Get Mystery Box with random crypto!

ABX

የቴሌግራም ቻናል አርማ muhammedseidabx — ABX A
የቴሌግራም ቻናል አርማ muhammedseidabx — ABX
የሰርጥ አድራሻ: @muhammedseidabx
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 8.70K
የሰርጥ መግለጫ

ወደ ቤታችሁ እንኳን መጣችሁ!!

Ratings & Reviews

2.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 57

2021-03-31 14:31:10 የቂን አሎት?

የቂን ማለት ዙርያህ ሁሉ በተስፋ አስቆራጭና ድቅድቅ ጨለማ የተሞላ ቢሆንም አላህ ያሰብኩትን ሁሉ ያሳካልኛል ብሎ ማሰብ ነው።


http://t.me/MuhammedSeidABX
673 views11:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-03-31 13:11:12 ቀናት እኮ አንዴ ከሄዱ አይመለሱም። ምንም ይሁን መልካም ይሁን ነገር ሥሩባቸው።

http://t.me/MuhammedSeidABX
740 views10:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-03-30 10:00:09 እኔን ለሚያውቅ፣ ስለኔ ለሰማ፣ በአካል ላገኘኝም ላላገኝም ሁሉ መልዕክት አለኝ።

ለአላህ ብዬ እወዳችኋለሁ ። አላህ ምስክሬ ነው።


https://t.me/MuhammedSeidABX
1.2K viewsedited  07:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-03-29 18:05:57 የሰርጓ ለታ (4)
*
“የሰርጓ ለታን ትረካ ምነው ጨርስልን እንጂ!” አሉኝ አንዳንዶች በዉስጥ መጥተው፡፡

ብዙ ሰዎች ትረካዎች የገሃዱ ዓለም  ተጨባጭ አይመስላቸዉም፡፡ የሌላ ዓለም ሕይወት ይመስላቸዋል፡፡ ለዚህም ነው አጨራረሱን ለማየት ይናፍቃሉ፤ ያቺን ምስኪን ልጅ የት አደረሳት ብለው ይጠይቃሉ ፤ ዱንያ እኮ በሚስኪኖች የተሞላች ናት። እርግጥ ነው ለሰዎች ብለን የምናበጀው የተለየ አጨራረስ የለም፡፡ የምንተርክላቸው ሰዎች በኛው መሃል ናቸዉና የእነርሱን ሕይወት በማየት ብቻ ሌላዉም ትረካዉን ማስቀጠል ይችላል፡፡

“የሰርጓ ለታ” ትረካ በሰርጉ ዕለት ምሽት በረከቱ ለሆነችው ለሚስቱ ከማዘን ይልቅ ኃይልና ጉልበትና ተጠቅሞ  የአንዲትን ልጃገረድ ሥነልቦና ክፉኛ ስለጎዳው አንድ “አውሬ” ወጣት ነው የሚያወጋው፡፡ አላህ ሐላል ያደረገለትን የወሲብ ስሜት በፍቅር፣ በቀስታና በእንክብካቤ ከመወጣት ይልቅ ስሜቱ ጋልቦት እና እልህ አሸንፎት ከአዕምሮው ይልቅ ጡንቻዉንን በመጠቀሙ ምክንያት የአንዲትን እህት ሕይወት አበላሸ፡፡
ትረካው የአንድ እና ሁለት ሴቶች ታሪክ ብቻ ነው ብዬ አላምንም፡፡ ለዚህም ነው ለጀማዓው ያቀረብኩት ።

ዱንያ እንዲህ ናት እንግዲህ ወዳጆቼ፤ በአንዲት ቅጽበትና አጋጣሚ ነገሮች ይለዋወጣሉ፤ ሁኔታዎችም ይቀያየራሉ፤
ለአንዳንዱ የሰርጉ ዕለት የረጀም ደስታው መነሻ ሊሆን ይችላል፤ ለአንዳንዱ ደግሞ ከሰርጉ የሚተርፈው ነገር ቢኖር ትዝታ፣ ሐዘንና መጥፎ ጠባሳ ብቻ ይሆናል፡፡

