዘናል (2)
በሙሐመድ ሰዒድ (ABX)
*** ,,,,,,******

አልሐምዱ ሊላህ ትልቅ ዕውቀትንም ታድለናል፡፡ ወደ መንገዱ ለመራን ጌታ ምስጋና ይገባው፡፡ አላህን አውቆ ከመገዛት በላይ ምን ዕውቀት አለ!፡፡ ከርታታ ነፍሳችን እርካታ የምታገኝበትን ነገር ማወቅ ግዙፍ ዕውቀት ነው፡፡ ሰው ሁሉን ነገር ቢያተርፍና ነፍሱን ግን ብትጎድል ምን ይጠቀማል!፡፡ ምንም፡፡ ወላሂ ምንም፡፡ 

ምናልባት ከምድር ሀብት የምንመኘውን ያህል ባናፍስም ወደ ሰማይ ቤት የሚወስደዉን መንገድ ይዘናል፡፡ አላህ በመንገዱ ላይ ያኑረን፡፡ ፅናቱንም ይለግሰን፡፡

ከዱንያ ጅረቶች ሁሉ ባንጠጣም ምንጩ ላይ ተደላድለናል፡፡ እናም ልንደሰት ይገባል፡፡ አልሐምዱ ሊላህ።

የሚበልጠውን ይዘናል፡፡
እናስተውል -  ከብዙዎች የሚበልጥ ብዙ ነገር አለን፡፡ አላህ ዘንድ እውቅና ያለው ብቸኛ ሃይማኖት ኢስላም ነው፡፡ የዛሬም ሆነ የነገ ስኬት የሚገኘው በዚሁ እምነት ነው፡፡ የሚበልጠዉን ይዘናል፡፡ አምላካችን ከጠማሞችም ሆነ ከተቆጣባቸው ማኅበረሰቦች መካከል አላደረገንም፡፡ በርሱ ከሚያጋሩትም አላደረገንም፡፡ ከአጓጉል ፈላስፋዎችና አዋቂ ነን ባዮችም አላደረገንም፡፡ 
'እስቲ ፀጋዎቻችሁን ከፍ አድርጋችሁ አሳዩ' ቢባል ብዙ ነገር አለን፡፡ አዛኙ አምላክ ጌታችን ነው፡፡ መካ ላይ ስለተወለዱት የሰው ጨረቃ ነቢያችን ናቸው፡፡ ዓለምን ያበራው የእስልምና ፀሐይ የኛው ሀብት ነው፡፡

ለካስ ተሞኝተናል፡፡ ጤናን የመሰለ ምርጥ ልብስ ለብሰን የሰው ቡትቶ ያምረናል፡፡ አላወቅንም እንጂ ትላልቆቹን ሀብቶች ወርሰናል፡፡  ለካስ የሚበልጠውን ይዘናል!!!

የዉሸት ኃይማኖቶች በየአካባቢው እንደ አሸን ፈልተዋል፡፡ በአስተምህሯቸውና በእምነት መርሃቸው ለአዕምሮ ለመቀበል የሚቸግሩ ዉስብስብና አስገራሚ ይዘት ያላቸው ናቸው፡፡ በብዙ አጋጣሚዎች ላይ ብዙዎች የሚፎክሩበትን አየሁ፡፡ የሚኩራሩበትን ነገር አስተዋልኩ፡፡ ከፈጣሪ ርቀው በፍጡራን ሲመኩ ተመለከትኩ፡፡ ምንም ሳይኖራቸው ብዙ እንዳላቸው ሲመፃደቁ ታዘብኩ፡፡  ‹በእገሌ ደስ ይበላችሁ!› ሲሉም በገዛ ጆሮዬ ሰምቼ ደነገጥኩ፡፡ …

አዎን … የሚበልጠውን ይዘናል፤ ቁርኣናችን ሁሉን መፅሐፎች የሻረ ታላቅ እውነት፣ የላቀ መለኮታዊ ራዕይ ነው፤ ነቢያችን የነቢያት ሁሉ ዓይነታ ናቸው፤ እስልምናችን በአላህ ዘንድ ተቀባይነት ያለው ሃይማኖት ነው፤ እኛም ሙስሊሞች ደግሞ በላጭ ሕዝቦች ነን፡፡ የሚበልጠው ሁሉ በኛ እጅ አለ፡፡ በርግጥም አላህ አድሎናል፡፡ እናም ዘወትር ደስ ይበለን …
የ……ሚ……በ…….ል……ጠ……ው…..ን … ይ……ዘ…..ና…..ል፡፡
 


http://t.me/MuhammedSeidABX
567 views07:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-03-19 18:46:18 የሚበልጠዉን ይዘናል … (1)
“አትጨነቁ” ከተሠኘው መጽሐፌ
ሙሐመድ ሰዒድ(ABX)

