Get Mystery Box with random crypto!

ISLAMIC SCHOOL

የቴሌግራም ቻናል አርማ islam_and_science — ISLAMIC SCHOOL I
የቴሌግራም ቻናል አርማ islam_and_science — ISLAMIC SCHOOL
የሰርጥ አድራሻ: @islam_and_science
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ሀገር: ኢትዮጵያ
ተመዝጋቢዎች: 18.51K
የሰርጥ መግለጫ

✍ ጅልከሆንክ ጅል ተከታይ ጀንትል ከሆንክ አስከታይ ትሆናለህ..!
ጅልም ጀንትልም ካልሆንክ ደግሞ አርፈህ በራስህ ዓለም ትኖራለህ..! አንባቢ እንሁን፡፡ለውጥ ከራስ ቢጀመር ...የቸገረን ጥሩ መካሪ ሳይሆን፤
የሰማነውን መተግበር ነው ያቃተን!ጅህልና በሽታ ነዉ፡፡
🎖For any comment T.me/Aisuu_bot
💠Another channal
@IslamisUniverstiy_public_group

Ratings & Reviews

3.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 3

2023-04-01 18:17:50 እባካችሁ አሊሞች ሸይሆች  እኛን ወጣቶች በቁርአን በሀዲስ ኮትኩታችሁ ለነገ ትዉልድ ማስተላለፍ ቢያቅታችሁ እንደዚህ ፈሳድ የሆነን በየአመቱ ተከታይ አታድርጉን እባካችሁ ወጣቱን የማይጠቅም የማይጓዳ ጀነሬሽን ባለማድረግ ተባበሩን


የተወሰነ ሰዉ ባይሄድ አሁን ባለቸዉ አቋም የሚቀር የሚቆም አይደለም
ግን አለመሄድ የባለቤቱ ወሳኔ ነዉ...አምና ታስታዉሱ ከሆነ ደሴ በተደረገዉ የጎዳና ኢፍጣር ከአየሁ ቡሀላ
በዛዉ በተደረገ ቀን ከአሁን ቡሁላ ላልሄድ ብየ ምያለሁ....ከዘንድሮ ጀምሬ አደባባይ ኢፍጣር አልሄድም
ይሄን ያነበበ አስተንትኖ ነገሮችን ከግራም ከቀኝም ከሆላም ከፊትም ከሁሉም አቅጣጫ ተመልክቶ በየአመቱ ለወደፊት ለሚካሄድ ኢፍጣር ራሳችሁን ብታገሉ ባይ ነኝ ...የአንድ የሁለት ሰዉ መቅረት ይሄን የአደባባይ ኢፍጣር ለማስቆም አቅም ባይኖረዉም ግን ለወደፊት በየአመቱ ለሚፈጠር ቢድአ ተባባሪ አለመሆን አንድ የሙስሊም ግዴታ ነዉ





ነገር ግን አንዳንድ ደጋግ የአላህ ባሮችና ኢብኑ መስኡድ ኢስላሚክ ሴንተር በየጎዳናዉ የተቸገሩን ማፍጠሪያ የሌላቸዉን በየጎዳናዉ ያስፈጥራሉ እንደዚህ ያሉትን ደጋግ ባሮች ጀመአዎች ለአላህ ብለዉ የሚሰሩን አላህ ንያቸዉን አጅራቸዉን እጥፍ ድርብ ያርግላቸዉ ይሄ መበረታታት ያለበት ነዉ...ነገር ግን የአደባባይ ኢፍጣር ተብሎ ፆታ መለየት እስከሚያቅት  ወንድ ሴት ተደባልቆ ታላቁ በአይኑ የተለየ ይሄን ያህል ሜትር  ክብረ ወሰን በጠስን እያሉ በዲን ስበብ ፈሳድ ባይበዛ ኸይር ነዉ፡፡