ያች ልጅ እስከዚያች ቀንና ሰዓት ድረስ በሕይወቷ ደስተኛ ነበረች፤ ፍልቅልቅ ሳቂታም ነበረች፡፡ በያን ቀን ባጋጠማት ችግር ምክንያት የረጅም ጊዜ ደስታዋ ራቃት፤ ፈገግታዋም ሸሻት፣ ሕይወት አስጠላት፣ መኖርም ቀፈፋት፡፡
ዛሬ ላይ ወንድ ልጅ በተጠጋት ቁጥር ትፈራለች፣ ትሸክካለች፣ ትንቀጠቀጣለች፣ ነፃ ሆና ለማውራት ትቸገራለች፡፡ በዚህም የተነሳ ብዙዎችን ግራ አጋብታለች፣ እሷም ብትሆን በርካቶች እያገለሏትና እየራቋት እንደመጡ ታዝባለች፡፡  ሁኔታዋን ለማስተካከል ዉስጧ ቢፈልግም፤ የተቻላትን ያህል ከራሷ ጋር ታግላ ብትሞክርም ይህን ችግሯን መቅረፍ ግን አልቻለችም፡፡ 

በዚሁ ዙርያ የሚከተሉትን በመምከር መቋጫ እናበጃለን፡-

1-      የሰርግ ዕለት በወጣት ተጋቢዎች ሕይወት ዉስጥ ወሳኙ ዕለት ነው፤ ተጣማሪዎች አንደኛው ከሌላኛው ኸይር ይጠቀሙ ዘንድ ሁለት ረከዓ ሰግደው ዱዓ ማድረግ ይኖርባቸዋል፤ የሙሽሮች ዱዓ ተቀባይነት አለው ተብሏል፡፡

2-     ሁሌም ቢሆን ስሜት ከየትኛዉም ዓላማ በላይ እንዳይነግስ ጥንቃቄ ያስፈልጋል፤ ወጣትነት እሣት ነው፤ በተለይ በዚያች ቅጽበት ራስን መቆጣጠርና መግራት ግድ ይላል፡፡

3-     “አንዳችሁ እንደ እንሠሣ ሚስቱን አይገናኝ …” ይላሉ ነቢያችን ( ሰ.ዐ.ወ.)። ከሚስት ጋር በሚደረገው እዝነት፣ ልስላሴ፣ ቀስታ፣ መግባባት፣ መናበብ መቅደም ይኖርበታል፡፡

4-     “ለተሰባሪዎች እዘኑላቸው …” ይላሉ የአላህ ነቢይ (ሰ.ዐ.ወ.)፡፡ ወንድ ልጅ በአልጋ ጨዋታ ራሱን ብቻ ማዳመጥ የለበትም፤ በአካልም ሆነ በሥነልቦና በሙሽሪት ላይ ጉዳት ከማድረስ ሊጠነቀቅ ይገባል፡፡

5-     “ሴቶች የወንዶች እህቶች ናቸው፡፡” ብለዋል የአላህ ነቢይ (ሰ.ዐ.ወ.) ፡፡ እህትህን በምትይዘው መልኩ ሚስትህን ያዝ፡፡ ሴት ልጅ እዝነት፣ ልስላሴ፣ ፍቅር፣ እንክብካቤ፣ ክብር ያስፈልጋታል፡፡

እህት ሆይ!

