Get Mystery Box with random crypto!

የቴሌግራም ቻናል አርማ keabawandebet — ከ
የቴሌግራም ቻናል አርማ keabawandebet — ከ
የሰርጥ አድራሻ: @keabawandebet
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 5
የሰርጥ መግለጫ

በገጠር ኢትዮጽያ ቅድስት ቤተክርስቲያን ሁለንተናዊ መረጃ እና የአገልግሎት ማነቃቂያ ለመስጠት የተከፈተ መንፈሳዊ የዘገባ እና የድጋፍ ማሰባሰቢያ ቻናል ነው እሮብ እና ቅዳሜ ብቻ ይጠብቁን

Ratings & Reviews

3.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 9

2022-09-15 07:49:24 https://vm.tiktok.com/ZMF1hvUsH/
https://vm.tiktok.com/ZMF1hvUsH/
https://vm.tiktok.com/ZMF1hvUsH/
1.7K views04:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-14 07:44:23 ደጉ ሳምራዊ ሆይ እንደ መንገደኛው በወደቅሁበት በረሃ ማለፍህን እየተጠባበቁ አሁንም በኢያሪኮ ጎዳና ቁልቁለቱ መካከል ላይ ነኝና አትለፈኝ፡፡

ጌታ ሆይ ከእኔ ተሽለው ያልወደቁት ቢያዩኝም ትተውኝ አለፉ እንጂ ሊያነሡኝ አልቻሉም፡፡ እንደ ቀደሙት መንገደኞች ፈርተው አይመስለኝም፡፡ ይልቁንስ ሸተተን ብለው ሳይሆን አይቀርም፡፡ ደጉ ሳምራዊ ሆይ መበላሸቴ እውነታቸውን ነውና እባክህን አንተ ወደእኔ ተመለከት፡፡ ከወደቅሁበት ዛሬም አንሣኝ፡፡

እንደ ወንጌሉ በፍጹም ትሕትናህ በአህያህ ላይ ጫነኝ፡፡ ሰው መሆንን ወድደህ ሰው አለመሆንን ጠልተህ ስለእኔም ጭምር ሰው ሆነህ እንደ አህያ ደካማ የሆነ ባሕርያችን ገንዘብ አድርገሃልና ከወደቅሁበት አንሣኝ፡፡

ጌታዬ ሆይ ስለእኔ ሰው ሆነሃልና በፈቃዴ ከሰውነት ባሕርይ ተራቁቼ ከእንስሳነትም ወርጄ በጠባዬ አውሬ የሆንኩትን እኔን ለሰውነት መዓርግ አብቃኝ፡፡

ናከደበነፆርን ግብሩን አይተህ አረአያውን ለውጠህ አውሬ ካደረግኸው በኋላ ወደስውነነት እንደመለስከው እኔንም በጠባዬ አውሬ የሆንኩትን ስለእኔ ሰው መሆንህን አስበህ ለሰውነት አብቃኝ፡፡

ስለእኔ በበረት ራቁትህን በብርድ ተወልደሃልና፤ የኃጢአት ብርዴን አርቅልኝ፡፡ ስለእኔም ጭምር ብለህ በከብቶች እስትንፋስ ተሟሙቀሃልና፤ በሙቀተ መንፈስ ቅዱስ እኔን ከኃጢአት ብርድ አላቅቀኝ፡፡

ስለእኔ ቅጠል ለብስሃልና አውልቄ የጣልሁትን ወንበዴዎቹም የዘረፉኝን የልጅነት ልብሰ ጸጋዬን መልሰህ አልብሰኝ፡፡

ጌታዬ ሆይ የጠፋነውን ወደመንጋህ ለመመለስ አንተ ስለእኛ ተሰደሃልና አቤቱ እኔን መልሰኝ፡፡ የጠፋ በግህን ከቅዱሳን ኅብረት ከቅድስና ጉባኤህ ከመንጋህ ደርበኝ፡፡

እንርሱን አንድ ጉባኤ አንድ አካል ላደረገ ለቅዱስ ሥጋህና ለክቡር ደምህም አብቃኝ፡፡

ጌታዬ ሆይ አቤቱ በአዲስ ዘመን ዋዜማ በአጠገቤ እለፍና አንሣኝ፡፡ ዘይትና ወይን ባልካቸው የመሥዋዕት ደምህ ቁስሌን ጥረግልኝ፡፡ ጨርቅ በተባለ ፍቅርህም ግጥም አድረገህ እሰርለኝና ከጥላቻ፣ ከከንቱነት፣ ከግብዝነት፣ ከለፍላፊነት፣ ከኩራትና ከትዕቢት፣ ከዝሙትና ከርኩሰት ቁስሌ ማገገምን ስጠኝ፡፡