ኸይር ፅፌ ከሆነ ከጀሊሉ ነዉ መጥፎ ወይ ስህተት ፅፌ ከሆነ ከሸይጧን ነዉ አዉፍ በሉኝ ስህተት ከሆነም አሳማኝ ምክንያት ከአገኘሁ ስህተት ነዉ ብየ ፁሁፉን ከቻናል እሰርዛለሁ
711 viewsedited  15:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-01 18:17:40 የጎዳና ላይ ኢፍጣር ደረሰ
        አሚር ሰይድ
     
አሰላሙ አለይኩም እንዴት ናችሁ
በፊት በልጅነታችን መድረሳ ቁርአን በምንቀራበት ጊዜ ከኢድ አልፈጥርና ከኢደል አድሀ በላይ ለልጆች የምንወደዉ የሚበላበት የሚጠጣበት
መድረሳ መስጂድ ዉስጥ ነሺዳ ፕሮግራም አዘጋጅተን የምንማማርበት በአል የመዉሊድ በአል ነበር...በልጅነታችን ለብዙ አመታት መዉሊድ በአልን በደስታ እናከብር ነበር...እድሜያችን በሰለ ዲነል ኢስላምን ሰዉ ማወቅ ሲያስተነትን ወደ ቁርአን ሀዲስ ስናዳምጥ ለስልጣን ብለዉ ሳይሆን ለአላህ ለዲነል ኢስላም ብለዉ የሚያቀሩ የሚያስተምሩ ዳኢዎች ኡስታዞች መውሊድ ሀራም መሆኑን በማስረጃ በማስደገፍ ሲነግሩን ትክክል ይሄ ቢድአ ነዉ በመዉሊድ ምክንያት ወደ ተለያየ ሀገር እየተሄደ ፈሳድ ዚና ይበዛል ሺርክ ይሰራል ተብሎ በማስረጃ አስተማሩን ሰሚዕና ወአጦዕና ብለን ብዙ ሰዉ መዉሊድን ቤተሰቦቻችን ሳይቀር ማክበር አቆምን አልሀምዱሊላህ

ዛሬስ?? የጎዳና ላይ ኢፍጣር ተብሎ ከመዉሊድ የማይተናነስ ችግር ይዞ መጥቷል፡፡

መቼም አሁን ላይ ስንት አሊም መሻይሆች ባሉበት ሀገር እንደኔ ያለዉ ጃሂል መናገር መፃፍ አቅሜ ባይፈቅድም ግን እያዩ ማለፉ ብዙም አልተዋጠልኝ ይህ ትዉልድ ለወደፊት በረመዳን አንድ ቀን በየአመት የጎዳና ላይ ኢፍጣር ተብሎ በዲን በኢስላም የሌለ ቢድዓ አይታወቅም እኛም ሙተን የሚቀጥል የዉመል ቂያማ ድረስ ሊደርስ ይችላል መቼም ዲነል ኢስላምን አላህ ይጠበቀዋል ግን
ለብዙ አስርት ወይ መቶ አመታት ሊቀጥል ይችላል...
ግን በኛ ዘመን መጀመር አሳፋሪ መሆኑን ልናዉቅ ይገባል

ብዙ ሰዎች የጎዳና ኢፍጣርን በሁለት ምክንያት ይደግፋሉ
➊ የሙስሊሙን አንድነት ለማጠናከር በሚል
➋ የሌላ ሀይማኖት ተከታዮች መንገዱን አደባባዩን እነሱ ብቻ ለምን ይጠቀማሉ እኛም እንጠቀም አይነት ነዉ፡፡

☞ብዙ ሰዎች አንድነትን ለማጠናከር ሲባል የቱ አንድነት?? ሀብሀብ ተምር በመንገድ ላይ ተበልቶ ነዉ እንዴ ስንት አሊም በተለያዩ የዲነል ኢስላም ነገሮች ያልተስማማበትን በጎዳና ኢፍጣር ላይ አንድነት የሚመጣዉ??? ወይስ የአደም ዘር ወንዱም ሴቶም በአደባባይ ሲያፈጥር ነው እንዴ አንድነት የሚባለዉ??
☞ የሌላ ሀይማኖት ተከታዮች መንገዱን አደባባዩን እደተጠቀሙበት ነዉ የሚሉ አሉ...አዎ ይጠቀሙ እኛ ከእነሱ ይሄን መዉረስ የለብንም ...አላህም በቅዱስ ቁርአኑ በዱንያ እንደሚደሰቱ ነግሮናል እንደፈለጉ ይደሰቱ ይጨፍሩበት... ይልቅ እኛ በእነሱ ከምንቀና ስንት ቁርአን ሀፊዞች ዳኢዎችን ኸይር ስራ የሚሰሩን በንከተል ይሻላል እንጂ ሌሎች ሀይማኖት ተከታዮች እግር በእግር መከታተል ትርፉ ቡሀላ ጥፋት ነዉ፡፡