6-      ከጉዳት በኋላ መጠንከርና ወደፊት ማየት ብቻ ነው የሚያዋጣው፤ የፈሰሰ ዉሃ አይታፈስም፤ ያለፈዉን የጉዳት ሕይወትሽና ታሪክሽና ዝጊበት፣ ለትምህርት ካልሆነ አታንሺው፤

7-     ያለሽበትን ሁኔታሽን ለማስተካከልም አትፍሪ፤ አትፈሪ፣ አትሳቀቂ፡፡  መፍራትም ሆነ ማፈር ነገሮችን ሊያስተካክሉ አይችሉም፡፡

8-     ከጉዳትሽ ለማገገም መልካም የዲን እህቶችንና ወንድሞችን አማክሪ፡፡ ከነርሱም ጋር ዋዪ ተመካከሪ፡፡

9-     በሥነልቦና ባለሙያ ታዪ፤ ምክሮችንም ተቀበዪ፡፡ በሽታዉን ያልተናገረ መድኃኒት አይገኝለትም፡፡

10-    ተስፋ የለኝም አትበይ፤ ራስሽንም አታግልይ፤ ተስፋ የሌላቸው የሞቱ ብቻ ነው፡፡

11-     አላህ አሁንም ሰው ጥሩ ሰዎች ሞልተዉታል፤ በእውነት አፍቅሮ የቀረበሽ፤ በሥነምግባሩ ጥሩ እና ታማኝ የሆነ ሰው ለጥምረት ከጠየቀሽ ችግርሽን በግልጽ ንገሪው፤ ተወያዩበት፡፡ ኢንሻአላህ በትዕግስትና በእምነት አብራችሁ ትፈቱት ይሆናል፡፡

12-    በራስ መተማመንሽን አዳብሪ፤ ኢንሻአላህ ሁሉም መልካም ይሆናል በይ፡፡
13-    ዱዓ፣ ሶደቃ እና መልካም ሥራ የማይፈቱች ችግር ምን አለ!!…

ጌታዬ የተጎዱትን ሁሉ ይጠግን፣ የታመሙትን ይዳብስ።
እሱ በሁሉ ነገር ላይ ቻይ ነዉና።

ሰላማችሁ ይብዛ፡፡
 
መልካም ምሽት


http://t.me/MuhammedSeidABX
1.4K views15:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-03-28 06:17:44 የሰርጓ ለታ (3)
**********

የተወለደው ልጇን ሥሙን ሷቢር አለችው፡፡ ከብዙ ትዕግስትና ፈታኝ ፅናት በኋላ ነበር የተወለደው፡፡ አንዳንድ ሀሳቦች አልፎ አልፎ ከሚረብሷት በስተቀር ከሰዉዬው ቤት ከወጣችበት ጊዜ ጀምሮ ሰላም አገኘች፡፡ አይታ እንዳላየች፣ ተጎድታ እንዳልተጎዳች ሆና ለመኖር ታገለች፡፡ በአራስነት ጊዜዋ ከወላጆቿ ጥሩ እንክብካቤ አገኘች፡፡

 ቀናት ሄዱ፣ በአንድ ቀን  በሰርጓ ዕለት በተፈጠረ ግብግብ ካገኘችው ልጇ ጋር አርባ ቀናትን ተኝታ አሳለፈች፡፡ የልጇም ሆነ የሷ ጤና ጥሩ ነው፡፡ የልጇ ነገር ግርም ይላታል፡፡ ዕድሉ ነው እንግዲህ፤ ጀሊሉ ቀድሞዉኑ ተፈጠሪ ያላት ነፍስ ማንም ምንም ሊያስቀራት አይችልም ለካ! ትላለች፡፡

የአራስ ቤት ጊዜ አለፈ፣ በሂደት ልጇም ጠነከረ፣ እሷም ተነሳች፣ በአካልም በመንፈስም በደንብ ለመቆም ሞከረች፣ ሥራም ጀመረች፡፡
አቤት የሴት ልጅ ፈተናዋ!፡፡

የተወለደው ልጅ እንዳያድግ የለ በዋናነት በአያቶቹ ቤት አደገ፤ ሦስት እና አራት ዓመትም ሆነው፡፡ ያኔ ሰዉነቷ ሳይጠነክር ገና በ16 ዓመቷ ነበር ያገባችው፡፡ በልጅነት ዕድሜዋ ልጅ ታቀፈች፣ ወልዳ ተነስታም ቢሆን ገና አንድ ፍሬ ልጅ ትመሰላለች፡፡ እንደገና ቆነጀች፣ እንደገና ተመለሰች፣ እንደ አዲስ በራች፣ በሥራ ቦታና በየአጋጣሚው ሁሉ ዐይን ዉስጥ ገባች፣ በተመልካቾች ታየች፣ ፈላጊዎቿም ተከታትለው መጡ፣ ለትዳር ጠየቂዎቿ በረከቱ፡፡