*,,,***,,,,,****

በዚህች ዱንያ ላይ በኖርኩበት ዕድሜዬ ከሰው ልጅ አንፃር ብዙ ነገሮች ሲለዋወጡ አይቻለሁ፡፡ አስደንጋጭ ነገሮችን ተመልክቻለሁ፡፡ ለ15 ዓመታት ያህል ከአልጋው ያልወረደን በሽተኛ አይቻለሁ፤ ዉብ ዐይኖች የነበራት ኮረዳ በቀኑ በብርሃኑ ብዥ ብሎበት በዚያው ሁለት ዐይኖቿ ጠፍተው አጋጥሞኛል፤ በበሽታ ምክንያት ፀጉሯ ረግፎ የተለወጠችዋንም እንዲሁ፤  ለጥቂት ዓመታት የተለየሁትን ጓደኛዬን አንደበቱ ታስሮ አግኝቼዋለሁ፡፡ ሰውነቱ ሙሉ በሙሉ ተሳስሮ ቤት ዉስጥ የቀረውንም እንዲሁ፡፡ ….

እነኚህ ሁሉ የአላህ ተዓምራት ናቸው፡፡ ዱንያ ትርዒቷ ማብቂያ የለውም፡፡ ጌታዬ አላህም እንደሻው ያረጋታል፡፡

ዱንያ ምንጊዜም ዱንያ ናት፡፡ ሰዉም ምንጊዜም ሰው ነው፡፡ ሕይወት በገጠመኝ የተሞላች ናት፡፡ አንዳንዴ ከልክ በላይ ደስተኛ እንሆናለን፤ አንዳንድ ጊዜ ደግሞ ምርር ብለን ራሳችንን እንጠላለን፡፡
ወንድም እህቴ ሆይ! ሁሉም ጫፍ የወጡ የዱንያ ስሜቶች ልጓምን ይፈልጋሉ፡፡ ሰከን ማለትና ተረጋግቶ ማሰብን ይሻሉ፣ ነገር ማሳደርን ግድ ይላሉ፡፡ በትኩስ መወሰን፣ በነሻጣ ቃል መግባት፣ በሐዘን ተስፋ መቁረጥ ለቁጭት ይዳርጋል፡፡
ነገር ሲያድር ይበስላል፤ የደፈረሰ ዉሃም ሲሰክን ይጠራል፡፡ በአንዲት ቅጽበት ስንደሠት ደስታው በርግጥም እውነተኛ ደስታ ስለመሆኑ መጣራት አለበት፡፡ ሐዘኑም ተጋኖ እንዳልሆነ መገምገም ይኖርበታል፡፡ ካልሆነ በጥድፊያ የሚወሰኑ ዉሳኔዎች ጉዳታቸው ያመዝናል፡፡ አደጋቸውም ይበዛል፡፡ ተረጋጉ፡፡

እና …
 ከብዙ ማማረር በኋላ ዙሪያዬን ተመለከትኩ፡፡ ቆም ብዬና ጊዜ ሠጥቼ ዙሪያዬን ቃኘሁ፡፡ በዚህ የሩጫ ዘመን ጊዜ ወስደን ጥቂት ካልቆምን በስተቀር ልናያቸው የሚገቡ ብዙ ነገሮች ያመልጡናል፡፡ ያልተነካ ግልግል ያውቃል ብላችሁ በምሬታችሁ ከመቀጠላችሁ በፊት እስቲ ላንዳፍታ ቆም በሉ፡፡ ካልቆምን በስተቀር ብዙ የማይታዩን ነገሮች ይኖራሉና እስቲ ጥቂት እንቁም፡፡ እናም ቆሜ አስተዋልኩ …