በ2013  የሌላ ሀይማኖቶች ሙስሊሙን ለመጨቆን ትንሽ ተንቀሳቅሰዉ ስለነበር በጎዳና ማፍጠሩን እኛም በሀገራችን ይመለከተናል ኸይር ሆነ ጎዳና ላይ ማፍጠሩ
አምና 2014 ተደገመ በየሀገሩ በአደባባይ ተፈጠረ
ዘንድሮ 2015 ደግሞ ይሄዉ ለሶስተኛ ዙር በአደባባይ ይፈጠራል፡፡ እኔ በ2013 በ2014 አብሬ የዚህ አደባባይ ኢፍጣር ተሳታፊ አጅር ያለዉ ይመስል ስራም ሰርቻለሁ ግን ዘንድሮ በዚህ የጎዳና ኢፍጣር አልሳተፍም፡፡ ለምን አምና የጎንደር ሙስሊሞችን አንርሳ በዚህ የጎዳና ኢፍጣር መዘዝ ብዙ ሙስሊም ወንድም እህት እናት አባቶቻችን ተገለዋል ቆስለዋል የአካል ጉዳተኛ ሁነዋል ንብረታቸወ ተዘርፏል ክብራቸዉ ተነክቷል እናም ዘንድሮ የጎዳና ኢፍጣር በነዛ የጎንደር ሙስሊሞች በሞቱት በተጎዱት ላይ በደል መፈፀም ነዉ፡፡ በዚህ በጎዳና ኢፍጣር ላይ በአይኔ ያየሁት ችግር
☞ወንድና ሴት ይቀላቀል ፊት ለፊትም አብሮ ብዙ ሰዉ ያፈጥራል ከአጂ ነቢይ ጋር
☞በዚህ ጊዜ ሴቶች እንደ በአል አርገዉ ነዉ ከቤት የሚወጡት ኑሮ ተወዶ ለራሱ ያልተዉትን ኮስሞቲክስ
ፌር ተቀብተዉ በቃ ለትዳር ፍለጋ ለመጀናጀን ነዉ የሚወጣዉ 70%ሴቱ
☞ በዚህ ጊዜ ዚናም የሚሰራ ሊኖር ይችላል..ወይም በዚህ ቀን ስልክ የሚቀያየረዉ ብዙ ስለሆነ በትዳር ስበብ የዚና መስመር ሊጀምሩ ይችላሉ
☞በtiktok በfacebook በማህበራዊ ሚዲያ የሴቶች የወንዶች ፎቶ ጥልቅለውጥቅ ብሎ ሚዲያ ሲያጨናንቅ አይተናል ..ሴቱ የሚያደርገዉን የሚይዘዉን የሚጨብጠዉን አጥቶ ነበር ሴትነት ትርጉሙ እስከሚጠፋቸዉ
☞ ጎዳና ኢፍጣሩ ሰዉ ሲበተን በዘንድሮ ዘመናይ ዘፋኞች ይቅርታ ሙነሺዶች ለማለት ነዉ በእነሱ ወንድ ሴት ተደባልቆ ሲጨፍሩ አምና የታዘብነዉ ነዉ..አሁን የአምናዉ የአደባባይ ኢፍጣር video በእጄ አለ ...በጣም አሳፋሪ ነዉ ከምር

የሙስሊም አንድነት የሚባለዉ ወንድ ሴት አብሮ በመንገድ ሲያፈጥር ሲጋፋ ነዉ እንዴ?? ጎበዝ

አሁን ይሄ የጎዳና ላይ ኢፍጣር ከመዉሊድ በምን ተለየ????