ግና በተጠየቀች ቁጥር በረገገች፣ ደነበረች፣ ባነነች፡፡ የሰርጓ ለት ጉዳቷ ዛሬም ድረስ እየታወሳት ይረብሻታል፤ ለብሳ ቢያምርባትም ዉስጧ አልተደራጀም፣ ህመሟ አልሻረላትም፣ ቁስሏ አልደረቀም፣ ጠባሳዋ አልጠፋም፣ ሰዉነቷ አልተዘጋጀም፣ መንፈሷ አልጠገገም፡፡ በሷም ይሁን በቤተሰብ በኩል አድርገው የሚመጡ ጥያቄዎች ከቀን ወደ ቀን በዙ፡፡

ሀያ ዓመቷ ላይ ያለች ትኩስ አፍላ ወጣት ናት፡፡ ግና በወንድ ምክንያት ወንድ የሚባል ፍጡር ሁሉ አስጠላት፣ ሁሉም አንድ መሰሏት፣ ስሜታቸዉን ብቻ ተከትለው የሚንጉዱ ጨካኝ አረመኔዎች ። አታምናቸዉም፣ በሙሉ ልብም አትቀርባቸዉም፣ ከአንድና ሁለት ቃላት በላይ አታወራቸዉም፡፡

አብዛኛው ሕይወቷ ብቸኝነት ነው፣ ሥራ እና ቤት፣ ክፍሏና ሳሎን፡፡ ብዙ ወሬዋ ከጌታዋ ጋር ነው፡፡  ሶላት፣ ዱዓና ፆሟ ላይ ብርቱ ናት፡፡ ብርቱ! በዚህ ፈታኝ ዓለም ብርቱነቷ እስከመቼ ይቀጥል ይሆን!

ጠያቂዎቿ እንቢተኝነቷን ሲያዩ ይገረማሉ፤ ሚስጢሯን ስለማያውቁ ግራ ይጋባሉ፡፡ ጎረቤት የመለሰቻቸዉን ወንዶች ይቆጥራል፣ ዘመድ ኃይለኝነቷን ያወራል፣ ባዳ ሴት መሆኗን ይጠራጠራል፡፡
ቆንጆ ናት፣ ወጣት ናት፣ ምንድነው ወንድ እንዲህ የሚያሸሻት ይላሉ ብዙዎች፡፡ በርሷ ሲደክማቸው በወንድሞቿና በጓደኞቿ በኩል ያስጠይቃሉ፣ መልሷ ቁጣ ነው፤ ንግግሯ ኩርፊያ ነው፣ ሁኔታዋ ሽሽት ነው፡፡ ረጋ ብላ ሻል ያለ መልስ ሠጠች ከተባለ ላስብብት ነው፤ ከዚያ ፈቃደኛ አይደለሁም፣ ዝግጁ አይደለሁም፣ ተወኝ፣ ልቅርብህ፣ … እና የመሣሠሉት፡፡

ቀናት ሄዱ፤ በቀናት መካከል አንዳንድ ጊዜ ቆም ብላ ታስባለች፤ የወደፊት ሕይወቷን አሻግራ ትመለከታለች፣ እስከመቼ ድረስ እንዲህ ልኖር ነው ግን? ትላለች፤ ግራ ይገባታል፡፡ ትጠይቃለች????? ዕድሜ ልኳን ወይንስ!! ....ስታስበው በመሃል ትባንናለች፤ ትደነግጣለች፣ ትሸበራለች፡፡