  በብዙ የአላህ ፀጋዎች ተከብብያለሁ፡፡ ትልቁ እምነት ነው - እስልምና ፡፡ ኢስላምን ለሠጠኝ ጌታ እኔ ምን ልሠጠው እችላለሁ!፡፡

 ብዙ ነገርም ተሰጥቻለሁ፡፡ ከዋናዎቹ ብንቆጥር አንዱ ጤና ነው፡፡ አንዳንዴ ቆንጠጥ ቢያረገኝ ወደራሱ ሊመልሰኝ፣ እጄን ለዱዓ እንዳነሳ ቢያግዘኝ እንጂ ምን አደረገኝ፡፡ ጌታዬ ሆይ አንተ እንደፈለግክ አድርገኝ፡፡ እንኳን እኔ ታላቁ ነቢይ (ሰ.ዐ.ወ.) “ቁጣህ አይሁን እንጂ ምንም ብታረገኝ ግድ የለኝም፡፡” ይላሉ፡፡

ብዙ ንብረትም አለኝ፡፡ ትልቁ አዕምሮ ነው፡፡ አዕምሮን የተሠጠ ሰው ብዙ ነገር ተሠጠ፡፡ ሰው አዕምሮ ከሌለው ምድር ላይ የመገኘቱ ነገር ምንም ትርጉም የለውም፡፡

እናም አየሁ አየሁና እንዲህ አልኩ … አስተባበልን፣ ካድን እንጂ ብዙ ነገር ተሠጥተናል አልኩኝ፡፡ አላስተዋልንም እንጂ የሚበልጠውን ይዘናል፡፡
እንደኔ እንደኔ ሁሉ ነገር አለን፡፡ ቀረን የምንለው ነገር ቢኖርም የሚበዛው በእጃችን አለ፡፡ ትናንሽና ቅርንጫፍ ነገሮችን ሁሉ ባንታደልም ትልቁን ግንዱንና ዋናውን አትርፈናል፡፡ ትልቁ ነገር ዲናችን ነው፣ መሠረታዊው ጉዳይ የቆምንበት እምነት ነው፡፡ በፀና መሠረት ላይ የቆመ ሰው አይወድቅም፡፡ ዋናው ሀብት ዛሬ በሕይወት እያለን፤ ነገም ከሞት በኋላ ሊጠቅመን የሚችል ነገር ነው፡፡ እናም ወሳኙን ነገር ይዘናል፡፡ በላጩን ሀብት ጨብጠናል፡፡ ….

ይቀጥላል


http://t.me/MuhammedSeidABX
510 views15:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-03-19 17:46:10 ጥቂቶቹ እነሆ፡-

የጀነት ጉጉት

1.     አሕመድ ቢን ሐርብ ፤ አላህ ይዘንለት
“አንዳንዶቻችን፣ ከፀሐይ ሐሩር (ሽሽት) በጥላ እንከለላለን፤ ምነዋ ታድያ ከእሳት (ረመጥ ለመዳን) በጀነት የማንጠለል?!” ሲል ይጠይቃል ።

2.     ኡሙል በኒን -የዑመር ኢብን ዐብዱልዐዚዝ እህት (ረ.ዐ) 
“ከንፉግ ሁሉ ንፉግ፣ ጀነትን ለራሱ የሚነፍግ ነው።” ብላለች።

3.     የሕያ ኢብን ሙዓዝ ፤ አላህ ይዘንለት
“ስለ ነፍሴ ሕልፈት የማለቅስ አይደለሁም፤ ይልቁንም የኔ ማንባት፣ መሻቴ አይሰምር (ጉዳዬ አይሞላ) እንደሁ ከመፍራት ነው!” ብሏል።

4.     ዑመር ኢብን ዐብዱልዐዚዝ (ረ.ዐ) 
“ረጃእ ሆይ (ስማኝ)! እጅግ ገጉ የሆነች ነፍስ አለችኝ፤ (እና ይህች ነፍሴ) ፋጢመት ቢንት ዐብዱልመሊክን ተመኘች፤ አገባኋትም። ወደ ሹመትም አማተረች፤ ተሾምሁላትም። ኸሊፋነትንም ከጀለች፤ አገኘኋትም። አሁን ደግሞ ጀነትን ናፍቃለች፣ የኃያሉና የተከበረው አላህ ፍቃድ ከሆነ እንደምቀዳጃት ተስፋ አደርጋለሁ!” ብለዋል።

 
5.     ዐጧእ ኢብን መይሰራ (ረ.ዐ) 
“በምድራዊ ሕይወታችሁ ጉዳይ አልመክራችሁም፤ እናንተ በርሷ የተካናችሁና የተሰጣችሁ ናችሁና። አደራ የምላችሁስ በአኺራችሁ ጉዳይ ነው። በዚህች ጠፊ አላፊ ሀገር ሳላችሁ፥ ለዘላቂይቱ ዓለም ትጉ!” 