በአገልጋይህ በኩል ስበህ የእንግዶች ማደሪያ ወዳልካት ቤትህ አስጠጋኝ፡፡ ጌታዬ ሆይ እባክህን ለእኔ ለምስኪኑ ዛሬም ዲናርህን ክፈልልኝ፤ አቤቱ ሁለቱ ዲናሮችህ በተባሉ በብሉይና በሐዲስ እጅግ የደከመች ቁስለኛ ነፍሴን መግበህ አድንልኝ፡፡

የነፍሴ እረኛ ሆይ በአንተ ዘንድ ዝለት መሰልቸት የለምና የእኔ መቅበዝበዝ አይተህ ቸል አትበለኝ፤ ጠባቂዬ ሆይ በኃጢአቴ ምክንያት ካገኘኝ ደዌ ሥጋ ደዌ ነፈስ ፈውሰህ ሰው አድርገህ አቁመኝ፡፡

ስለእኔ የእሾህ አክሊል የደፋኸው ጌታ ሆይ የአንተ ራስ ስለእኔ ተወግቷልና ኅሊናዬን ከሚወጋኝ የሀሳብና የኃጢአት እሾህ አድነኝ፡፡

በውኑ አንተ ለእኛ ብለህ ካልሆነ በከንቱ ተወግተሃልን? ስለዚህ ጌታ ሆይ ቤተ መቅደስ ውስጥ ቆሜ እየጸለይኩ እያስቀደስኩ ሳይቀር እሾህ ነገር እያሰወጋ ከሚያቆስለኝ ክፉ ሀሳብ ስለደፋህልኝ የእሾህ አክሊል ብለህ እኔን አድን፡፡

አቤቴ እረኛዬ ሆይ በዘመነ ሥጋዌህ ኃጢአትህ ተተወልህ፣ ኃጢአትሽ ተተወልሽ እንዳልካቸው ኃጢአትህ ተትቶልሃል የሚለውን ድምጽህን አዲሱ ዘመን ከመግባቱ በፊት አሰማኝ፡፡

የልጆችን ለውሾች መስጠት አይገባም እንዳልካት ሴት ፈውስ ባይገባኝ እንኳ ጌታ ሆይ ውሾችም ከጌቶቻቸው ማዕድ የወደቀውን ፍርፋሪ ይበላሉ ስትለህ እምነቷን አይተህ እንደፈወስክላት እኔንም በእምነት ፍጹማን ከሆኑት የተረፈውን የፈውስ ፍርፋሪ አቅምሰኝ፡፡

ቤዛዬ ሆይ ስለእኔ ተገርፈሃልና በመገረፍህ ቁስል ፈውሰኝ፡፡ በሙሴ ፊት ብርሃን በሳልከበት በአንተ ፊት ላይ አይሁድ የረከሰ ምራቃቸውን ሲተፉብህ የተጋሰከው ቤዛዬ ሆይ ዛሬም እኔ በየቀኑ በአንተ ፍጡር ላይ የምተፋውን አይተህ አላጠፋኸኝም፣ ነገር ግን ርኩሱን ምራቅ በብርሃናዊ ፊትህ ላይ ስለመቀበልህ እኔን ከርኩሰቴ አንጻኝ፡፡

አንተ ስለእኛ ስለሁላችን ተከሰህ በጲላጦስ ፊትህ ቀርበህልናልና አቤቱ ጌታ ሆይ እኛ ስለኃጢአታችን አንከሰስ አንወቀስ፤ በአንተ መከሰስ እኛ እንፈወስ እንጂ፡፡ ጌታ ሆይ ስለአንተ መንገላታታ የምእመናን መንገላታት ይበቃ፡፡ ስለአንተ መናቅ እኛ በድነቁርናና ባለማሰብ፤ ባለማቀድና ባለመሥራት የገጠመን መናቅና መገፋት በአዲሱ ዐመት ይከልከልልን፡፡

ጌታ ሆይ ስለእኛ መስቀል ተሸክመህ ሦስት ጊዜ ወድቀሃልና፣ በግል በሠራነው ኃጢአት ከወደቅንበት ውድቀት፣ እንደተቋምም ተሰነካክለን ከወደቅንበት አዘቅት፣ የአባቶችን ገድልና ትሩፋት ይዘን ስለወደቅንበትም ታሪካዊ ውደቀት የአንተ መውደቅ ቤዛ ሆኖን እንነሣ፤ አቤቱ አንሣን፣ ቀጥ አድርገህም አቁመን፡፡

ተነሣ አልጋህን ተሸክመህ ተመላለስ እንዳልከው፤ ተነሡ ወንጌል እውነት ይዛችሁ፣ የተኛችሁበትን የታሪክ፣ የገድልና የፍቅር አልጋ ይዛችሁ በአገልግሎት ተመላለሱ ብለህ በኃጢአትና በድከመት የሰለሉ እግሮቻችንን አጽና፡፡