 አንዳንዴ ደግሞ መጥፎ ነገር ያሳስባታል፤ ያንን ሰዉዬ መበቀል ታስባለች፣ ያቺን ቀን፣ እጇን ይዘው የሠጧትን ወላጆቿን ሁሉ ትረግማለች፡፡ ዕድሏ እንዳበላሹ፣ ሕይወቷን እንዳሰናከሉ፣ ጉዞዋን እንዳደናቀፉ፣ ወጣትነቷን እንደቀጩ ይሰማታል፡፡

ባስ ሲልም ከፍተኛ ስጋት ያድርባታል፣ ፍርሃት ይወራታል፣ በቃ ካሁን ወድያ ወጣትነቷን ላታይ ነው፤ በዕድሜዋ ላትዝናና ነው፣ ፍቅርን ላታጣጥም ነው፣ ቤተሰብ ላትመሠርት ነው፣ ይህ ሁሉ ይመጣባትና ትጨነቃለች፡፡ ግራ ተጋባለች፣ ክንፏን እንደተመታች ወፍ ተስፋ ትቆርጣለች፡፡

 ልጇ መጽናኛዋ ነው፣ የኑሮ ትርጉሟ ነው፣ ተስፋዋ ነው፣ ጉልበቷ ነው፣ ማታ እሱን ታቅፋ ታድራለች፣ ቀን እሱ ይዛ ትወጣለች፣ ዚያራ ሽርሽር ትሄዳለች፡፡

የተቀረው ሕይወቷ ባዶ፤ ዙርያው የተከረከመ ይሆንባታል፤ … አንዳንድ ጊዜ መልካም ሀሳቦች ይመጡላታል፡፡ እዝነት አላቸው፣ ሻል ይላሉ ብላ ላሰበቻቸው ለሚጠይቋት ወንዶች ስለ ችግሯ ማማከርና መንገር ታስባለች፤ ግና ተመልሳ ትተወዋለች፣ ድፍረት ታጣለች፤ ቢስቁብኝስ፣ ቢሸሹኝስ፣ ሙድ ቢይዙብኝስ፣ ቢያስወሩብኝስ … እያለች ትጨነቃለች፡፡ ብዙ ሰዎች ዛሬ ላይ ራስ ወዳድ ሆነዋል፤ ችግሯን ቢያውቅላትም ከነእንከኗ የሚቀበላት፣ የሚሸከማት፣ ጊዜ ወስዶ ፣ ነገሩን ቀለል አድርጎ፣ ትዕግሥት ተላብሶ ... አካሏንና ሥነልቦናዋን የሚያክም ያለ አይመስላትም ...

 ለአንዳንድ በጣም ለምትቀርባቸው ሰዎች መንገር ታስብና ደግሞ እነርሱን ማስጨነቅ እንዳይሆንባት ትፈራለች፣ ለነርሱ ታስባለች …
በዚህ መልኩ ….

ይቀጥላል …

http://t.me/MuhammedSeidABX
815 views03:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-03-27 19:30:56 ንግግራቸው ስለማረካችሁ ብቻ የታዋቂ ሰዎችን ቀረቤታና ወዳጅነት አትመኙ፣
ሕይወት ዉጫዊ ገፅታ ብቻ ከሆነች ቆየች፣ ዉስጠባዶ ብዙ ነዉና ሰዉን እዘኑለት እንጂ አትታዘቡት።
ብዙዎችም ሥማቸው ከሥራቸው፣ ጥላቸው ከማንነታቸው በላይ ገዝፎ ይታያል።
ዘንድሮ ሰዎች ያለበሱት ልብስ ያልሰፋው ማን አለ ወዳጆቼ!
ሰዎችን ተከትለን ከጠበቅናቸው በታች ወርደው አገኘናቸው ከማለታችን በፊት አሁኑኑ ራሳችንን ሆነን መገኘት።

http://t.me/MuhammedSeidABX
962 views16:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-03-27 19:30:40
942 views16:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-03-27 18:04:32
895 views15:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-03-27 06:22:06 የሰርጓ ለታ (2)
...
አዎን ነበረች ...

