የሰርጥ አድራሻ:
ምድቦች:
ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች:
5
የሰርጥ መግለጫ
በገጠር ኢትዮጽያ ቅድስት ቤተክርስቲያን ሁለንተናዊ መረጃ እና የአገልግሎት ማነቃቂያ ለመስጠት የተከፈተ መንፈሳዊ የዘገባ እና የድጋፍ ማሰባሰቢያ ቻናል ነው እሮብ እና ቅዳሜ ብቻ ይጠብቁን
Ratings & Reviews
Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.
5 stars
1
4 stars
0
3 stars
1
2 stars
1
1 stars
0
የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 7
2022-10-09 17:25:43
የጠፋው ልጅ
#ስለ_ጠፋው_ልጅ ታሪክ ስንነጋገር በዚህ ታዳጊ ወጣት የእያንዳንዳችን ምስል በጥቂት እንመለከታለን።
ምንም እንኳን ታሪክ ቢሆንም እኛ ማን እንደሆንን ምን እንደምናስብ አመልካች ነው።መልካችንን ያሳየናል፣እኛ ራሳችንን ከምናውቀው በላይ ፈጣሪ እያንዳችንን የበለጠ ያውቀናል።
ይኽንን ታሪክ ስናዳምጥ ስቶቻችን ሕይወታችንን ቆም ብለን መርምረናል።
መልካም ይህ ታሪክ የእኔ ሕይወት ይመለከታል ብለን ያሰብንን ስንቶቻችን ነን?
ሙሉውን ያዳምጡ
መልካም የማዳመጥ ትምህርት
249 views14:25
2022-10-09 17:03:27
የዕለተ ሰንበት የምስራች
በኢትዮ ኬንያ ድንበር በሆነችው የመንደር ቀበሌ 400 ኢ አማንያን አርብቶአደሮች ተጠምቀው የቅድስት ቤተክርስቲያንን ልጅነት አገኙ....
“ብዙ ሕዝብም ወደ ጌታ ተጨመሩ።”ሐዋ 11፥24
እግዚአብሔር ይመስገን ።
ዛሬ መስከረም 29/2015 በደቡብ ኦሞ ሀገረስብከት በኢትዮ ኬንያ የድንበር ቀበሌ በሆነችው ቡቡሃ መንደር 400 አርብቶ አደሮች ሐብተ ወልድ ስመ ክርስትናንን በሰማዕቷ ቅድስት አርሴማ ቤተክርስቲያን ተቀብለዋል።
ክርስትና የብልጦች ሳይሆን የየዋሆች ንጽሁ መንገድ ነው። አስልተህ ሳይሆን ተሰልቶልህ የምትመራበት የቀራንዮ ጎዳና ነው።
እግዚአብሔር ይመስገን !
@yeemariyaam21
@yeemariyaam21
@yeemariyaam21
250 views14:03
2022-10-07 06:02:59
በእውነት ደስ የሚል ነው
ላስተዋለው
https://youtube.com/shorts/SHTguiNyd5k?feature=share
494 views03:02
2022-10-05 20:33:38
ለዓመታት በልጅ እጦት የተፈተኑ ቤተሰቦች በአርባምንጭ ዝጊቲ አቦ ምልጃ የሆዳቸውን ፍሬ እያገኙ ነው.......
~~~~~
ይህኝ ጥንዶች ትዳር ከመሰረቱ በኃላ ለሰባት ዓመታት የሆዳቸውን ፍሬ ፣የአይናቸውን ማረፍያ የሚሆን ልጅ ፍለጋ ለማግኘት በብዙ ተፈትነዋል።
ከዘመናዊ ህክምና እስከ ወዳጅ ዘመድ ምክር ፈጻሚነት ድረስ እየከወኑ የእግዚአብሔር ስጦታ የሆኑ እንቦቅቅላ ልጃቸውን ለማግኘት ደክመዋል።
ነገር ግን አንዳች ጠብ ያለላቸው መፍትሄ አተው ለሰባት ዓመት ዘለቁ።ሁሉም መፍቴሄዎች ከድካም በቀር አንድ በጎ ነገር ታጣበት።
በስተመጨረሻ የቤቱ ራስ የሆነው ባል ወደ አርባ ምንጭ ዝጊቲ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ቤተክርስቲያን በመምጣት ጸበላቸውን በመጸበል ፆም ጸሎት በመያዝ ጻዲቁን በሱባኤ አናገራቸው።
የለመኑትን በጎ ነገር ቸል የማይለው የአርባምንጩ ዝጊቲ አቦ አነሆ በምልጃ ረድኤታቸው ደርሰውለት ከዓመታት በኅላ እቅፋቸው በልጅ ጠረን ይረሰርስ ዘንድ ቅዱስ እግዚአብሔር ፈቀደ።
"ጻድቁን ልጅ ለምኜ ሰጥተህኛል እና እነሆ የአንተ የሆነውን ልጄን አንተው ውሰደው " ሲሉ የህፃኑ ቤተሰብ ሐብተወልድ ስመ ክርስትና በአርባምንጭ ዝጊቲ አቦ አስነስተው በሐዘን እና በተሰበረ ልብ ወደ አጥቢያው የመጣ ቤተሰብ በፍሰሐ እግር ወደ ሀገራቸው ተመለሱ ።
እግዚአብሔር ይመስገን !