ጌታ ሆይ ስለእኛ ተቸንከረሃልና ከተቸነከርንባቸው የጎሰኝነት፣ የድንቁርና የጥቅመኝነትና የአድሎ ችንካሮች አልላቀን፡፡

አቤቱ ጌታ ሆይ ስለእኛ የሆምጣጤውን መራራ ጽዋ ቀምሰሃልና በምትኩ ከፍቅርና ከይቅርታ፣ ከዕወቀትና ከምሕረት ጽዋ እኛን አቅምሰን፡፡

ሳይገባህ ስለእኛ ተገንዘህ ተቀብረሃልና አቤቱ ከድንዛዜ መግነዝ ፍታን፣ ከጥልቅ የድንቁርና መቃብርም አውጣን፡፡ ስለ ልዩ ትንሣኤህ ትንሣኤ ልቡና ወኅሊና አድለን፡፡

ስለ ቅድስት ዕረገትህም ዕርገተ ኅሊናና አልዕሎ ልቡናን አሳድርብን፡፡ ስለ ዳግም ምጽአትህም በቀኝህ የሚቆሙ ወዳጆችህ የሚሠሩትን ምግባረ ሃይማኖት ለመሥራት አብቃን፡፡

ጌታ ሆይ በዚህች በዿግሜ ኢዮብን በዮርዳኖስ ወንዘህ አጥበህ እንደፈወስነው እኛን ኢትዮጵያውያንን ከሚያጸይፍ ቁስለ ነፍሳችን ፈውሰን፡፡ እጠበን እንጠራለን፤ አንጻንም እንነጻለን፡፡

ጌታ ሆይ ስለእኛ አይደለም መምጣትህን አስቀድመው ይነግሩ ዘንድ ስለነገርሃቸው አርእሰተ አበውና ነቢያት፣ መርጠህ አስተምረህ ሾመህ ዐለምን ወደአንተ ይመልሱ ዘንድ መስቀል መከራ ሞትን አሸክመህ ስለላክሃቸው ሐዋርያት፣ ኑፋቄ ዘርቶ መንጋውን ከአንተ ለመለየት የተጋውን የዲያብሎስን ሽንገላ ተቃውመው ሃይማኖትን በንጽህ ስለጠበቁ ሊቃውንት፣ ፍትወታትን ድል

ነሥተው በተጋድሏቸው ያለደም መፍሰስ ሰማዕትነትን ስለተቀበሉ ጻድቃን፣ የነገሥታትን ማስፈራራትና የሚያደርሱባቸውን መከራ ሳይሰቀቁ ነገሥታተ አሕዛብን ድል ስለነሡ ሰማዕታት፣ በንጽሕ እና በትጋት ሆነው ያለመታከት አንተን ስለሚያገለግሉ ሊቃነ

መላእከትና ሠራዊተ መላእክት ብለህ ይልቁንም ደግሞ ከሁሉም በላይ ስለሆነች ከእርሷ ሰው ትሆን ዘንድ ስለመርጥካት የንጽሕና መሠረት የባሕርየ አዳም መመኪያ ስለሆነች ስለንጽሕተ ንጹሐን ቅድስተ ቅዱሳን

ድንግል እናትህ ብለህ ጌታ ሆይ በወደቅሁበት አዘቅት እለፍና እኔን ምስኪኑን ቁስለኛ የዲያብሎስ ምርኮኛ ከወደቅሁበት አንሣኝ፤

በሚቀጥለው ዐመትና በመጪዎቹ ዘመናትም አንተን በመከተል ሕግህን በመጠበቅና ፈቃድህን በመፈጸም አንሣኝ፡፡

ለፈቃዴ አሳልፈህ አትሰጠኝ፣ ይልቁንም ለፈቃድህ የምገዛበትን ልቡና ሥጠኝ፡፡ አቤቱ አትተወኝ አትጣለኝም፣ አሜን፡፡

@yeemariyaam21
@yeemariyaam21
@yeemariyaam21
1.9K views04:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-14 07:44:23 አቤቱ በእኔ በኩል እለፍ ፡፡

ጌታ ሆይ በኢያሪኮው መንገደኛ በኩል እንዳለፍህ ይህች ዐመት ከማለቋ በፊት እባክህን በእኔም በኩል እለፍ፡፡

የጠፋውን በግ አዳምን የፈለግኸው ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ አቤቱ እኔንም ፈልገኝ፤ ባገኘኸውም ጊዜ እንደተሸከምኸው እኔንም ተሸከመኝ፡፡