ጉዳዩን ሲጨርስ፣ ባደረገው ረክቶም ግራ ተጋብቶም ዞሮ ተኛ፣ ….
እሷ ግን የባሰዉኑ ደከመች፣ ተዝለፈለፈች፣ ራሷን ሳተች፡፡
ድንገት ዞር ብሎ አዳመጣት፣ ትንፋሷን ሲያጣ ደነገጠ፣ ቶሎ ለባበሰና ታክሲ ጠርቶ ወደ አንድ ሆስፒታል ወሰዳት፣ የተለያዩ ድጋፎች ከተደረጉላት በኋላ ጠዋት አካባቢ ነቃች፡፡

ልክ ስትነቃ አንዲት ሐኪም ፊትለፊቷ ቁጭ ብላለች፡፡ ምን እንደሆነች፣ የት እንዳለች ለማወቅ ሞከረች። ሓኪሟ አረጋጋቻት፣ ጠየቃቻትም፡፡ ሙሽራ ስለመሆኗ እና ከትናንት ጀምሮ የሆነዉን ሁሉ አንድ በአንድ ነገረቻት፡፡

ሰዉነቷን፣ ኃፍረተ ገላዋንና ማህፀኗን ሁሉ ገልጣ በደንብ አየቻት፣ ፈተሸች፡፡ ባየችው ነገር በጣም ደነገጠች፣ ብዙ ደም ፈሷታል፣ በጠላት የተደረገ በሚመስል መልኩ ማህፀኗ ክፉኛ ተጎድቷል፡፡ ሐኪሟ በርግጥ እንዲህ ያደረጋት የገዛ ባሏ ስለመሆኑ ተጠራጠረች፣ ባሏን አስጠርታ የቻለችዉን ያህል ተቆጣችው፡፡ ፀፀት ገባው። ያለመታገስ ያመጣበት ጣጣ ምን ያህል ከባድ እንደሆነ ተረዳ።
የተጎዳ አካሏን ተሰፋች፤ ሥነልቦናዊ ህክምናም ተደረገላት። ከ15 ቀን በኋላ ነበር ከሆስፒታል እንድትወጣ የታዘዘችው፡፡
በዚህን ጊዜ ግን ወደ ቤቱ አልገባም ብላ አስቸገረች፡፡ ሰዉዬው አውሬ እንጂ ሰው መስሎ አልታይ አላት። ቤቱም የዱር አውሬ ቤት መሠላት። ቤተሰብ ስለጉዳዩ የሚያውቀው ነገር ስላልነበር በልጃቸው ድንገተኛ የባህሪ መቀያየር ሁኔታና በዉሳኔዋ ግራ ተጋባ፡፡
ኋላ ላይ በሱ ከባድ ፀፀት፣ ለቅሶ እና በቤተሰብ ብዙ ልመና ወደ ቤቱ ሄደች፡፡ ግና ቤቱ ምቾት ነሳት። እያንዳንዱ ቀን የዓመት ያህል ረዘመባት፤ በቀረባት ቁጥር ጥፍርና ጥርስ አውጥቶ የሚመጣባት የዱር አውሬ እንጂ ሰው መስሎ አይታያትም፡፡ በተለይ ምሽት በመጣ ቁጥር እንደ ህፃን ልጅ ትባንናለች፣ ትደነግጣለች፣ ትፈራለች፣ ትጨነቃለች፡፡ እንዲሁ በስጋት እንደተናጠች ሦስት ወራትን አብራው አሳለፈች፡፡ ለሱም ለሷም ጥሩ ጊዜ አልነበረም ።