ዘንድሮ ስንት ሙስሊም በኑሮ ዉድነት በርሀብ በሚፆሞበት በአገሪቱ ወቅታዊ ችግር ምክንያት ስንቶች ከአገራቸዉ ከመኖሪያቸዉ ተፈናቅለዉ መጠለያ ዉስጥ የሚበላ የሚጠጣ ከእርዳታ ብቻ እየተቀበሉ ረመዳን በሚያሳልፉበት ጊዜ እነሱን መርዳት ሲገባን እንዴት በዚህ አደባባይ ኢፍጣር ሰዉ ጠግቦ ላይበላ ፈሳድ ወንጀል ይሰራል???

የሚገርመዉ አምና ለጎዳና ኢፍጣሩ ላይ የአህባሽ አመለካከትን የሚያራምዱ አቂዳ ተከታዮች በብዛት መጥተዉ አይቻቸዋለሁ...አህባሾች ለደአዋ ለዲነል ኢስላም ለመመካከር ሲጠሯቸዉ አይመጡም ነገር ግን ለእዚህ ለጎዳና ኢፍጣር መጡ እነሱ የተሻለ ኸይር ነገር የሚሰራ ቢሆን እንደማይመጡ እርግጥ ነዉ ግን ኢፍጣሩ ሲያበቃ ለብቻቸዉ ሁነዉ በራሳቸዉ አመለካከት አቂዳቸዉን በነሽዳ ወንድና ሴት ተደባልቀዉ  ሲያስተላልፉ ነበር ...ለደአዋ ለኢስላም እንወያይ ሲሏቸዉ የማይመጡ እንዴት ለአደባባይ ኢፍጣሩ መጡ???
አንዳንዶች አይታወቅም አዲስ አበባ ከአፍሪካ ወይ ከአለም አንደኛ አደባባይ ኢፍጣር ክብረ ወሰን ለመበጠስ ልትሉ ትችላለሁ እሺ እንደ ተልካሻ ዲነል ኢስላም የማያቀዉ የሚያሳምን የሚመስል መልስ ልታመጡ ትችላላችሁ ግን በአደባባይ ኢፍጣር ነዉ ወይስ በቁርአን ሀፊዞች ቁጥር ብዛት በተዉሂድ ክብረ ወሰን በጠስን ተብሎ ቢወራ አይሻልም???
እሺ አዲስ አበባ እንደዚህ ከተባለ ሌሎች ከተማ ለምን ምክንያት ማድረግ አስፈለገ???
ከምር ግን ሊታሰብበት ይገባል...እኛ ለልጃቻችን ለትዉልድ ይሄን ማዉረስ የለብንም....የኛ ልጆች የልጅ ልጆች ይሄ የአደባባይ ኢፍጣር በነብዩ ሰዐወ በሱሀቦች በአራቱ ኸሊፋ ጊዜ የሌለ መቼ ተጀመረ ሲባል በኛ ዘመን በእኛ ትዉልድ ነዉ ብሎ መነገሩ ታሪክ ላይ መፃፉ አግባብ አይደለም


መዉሊድን ሀራም ነዉ ለማለት ስንት ኡስታዞች ኡለሞች መዉሊድ በዚህ ዘመን የተጀመረ ነዉ ብለዉ እንዳላስተማሩ ዛሬ ገና በ2013 የተጀመረን አንድነት የሚመስል ፈሳድ ለምን መከልከል ተሳናቸዉ???
የዚህ በጎዳና ኢፍጣር ሰበብ የሚፈጠር ወንጀል ማዕሲያ እስከ ቆየበት ዘመን ድረስ የኛ አስተዋፆኦ እንዳለበት ለትዉልድ መጥፎ ነገር እንዳላስተላለፍን ልናወቅ ይገባል