የቀደመ ፍጥረትህን አዳምን ቸል እንዳላልከው ከእርሱ አብራክ የተገኘሁ እኔ ደካማ ልጁንም ቸል አትበለኝ፡፡ ይልቁንም ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ አንድ ሰው የተባለ አዳምን እንደተሸከምከው እኔንም ተሸከመኝ፡፡
አዎን ጌታ ሆይ በመንገድ ላይ የወደቀው ስም የለሽ አንድ ሰው እኔ እንደሆንኩ አውቂያለሁ፡፡

ከኢየሩሳሌም ልዕልና ነፍስ ወደ ኢያሪኮ የኃጢአት ቁልቁለት የወረድሁት እኔ እንደሆንኩ ገብቶኛል፡፡ አንተ ለእኔ ድኅነት የሠራኸውን አሸቀንጥሬ ጥዬ እኔን ካስቀመጥክበት ከፍታ ተንደርድሬ ለእኔ ፍላጎት ወደሚስማማው ቁልቁለት የወረድሁት በወንበዴዎች እጅም የወደቅሁት የኢያሪኮው መንገደኛ እኔ ነኝ፡፡ በምሥጢራት ከሚኖርበት ተግባራዊ የክርስትና ከፍታ በማስመሰልና በውድድር ወደሚኖርበት ዝቅታ የወረድሁት ስም የለሽ መንገደኛ እኔ ነኝ፡፡ በእውነትና በፍቅር ከሚኖርበት የወንጌል ተራራ ጥቅሶችን ወደፍላጎታችን ወደሚለጥጥ ገደል የወረድሁት የተመታሁ መንገደኛ እኔ ነኝ፡፡

አንተን በሕይወቴ አሳድሬ አንተ በእኔ እንድትሠራ ከሚያደርግ ከፍታ እራሴን ለአንተ የሚሠራ ወታደር ወደሚያስመስል የሕይወት አዘቅት አውርጄ የጣልኩት የቁልቁለት መንገደኛው እኔ ነኝ፡፡

ሰለወደቀው በማዘን ስለእርሱም በመጸለይ እውነተኞቹ ልጆችህ ከኖሩበት ከፍታ ሁሉንም ወደሚያስንቅና ወደሚያስተች ዝቅታ የወረድሁት መንገደኛ እኔ ነኝ፡፡ ነገሮችን በመንፈስና በአስተውሎት ከመመርመር በስሜትና በግብታዊነት ወደማበላሽበት ጉድጓድ የወረድሁትም እኔ ነኝ፡፡ በእቅድና በጥበብ ከመሥራት በትችትና በነቀፌታ በእልህና በብስጭት ወደመናገር ብቻ የወረድሁት ከንቱ በእውነት እኔ ነኝ፡፡ ጥቂቶቹን ልዘርዝር ብዬ እንጂ ጌታ ሆይ እኔ ያልተውኩት ሰገነት፣ ያልወደቅሁበትም አዘቅት ምን አለና፡፡

ስወርድ ደግሞ እንደተጻፈው ወንበዴዎቹ አገኙኝና ደበደቡኝ፡፡ የነበረችኝንም ሁሉ ቀሙኝ፡፡ ጌታ ሆይ እየወረድኩም ይዠው ከነበረው ያልቀሙኝ ምንም የለም፡፡

መጀመሪያ የቀሙኝ ስንገዳገድ የምደገፍባትን፤ አቀበት ቁልቁለት የማቋርጥባትን፤ አራዊትን የማርቅባትን፣ ሰንቅና ጓዜን የምሸከምባትን አንዷን ዘንጌን ጸሎቴን ቀሙኝና ድጋፍ አልባ አደረጉኝ፡፡ ተነሥቼ ልጸልይ ስቆም አካሌ እንደ ሐውልት ቆሞ ነፍሴን ይዘዋት ይዞራሉ፡፡ አንዳንዴ ጥርሴን ያስነክሱኛል፡፡ አንዳንዴ ስለአንተ ተቆርቋሪ አስምስለው ጦርነት ውስጥ ይከቱኛል፡፡

ሌላ ጊዜ በአንተ በኩል ማግኘት የሚገባኝን ጥቅም ያሳስቡኛል፡፡ ሌላ ጊዜ አንተ የማያስደስቱ የሚመስሉኝን እንድትቆርጥ እንድትጥል ያሳስቡኛል፡፡ ሌላ ጊዜ ደግሞ የተረሳ ዘመድ ወዳጅ፣ የሞተ የጠፋ ቤተሰብእ ሳይቀር እያሳዩ ተመስጦ በሚመሰል ሕይወት ውስጥ ያጃጅሉኛል፡፡