ሁኔታው እየከፋ ሲሄድ ፍች ጠየቀች። እሱ ፈቃደኛ አልነበረም። በመጨረሻም ከብዙ ጭቅጭቅና ልመና በኋላ ተፋታች።

ቀናት አልቆሙም ፣ የአላህ ነገር ሆነና በመጀመርያው ቀን ክስተት ብቻ አርግዛ ነበር፡፡ ቀናት በገፉ ቁጥር ሆዷም ገፋ፣ ዘጠኝ ወር ሞላ፣ ምጥ ሲመጣ ሆስፒታል ገባች፡፡
ሊያዩዋት ወደ ማረፊያ ክፍል ወስደው አስተኟት። አልጋዋ ላይ እንዳደረጓት በዐይኖቿ ጠርዞች ክብልል እያለ የሚወርደዉን እንባዋን መገደብ ተሳናት፡፡ ሌላ ስጋት ገባት፣ ሌላ መሸማቀቅ አሳሰባት። ተከታታዩዋ ነርስ ተደናግጣ ምን እንደሆነች ጠየቀቻት፡፡

ታሪኳን እንደደገና እንደ አዲስ አወራች፣ ፍርሃቷንም ገለፀች፡፡ በዚያን ቀንም ቤተሰቦቼ ሚስጢሯን ሁሉ ሰሙ፡፡ በሰሙት ነገር ተቆጩ፣ ተበሳጩ፣ አዘኑ፣ ተቆጡ፣ እስከዛሬ ያን ሁሉ ስቃይሽን ለምን ደበቅሽን አሉ። በርግጥ ልጃቸው ጉዳት ላይ ነበር የከረመችው።
 በመጨረሻ ልጅ ተወለደ፡፡  በኦፕራሲዮን ነበር የወለደችው፡፡  
.....

ይቀጥላል



http://t.me/MuhammedSeidABX
1.1K views03:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-03-26 07:43:43 የሰርጓ ለታ (1)
**
"ነይማ እስቲ ኸዲጃ እምንወያየው ነገር አለ።" አሉ ሸይኽ ዐሊ ዛሬ ቀን ላይ ስለመጡባቸው እንግዶች ከባለቤታቸው ጋር መክረው ለመወሰን ብለው፡፡
እናት ኸድጃ ደግመው ባይሰሙት የሚመርጡት ወሬ ነበር። በርግጥም ከባልተቤታቸው ጋር መግባባት አልቻሉም።
“ትልቅና የተከበረ፣ የምናውቀው እና የሚያውቀን ቤተሰብ ነው፤ ልጃችሁን ለልጃችን እያሉ እንዴት እንከለክላለን?”  አሉ አባት ሸይኽ ዐሊ፡፡
"በይሉኝታ ታስረን ራሳችንንም ልጃችንንም መጉዳት የለብንም።" አሉ እናት ኸዲጃ ።
 “እሷስ ብትሆን ሊነገራት ይገባል፤ እንንገራትና ምን እንደምትል እንስማ !” አሉ ወ/ሮ ኸዲጃ ግራ እየተጋቡ፡፡
“ምን እሷ ምን ታውቃለች? እኛ ነን ክፉ ደጉን፤ ባለጌ ጨዋዉን አይተን የምንመርጥላት!” አሉ አባት፡፡
“እንግዲያዉስ እንዲያ ከወሰኑ እኔ የለሁበትም፤ የልጁን መጥፎነት እንደሁ አገር ያወቀው ነው፤ ገና የሚታወቅና የተከበረ ቤተሰብ ነው በማለት ምን ብዬ ነው ጨዋ ልጄን የምሠጥ!” አሉ እናት ክፉኛ ተናደው፡፡
እናትና አባት ኃይለኛ ሙግት ዉስጥ ገቡ፡፡ ዉዝግቡ ከረረ። አባት ፎከረ፡፡ የት ትወስጂያት እንደሆነ እናያለን አለ፡፡
እናትም ዛተች፣ ልጄንማ ለዚህ ከይሲ አትድሩትም! አለች፡፡