ዝጊቲ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ቤተ ክርስቲያን - አርባምንጭ
@yeemariyaam21
@yeemariyaam21
@yeemariyaam21
382 views17:33
2022-10-04 20:38:54
ለገጠር ቤተክርስቲያን በሳምንት 10 ብር pinned an audio file
17:38
2022-10-04 10:13:49
739 views07:13
2022-10-04 10:13:48
በሰሞኑ በሲዳማ ሃገረ ስብከት ለይርባ ደባራ ኬላ መካነ ቅዱሳን አቡነ ኤዎስጣቴዎስ ወቅድስት ድንግል ማርያም ቤተክርስቲያን ንዋየ ቅድሳት ከናንተ ከበጎ አድራጊ ምዕመናን እንደሰበሰብን ይታወሳል።
በዛሬው ቀን ደግሞ ማለትም በ22/01/2014 ዓ.ም በቦታው ተገኝተን ከናንተ የሰበሰብነውን ንዋያትን ለቦታው ገቢ ተደረጋል።
በዚህ መልካም ስራ ላይ የተባበራችሁ ምዕመናን በሙሉ እግዚአብሔር ይስጥልን እናመሰግናለን አምላከ ኤዎስጣቴዎስ የልቦናችሁን መሻት ይፈጽምላችሁ።
በዚህ የበረከት ስራ ላይ መሳተፍ እየፈለጋችሁ ነገር ግን ግዙ የተባልነው እቃ ተገዝቶ በማለቁ ምክንያት ያልተሳተፋችሁ በቀጣይ የበረከት ስራ እንገናኛል።
አምላክ ሰማያዊ ዋጋችሁን አያስቀርባችሁ።
ያደረስናቸው ንዋየ ቅድሳት ዝርዝር
1. አትሮንስ
2. ዚቅ(ዝክረ ቃል)
3. ተዓምረ ኢየሱስ
4. ሃይማኖተ አበው
5. ድርሳነ ሚካኤል ወገብርኤል ወሩፋኤል...(በአንድ ላይ)
6. መጽሐፈ ሰዓታት
7. ሥርዓተ ሰሞነ ሕማማት
8. መጽሐፈ ግንዘት
9. ሀዲስ ኪዳን ትርጏሜ
10. መጾር መስቀል
11. ጽንሓ
12. አውድ
13. ትልቁ መጽሓፈ ቅዳሴ
14. የመቀደሻ መስቀል( ለቅዳሴ አገልግሎት የሚውል መስቀል)
ብዛት 2
15. ማዕፈድ
16. መዝሙረ ዳዊት
በአጠቃላይ ከእናንተ በተሰበሰበው በ14000ብር
ስለሁሉም እግዚአብሔር ይመስገን
እግዚአብሔር ይስጥልኝ
@yeemariyaam21
@yeemariyaam21
@yeemariyaam21
@BeGood16
615 views07:13
2022-10-03 22:53:29
ጋብቻን የፈለግኸው ለምንድነው? ማግባት የፈለግሽው ለምንድነው?
ባሎች የሚወዱት ጥቅስ ሚስት ለባሏ ትገዛ የሚለውን ነው። ሚስቶችም ባል ሚስቱን ይውደድ ያላል ይላሉ።
ችግሩ ያለው ሁሉም የራሱን ጥቅስ አለማንበቡ ላይ ነው። ባል የሚስትን ሚስት የባልን ጥቅስ ያነባሉ።እኔ አፍቃሪ ባል ነኝን? እኔ አክባሪ ሚስጥ ነኝን? ማለት ይገባል።
ወደ መልስ ስመለስ
ትዳር ላልመሰረታቹው በሙሉ
መልካም ትምህርት
1.1K views19:53
2022-10-03 08:48:16
አዲስ ዘማሪ ነው አዳምጡ
646 views05:48
2022-10-01 11:05:25
ኑ ቤተከርስቲያን ትጠራናለች አቤት እንበላት።
የኬንቼው እየሱስ ቤተክርስቲያን የንግድ ባንክ
አካውንት ነው
➯ 1000261754987
ለገጠር ቤተክርስቲያን በሳምንት 10br
https://t.me/KeAbawandebet
https://t.me/KeAbawandebet
https://t.me/KeAbawandebet
ሁላችሁም እኅት ወንድሞች የተጀመረውን ቤተከርስቲያን ከፍጻሜ እናደርስ ዘንድ እናት ቤተከርስቲያን እኛን ልጆቿን ትጠይቃለች።
ለተጨማሪ መረጃ ለቴሌግራም፣ ለማናገር ለምትፈልጉ +251927707000 @BeGood16 ( የኔን ስልክ መጠቀም የምትችሉት ለቤተክርስቲያን የሚሆን እቃ እገዛለሁ አድርስ ለምትሉ ብቻ ነው) ማንኛውንም ብር በቤተክርስቲያኑ አካውንት ማስገባት ትችላላችሁ
856 views08:05