የቀረ ሥራ የከሰረ ሀብትም አሳስበው ያናድዱኛል፡፡ ብቻ ነፍሴን የማይወስዱበት ቦታ የለም፡፡ ብሞት እንኳ መልአከ ሞት ነፍሴን ሊየንገላታት የማይችለውን ያህል ነፍሴን ያንከራትቷታል፡፡ ጸሎቴን ቀምተው ነፍሴን ማረፊያ ያጣች አሞራ አስመሰሏት፡፡

ስለዚህም የውስጥ ሰላሜ ተነጠቀ፡፡ እንኳን ከሌላው ከትዳር አጋሬ ከወላጅ ከቤተሰቤ በሰላም መነጋገሬን ሁሉ አከታትለው ቀሙኝ፡፡

ትዕግሥቴን ነጥቀዉ እንደ ፍየል ለፍላፊ፣ እንደ ጉጉት ጯሂ አደረጉኝ፡፡

ለሚናገረኝ ካልመለሰኩለት፣ የሚመለከተኝን ካልገላመጥኩት የተጠቃሁ እያስመሰሉ በመልካም የመመለስ ሀብቴን ዘረፉኝ፡፡ ይባስ በለው ልዩነቴን በእወቀት ከማስረዳት፣ ለመግባባት ከመወያየት አፋትተው የተለየለት ግልፍተኛ ተሳዳቢ አደረጉኝ፡፡

አሁንማ ካልተሳደብኩ ዐለም መሸነፌን አውቆ የሚስቅብኝ እያስመሰሉ እንኳን ይቃረኑኛል ለምላቸው በሀሳብ ይቀርቡኛል የምላቸውንም በእኔ መንገድ ስላልተናገሩ ብቻ የማላደላ ጀግና በማስመሰል እንድወርፋቸው ያደርጉኛል፡፡

ወደ ቀደመ ሕይወቴ እንዳልመለስም መንገዱን አጠሩብኝ፡፡ ጉባኤ ሔጄ እንዳልማር ጊዜ የማባክን ይመስለኛል፡፡

አንዳንድ መምህራንንም በትችት ስላስናቁኝ የመቀመጥ ትዕግሥቴ ራሱ የት እንደገባ አላውቅም፡፡ በጓደኛ ተጽእኖ ስቀመጥም ለእኔ ብሎ ከመስማት ይልቅ ይህ ለእነ እገሌ ነበር የሚያስፈልግ ያሰኘኛል፡፡

ሌላ ጊዜ ደግሞ ዛሬም ይህን ይሰብካል እንዴ ያሰኘኛል፡፡ እኔ በማዘወትረው ኃጢአት ሳላፍር መምህሩ የሚታወቅ ትምህርት አስተማረ ብሎ አያፍርም ወይ ያሰኘኛል፡፡

ሌላ ጊዜ ደግሞ የሚነገረውም አሽሙርና የማይረባ ያስመስልብኛል፡፡ እዚህ ከምማር በቃ ቤቴ ተቀምጬዬ አነብባለሁ ብሎ ካስተዋኝ በኋላ ቤቴ ስገባ ቴሌቪዥን ጋር ያፋጥጠኛል፡፡

እርሱ ሲሰለቸኝ ማኅበራዊ ሚዲያው ላይ የወጣ ነገር እንድመለከት በጓደኞቼ በኩል ያስደውልብኛል፡፡ እንደምንም ታግዬ ላነብብ ስነሣ እንቅልፍ እንደበረዶ ያዘንብብኛል፡፡

በቃ በጎው ነገር ካመለጠኝ በኋላ አልያዝ አልጨበጥ አለኝ፡፡ ምክር እንዳልጠይቅ ትልቅና አዋቂ ሰው ነው በሚባል የገጸ ባሕርይ ካባ ሸፍነው አሳፍረውኛል፡፡ ከዚህ ሁሉ የተነሣ በነፍሴ ሕመም ሥጋዬም ታማሚ ሆነ፡፡

እንደወፈረኩ ደከማ፣ እንደጠገብኩ ልፍስፍስ አደረጉኝ፡፡ እንዳልጾም ሰውነቴ ሁሉ እንቢ አለ፡፡ እንዳልሰግድም ጉልበቴ ሁሉ ተብረከረከ፡፡ በሁሉ ባዶ ሆኜ ቁጭ አልኩ፡፡

የነፍሴ መድኃኒት ጌታዬ ሆይ አፍ ማብዛቴን፣ ነገር መውደዴን አይተህ ነው መሰል አፍን በማስክ የሚያስይዝ የተግሣጽ ደዌ ብታመጣም የእኔ ነፍስ ግን አሁንም አላስታዋለችም፡፡