ጠያቂው ወገን መልስ ፍለጋ ድጋሜ ሽማግሌ ላከ፡፡ ቤተሰብ ተጨናነቀ፡፡ ሰፈር ጎረቤት ጉዳዩን ሰማ። ያልሆነ ወሬ ተወራ።
ቤተዘመድና ዘመድ ተሰባሰበና መከረ፡፡ ከብዙ ክርክር በኋላ የአባት ቃል አሸነፈ፡፡ ልጅትም ተለመነች። በመጨረሻም ሳትፈልግ፣ ሳትወድ በግድ ለማታውቀው ሰው ተሠጠች፡፡

በሰርጉ ቀን …
ሙሽሪት መንገድ ላይ ድንገት ታመመች፤ ድክምክም አደረጋት፣ አስመለሳት፣ እሷም፣ ባሏም አጃቢዎቿም ግራ ተጋቡ፣ መኪናው ይሁን ሙቀቱ አልታወቀም። አስሬ እያረፉና እየተናፈሱ እንደምንም ጉዞ ወደ ሙሽራው ቤት ሆነ፡፡ አይደረስ የለ ከብዙ እንግልት በኋላ ተደረሰ፡፡ ደማቅ ጭፈራ ነበር።
ሙሽራዉና ሙሽሪት ወደ ክፍላቸው እንዲገቡ ተደረገ፡፡ ሙሽሪት አሁንም እንደደከመች ነው፤ ምግብ አልቀመሰችም፣ የቀመሰችዉም ሆዷ ዉስጥ አልተረጋም፣ ቬሎዋን ጭምር ማውለቅ አቃታት፤ ሰዉነቷ ከዳት፣ ሄዳ እክፍሉ ዉስጥ ካለው ሶፋ ላይ ዘፍ አለች፡፡ ተጋደመች።
ባሏ ሊጠጋት ሲል አትንካኝ እዚሁ ልተኛ አሞኛል አለችው፡፡
አባባሏ ምቾት አልሠጠዉም፣ ተናደደ፣ ነብር ሆነ፣ 
እንዴት በዚህ ቀን ያማታል? የሚል ይመስላል ጥያቄው፤ ሌላ ነገርም እንደመጠርጠር አደረገው።
እንዳኮረፈ ሄዶ አልጋው ላይ ጋደም አለ፡፡

ሙሽሪት ትንሽ ሻል ሲላት ወደ አልጋው ሄዳ ከጎኑ ተኛች፣ እንዳኮረፈ ነው፤ እሱ ማባበል የሚገባትን ጭራሽ እሷ ታስረዳው ጀመር።
በዚሁ መሃል አሁንም ጋበዛት። ደክሞኛል አቅም የለኝም አለችው። በዚህን ጊዜ አልሰማትም፣ አላዘነላትም። ንቀትም መሰለው፣ ጠዋት ለጓደኞቹ ስለየትኛው ወንድነቱ ያውራ፣
ከሷ ህመምና ድካም በላይ ስሜቱ ጣርያ ነክቷል፤ ህሊናዉን ገፋ፣ እዝነቱን ተከላከለ፣ ስሜቱን አዳመጠ፣ ለሥጋው ጆሮ ሠጠ።

በዚያ ላይ ልጅት ጨዋ እንደሆነች ያውቃል፣ ትዝ ሲለው ቋመጠ፣ ምራቁን ዋጠ፣ ለሦስተኛ ጊዜ
ተጠጋት፣ ለመነችው፤ እሱ ግን ገፍቶ የመጣ ስሜቱን መቆጣጠር አልቻለም፤ የተወጣጠረ ሰዉነቱን ማርገብ ሞት ሆነበት፣ ንደረደረ፣ ተአስገድዶ የመድፈር ያህል በገዛ ሚስቱ ላይ እንደ አውሬ ሰፈረባት፤
ከዚያ በኋላ ስለራሱ እንጂ ስለሷ ሁኔታ ግድ አልነበረዉም፡፡ እሷም የሚሆነዉን በሰመመን ዉስጥ ሆና ከመታዘብ ዉጭ ምንም ማድረግ አልቻለችም፣ ራሷን መከላከል የማትችል ጀናዛ ነበረች …

ይቀጥላል

http://t.me/MuhammedSeidABX
1.3K views04:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