6.    ኢማም  ኢብኑል ቀይም ረሒመሁላህ
“ፀጋ በምቾት) አይገኝም። ለ ጊዜያዊ ደስታ የሚሸነገልን ዘላለማዊ ደስታ ትሸሸዋለች። ብርታት የሌለው ሰው ሐሴትም የለውም፤ ትዕግስትን ያላደለው እርካታ አይኖረውም፤ መከራ የሌለው ተድላን አይቸርም፤ ፈተናን ያልታደለ እፎይታ የለውም። የአላህ ባርያስ ማለት በጊዜያዊ መከራ (ውስጥ አልፎ) ዘላቂ ሐሴትን የሚጎናፀፍ ነው!”

7.     የሕያ ኢብን ሙዓዝ (ረ.ዐ) 
“ዱንያን መዘንጋት አዳጋች ቢሆንም፣ ጀነትን ማጣት ግን ከባድ ሐዘን ነው። እናም፣ ምድራዊ ሕይወትህን ለነገይቱ ዓለም ጥሎሽ አድርጋት!”

ምንጭ ፦ አንዲት ዕለት በጀነት
ማሕሙድ አልሚስሪ
ትርጉም ፦ ዒማዱዲን ዙልፊቃር

https://t.me/NejashiPP
510 views14:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-03-18 19:51:12 አንድ ዕድል ልሞክር ብለው መጨረሻ ላይ የመጡት /የደወሉት ወደኛ ሊሆን ይችላልና ሰዎች ሲተነፍሱብን አንሰላች ወዳጆቼ።

http://t.me/MuhammedSeidABX
827 views16:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-03-18 19:40:42 የቴሌግራም ወዳጆቼ
በፌቡ በላካችሁልኝ የዉስጥ መልዕክት አማካይነት ከማስበው በላይ እንደምትከታተሉኝ ተገነዘብኩ። አልሐምዱ ሊላህ ለካ ብዙ ወዳጆች አሉኝ።

ሰዉም አደለሁ?
ትንሽ ድካሙም፣ ገፍላዉም፣ ቢዚነቱም ስላለ ነው የጠፋሁት ወዳጆቼ
ቢኢዝኒላህ አለሁ።

ጀሊሉ እስከለተሞታችን የምናገለግለው ያድርገን።

http://t.me/MuhammedSeidABX
854 viewsedited  16:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-03-15 13:15:17 አምኜው ከዳኝ ብለህ ስታለቅስ አትኑር ...

ነፍስህ ጭምር አንድ ቀን ጥላህ ጥርግ ትላለች። ጀሰድህ ብቻዉን ቀፎ ሆኖ ይቀራል።

http://t.me/MuhammedSeidABX
1.0K views10:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-03-15 06:37:56 ማለዳ ዐይኑን ከከፈተበት ጊዜ ጀምሮ ምሽት ዐይኑን እስከሚዘጋበት ጊዜ ድረስ ቀኑን ሙሉ የሰዉን ነዉር ሲከታተልና ሲያነፈንፍ የሚዉል ሰው አለ፡፡

ምንም ላያተርፍበት ራሱን ትቶ ሌላዉን ይከታተላል፣ ዉድቀቱን፣ ድልጠቱን፣ ስህተቱን፣ እንከኑን ይሰልላል፡፡ ዉርደቱን ይጠብቃል፡፡ የት ዋለ፣ የት ሄደ፣ የት ገባ፣ የት ወጣ፣ ምን አገኘ፣ ምን አጣ … እያለ ስለ ሰው ይጠበባል፡፡ የራሱን ትቶ የሌላዉን ሕይወት ይኖራል፡፡ የራሱ አሮበት የሰዉን ያማስላል፡፡

“የራሱ ነዉር የሰዉን ነዉር እንዳያይ ያደረገው ሰው ምንኛ ታደለ፡፡” ይላሉ የአላህ  መልዕክተኛ (ሰ.ዐ.ወ.)

ባይሆን ወደራሱ የተመለከተ፣ በራሱ ጉዳይ ተጠምዶ የዋለ በራሱ ላይ ብዙ ጉድፍ ያያል፡፡
ሰባሐል ኸይር!
http://t.me/MuhammedSeidABX
1.3K views03:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