እጆቼ ማስኩን አፌ ላይ ቢያደርጉም ምላሴን ሊያስቆሟት ግን አልቻሉም፡፡ አንተ ለደቀመዛሙርትህ እንዳልከው አፍን የሚያረክሰው ከውጭ የሚገባው ሳይሆን ከውስጥ የሚወጣው ነውና ከነፍሴ ቁስል የተነሣ በአፌ የሚወጣው የነገር ጠረን አካባቢውን አሸተተው፡፡

እንኳን ለሌላው ለእኔም እየተሰማኝ ቢሆንም ነፍሴን የደበደቧት ወንበዴዎች ግን እንድነቃ አልፈቀዱልኝም፡፡ ስለዚህ ጌታ ሆይ የአፍ ብቻ ሳይሆን የልብና የኅሊና ማስክ እዘዝልኝ፡፡ እንደ ዳዊት ወዳጅህ ለአፌ ጠባቂ ሹምለት፤ ከንፈሮቼንም እንደ ቤተ መቅደስህ በር በምሕረትና በእውነት የሚከፈቱ አድርግልኝ፡፡

ጌታ ሆይ አሁን ችግሬ ገብቶኛል፤ ማስክ የሚያስፈልገኝ ለውጨኛው ሳይሆን ለውስጠኛው የኅሊና አፌ ነው፡፡ ጸረ ተሐዋሲ መድኃኒትም ከሥጋዬ ይልቅ ለነፍሴ እጆች እንደሚያስፈልጋቸው ገብቶኛል፡፡

አቤቱ ሰነድ በመደለዝ፣ ደም በማፍሰስ የረከሱ እጆቻችን በምን ይነጻሉ? የሐሰት ትርክት በመተረክ፣ የበለው ግደለው ቅስቀሳ በመጻፍ የዋሆችን በማነሣሣት ደም ያፈሰሱ የምሁር እጅ ነኝ የሚሉ የነፍስ እጆቻችንስ ቤትኛው ሳኒታይዘር ይነጻሉ? ጌታ ሆይ ዘንድሮ ሁሉንም ችግሮቼን ነግረኸኛል፡፡

በተለይ ርቀት ያለመጠበቅ፣ ቦታዬንም ያለማወቅ ችግር አስታውሼው አላውቅም ነበር፡፡ የእኔማ የተለየ ነው፡፡ እንኳን በሾምካቸው በጳጳሳት በካህናት በአንተ ወንበር ተቀምጬ ስፈርድ፣ ስገድል ሳድን፣ ስሰጥ ስነሣ ነው የኖርኩት፡፡

በወንጌል አልገባ ቢለኝ በበሽታ አስመስለህ ርቀትህን ጠብቅ ብትለኝም ልመለስ አልቻልኩም፡፡ ግን ወድቄያለሁና ተነሥቶ መቆም ርቀቴንም መጠበቅ እንዳይቻለኝ ደርገው ወንበዴዎቹ አጋንንት ስወርድ አግኝተው ደብደበውኛልና ተመልሶ መቆም ተሣነኝ፡፡

@yeemariyaam21
@yeemariyaam21
@yeemariyaam21
1.3K views04:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-12 13:10:36 ​​​​እንኳን ለታላቁ ነቢይና ሰማዕት ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ

@yeemariyaam21
@yeemariyaam21
@yeemariyaam21
1.7K views10:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-11 09:14:48 እንኳን አደረሰን

እኔን ተመለከቱ  3 ደቂቃ ነው 











እግዚአብሔር ይስጥልኝ
610 views06:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-10 23:52:55 ​​​​ የምወድህ ልጄ ሆይ እንደ ዘመኑ አንተም ተለወጥ

ልጄ ሆይ....... ወጣትነት ፈትኖህ፤ለስጋህ አድልተህ፤ነፍስህን አቀጭጨኻት ከአለም የኖርክበትን ዓመትህን ጥለኸው በንሰሐ እንደ ዘመኑ አንተም ተለወጥ።

ልጄ ሆይ ..... በአዲስ አመት ለአምላክህ የሚገባህን ግብር ትፈፅም ዘንድ በፍቅሩ አፀድ እንድትገኝ ካለመታዘዘ ተለወጥ።

ልጄ ሆይ ....... በአፈር ከሚሸነፈው ስጋዊ ዘርህ ወጥተህ ሰማያዊነትን ከሚያለብስህ ከማይጠፋው ሰማያዊ ዘር ክብረት ታደርግ ዘንድ ሰውን ካለመውደድ ጥላቻ ተለወጥ።

ልጄ ሆይ ...... በምክንያቶች ተደልለህ አፅዋማትን ዘለህ፤ምስጋናን ነፍገህ፥አገልግሎትን ንቀህ ከአለም ጫጫታ ውስጥ የዘፈቀውን ማንነትህ እንዳያጠፋህ እንደ ዘመኑ አንተም ተለወጥ።

ልጄ ሆይ ...... ዲያቢሎስ በቃል እንዳያስትህ፤በማማለል እንዳይጠልፍህ የመንጋውን ጠባቂ ቃልን ስማ፤ የመታዘዝን በረከት ታገኝ ዘንድ ከትምህክትህ እንደ ዘመኑ አንተም ተለወጥ።

ልጄ ሆይ .....ቀናት ሳይሆን መንፈስህ ይለወጥ፤ፀሐይ ሳትሆን የህይወት ጀንበርህ ይለወጥ።

ልጄ ሆይ ......ዕለታት አይሰልጥኑብህ፤ ዘመናት  እስከ ሞትህ ጥግ ድረስ እስኪገፉህ ሳትጠብቅ አንተም እንደ ዘመንህ ተለወጥ

ልጄ ሆይ .....የእግዚአብሔር ፍቅር ለተከፈተ ልብ ቸር ነው ። ርህራሄው ጥልቅ ነው ። በአምሳሉ ፈጥሮሃል እና እንዳትጠፋ አንድያ ልጁን ለሞት አሳልፎ እስከመስጠት የደረስ ጥልቅ ፍቅር አሳይቷል ። ስለዚህ ከዘመንህ ቀድመህ ተለወጥ።

ልጄ ሆይ ...አዛኝቷን ተለማመን፤መላአኩን ተማለደው ፤ቀደምት ቅዱሳን አባቶችህን ጥራ፤ ፃድቃንን ዘክር እንጅ ላለመለወጥ ተማምለው ቀናት ብቻ ከሚለወጥባቸው ሰልፈኞች ተርታ አትገኝ ።

በንስሐ ወደ በረቱ የምንመለስበት ዘመን ይሁንልን! አሜን

መልካም አዲስ ዓመት ይሁን ለኹላችን | ሠናይ ሐዲስ ዓመት ይኲን ለኲልነ
           ወስብሐት ለእግዚአብሔር
           ለወዳጅዎ ሼር ያድርጉ!

https://t.me/yeemariyaam21
854 views20:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-09 22:56:25 ‹‹አዲስ ዓመት መልካሙን የምንሰራበት ይሁንልን!››


:
☞ዘመናትን የሚያቀያይርና አዲስ ዓመትን የሚሰጠን እርሱ
ፈጣሪ ነው።
:
ይህንን የፈጣሪን ምህረትና ቸርነት የምናስብ ስንቶቻችን
ነን?
:
ሰው ደግሞ ተጨማሪ አዲስ ዓመትና እድሜ ካልተሰጠው
ምንም ማድረግ አይችልም፡፡
:
ፈጣሪ እንድንኖር ካልፈቀደልን አዲሱን ዓመት ካልሰጠን
ምንም ነገር ማድረግ አንችልም፡፡
:
# ሌላው ቀርቶ፦

➊.ወጥተን→የምንገባው፣
:
➋.ተቀምጠን→የምንነሣው፣
:
➌.ተምረን ለውጤት→የምንበቃው፣
:
➍.ሠርተን→የምናገኘው፣
:
➎.ነግደን→የምናተርፈው፣
:
➏.ወልደን→የምንስመው፣
:
➐.ለመጪው ዓመት ብለን እቅድ→የምናቅደው ፈጣሪ እንደ
ቸርነቱ ወደ አዲሱ ዓመት እንድንሸጋገር ሲፈቅድልን ነው፡፡
:
√ብዙ ሰዎች ግን የፈጣሪን ቸርነት ረስተዋል፡፡
:
√አዲስ ዘመን ሲሰጠን ዋጋ የሚከፈልበት ቢሆን ኖሮ ዋጋውን
ማን ይችለው ነበር?
:
√ግን ፈጣሪ አዲስ ዓመት የሰጠን ያለዋጋ በነፃ ነው።

√ለምንኖርበት ዕድሜ ለሰጠን ተጨማሪ ዓመት የጠየቀን ዋጋ
የለም፡፡
:
√ታዲያ ጊዜ የሰጠን ፈጣሪ ደግሞ ጊዜ እንድንሰጠው
እንድናመሰግነው ይፈልጋል።
:
❀︵♡︵♔︵♡︵♔︵♡︵♔︵♡︵❀
:
# አዎን ወዳጆቼ፥

☞አንዳንድ ሰዎች እንዲኖሩ፣ እንዲወጡና እንዲወርዱ አዲስ
ዓመትና ጊዜ ፈጣሪ ሰጥቷቸው ሳለ አዲስ ዓመት ለሰጣቸው
ለፈጣሪ ግን ጊዜ መስጠትና ማመስገን ተስኗቸው
ይስተዋላሉ፡፡
:
♡ይህቺን ቀን አስበው እዚህች ቀን ላይ፣ ለዚህች ዓዲስ
ዓመት ያልደረሱ ብዙ ሰዎች አሉ።

♡አንተ እኔ ሁላችንም ግን ደርሰናልና እንደ ቸርነቱና ምህረቱ
ለዚህ ላደረሰን አምላካችን እንዲህ እያልን እንፀልይ፦

➊.አምላካችን ሆይ፥ አዲሱን ዓመት ስለሰጠኸን
እናመሰግናሀለን።
:
➋.አምላካችን ሆይ፥ ከዚህ በኋላ የሚኖረን ቀሪ እድሜ
በፊትህ ያማረ ይሁንልን፡፡
:
➌.አምላካችን ሆይ፥ እድሜና ዘመናችን በቤትህ ይለቅ፡፡
:
ማለዳ ማለዳ በአዲስ ምስጋና፣
:
በአዲስ ዝማሬ፣
:
በአዲስ ሽብሸባ፣
:
በአዲስ ቅኔ፣
:
በአዲስ እልልታ ይህ በረከት የሆነው እድሜና ዘመናችን
በቤትህ ይለቅ፡፡

➍.አምላካችን ሆይ፥ ሳናመሰግንህ ላለፉት የምህረት
አመታት ሁሉ ዛሬ ይቅር በለን፡፡
:
➎.አምላካችን ሆይ፥ የሚከፋፍለን የሚያለያዬንን የጥል፤
የክርክር፤ የዘረኝነት ግድግዳ አንተ አፍርስልን።
:
➏.አምላካችን ሆይ፥ በአዲሱ ዓመት ፍቅርና አንድነትን
ስጠን።
:
➐.አምላካችን ሆይ፥ ሐገራችን ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ባርክ።
:
➑.አምላካችን ሆይ፥ በሰጠኸንም እንደ ቸርነትህ
በጨመርክልን አዲስ ዓመት መልካሙን እንድንሰራበት አንተ
ይርዳን! # ለዘላለሙ አሜን!
:
♡እስኪ ተመስገን በሉት። ተመስገንንንንንንንንንንንንንንንን
:
❀︵♡︵♔︵♡︵♔︵♡︵♔︵♡︵❀
:
# መጪው አዲስ ዓመት፦

➊.ሀጥያትን→በጽድቅ፣

➋.አለመጸለይን→በመጸለይ፣

➌.ስጋዊነትን→በመንፈሳዊነት፣

➍.አለማገልገልን→በማገልገል፣

➎.ድህነትን→በመስራት፣
:
➏.አለማንበብን→በማንበብ፣
:
➐.አለማወቅን→በመማር፣
:
➑.ጥላቻን→በፍቅር፣
:
➒.ክፉን→በመልካም፣
:
➓.ንፉግነትን→ በመስጠት፣ የምንከርመበትና ፍቅር የበዛበት
ብሩህ ዘመን ይሁንልን!
:
[☞መልካም አዲስ ዓመት☜]
:
«ሼር በማድረግ ለወዳጆ ያካፍሉ»
:
"ሰላማችሁ ይብዛ"
:

​​​#አድራሻ ፦

#ቤቴል አደባባይ  100 ሜትር ወረድ እንዳሉ   ኑሃ ህንፃ ቢሮ ቀጥር 3 ላይ እንገኛለን።

ለቀጠሮው +251927707000 ይደውሉ



    #ሰው_ሁን_ከሰውም_ሰው_ሁን

#ቴሌግራም

https://t.me/BiniGirmachew
https://t.me/BiniGirmachew
https://t.me/BiniGirmachew

SUPPORT ON YOUTUBE











       tiktok 

tiktok.com/@bini_girmachew
tiktok.com/@bini_girmachew

#ሰው_ሁን_ከሰውም_ሰው_ሁን
1.1K views19:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-09 08:28:28 https://t.me/yeemariyaam21
1.5K views05:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-09 07:48:36
@yeemariyaam21
@yeemariyaam21
@yeemariyaam21

ለማንኛውም ጥያቄ @Begood16  ላይ መጠየቅ ይቻላል
1.2K views04:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-09 07:15:25 እዚህ ላይ ገብታችሁ የተ ተሥራሃ
ምን ተሥራሃ? ምን ላይ ደረሰ የሚለውን ተመለከቱ እንግዲህ አስታወሱ በሳምንት 10 ብር ብቻ ተሰብስባ ነው

እግዚአብሔር ይስጥልኝ

https://vm.tiktok.com/ZMNKEhC4p/
https://vm.tiktok.com/ZMNKEhC4p/
https://vm.tiktok.com/ZMNKEhC4p/
1.1K views04:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