አሁን ላይ አሊሞች መሻይሆች የመስጊድ ኢማሞች  አሊሞችም መሻይሆችን ስልጣንን ላለማጣት ፍራቻ
የመስጊድ ኢማሞችም ይቺኑ የወር ደመወዛቸዉን ላለማጣት ፍርቻ ቢድአ ወንጀል መሆኑን እያወቁ ዝም ብለዋል የሚከለክል ስለሌለ ይሄን ፁሁፍ ያነበበ ሰዉ ቁርአን ሀዲስ አንፃር አስበን ህሊናችንን ዳኛ አድርገን
እኛ ባለመሄድ የዚህ ለወደፊት ብዙ አመታት የሚቀጥል እንደ መዉሊድ ቢድአ የሆነን የዚህ የአደባባይ ኢፍጣር ባንሄድ ጥሩ ነዉ፡፡
ደግሞ ይሄን የሚያካሂደዉ 90% ወጣቱ ነዉ
725 viewsedited  15:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-26 12:50:42 በነገራችን ላይ እንደ ወሎየ እያሰብኩም ሊሆን ይችላል... የኔ ሁለት አያቶቼ ክርስቲያን ናቸዉ ..አጎት የአጎት ልጅ ምናምን እንደ ወሎ አንድ ላይ በልተን ጠጥተን አድገናል ከዛ አንፃር እያሰብኩም ሊሆን ይችላል....ግን የኛ ሙስሊም ችግር ዲነል ኢስላምን እንኳን ለሌሎች ሀይማኖት ማዳረስ ይቅርና ለሙስሊሙ ለማስተማር ኡስታዞች ሸይሆች ከወጣት እስከ ትልቅ ሙስሊሙ በዱንያ ቢዚ ሁኗል የዚህ ችግር እንጂ
ሞክሩ እነሱን ኢስላምን በማስተማር ቀላል ነበር የኔ ቤተሰቦች 20% የሚሆኑት መልሰዉ ሰልመዋል
የኛ ችግር እነሱ ቦታ ተቀበሉ እንደዚህ አረጉ እርይ ኡኡኡኡ በቃ አለቀ የጮሀዉ ሁሉ 1% ሲሰራ አይታይም ጥጉን ይይዛል.... የሌሎችን ሀይማኖት ተከታዮችን ኢስላምን ለማስተማር እስከ ጥግ ድረስ ጥረት ሲደረግ አላየሁም...

ማወቅ ያለብን ለሌላ ሀይማኖት ኢስላምን ማስተማር ግዴታ እንዲሰልም አይደለም
ለኢስላም መጥፎ አመለካከት እንዳይኖረዉ ለማድረግ ጭምር መሆን መታሰብ አለበት ኢስላም የሚሰጠዉ አላህ ብቻ ነዉና...ከልምድ አንፃር አንድ ሰዉ ማስለም የፈለገ በጥረት የ5-7 አመት ትግል ያስፈልጋል
ሀይማኖት እኮ እንደ ስም በፍርድ ቤት ሂደህ በአንድ ወይ በሁለት ቀን የምትቀይረዉ ነገር አይደለም
ሀይማኖት መቀየር የህሊና ጦርተን ያለበት..ከቤተሰብ ከዘመድ ከወዳጅ የሚያራርቅ ከባድ ዉሳኔ ነዉ ስለሆነም የአሁን ሙስሊም በአንድ ወይ በሶስት ቀን የሚቀይሩ ስለሚመስለዉ አካሄድ አይችልም..እነሱን ከመወንጀል ከመከታተል ዉጭ እናም ይሄ መታረም አለበት በዚህ ቻናል ብዙ የማቃቸዉ የሌላ ሀይማኖት ተከታዮች ጋር ስለማቅ ስለምግባባ ጭምር ነዉ ፡፡
እናም መጀመሪያ ሁሉም ሙስሊም የኛ ጥርት ያለ ነዉ ማለት አንችልም የኑሮ ዉድነት እየመጣብን ያለዉ በተለይ በብዙ ስግብግብ ሙስሊም ነጋዴዎች መሆኑ አንዘጋ ይሄዉ ዘንድሮ ተምር 3000 ከዛም በላይ ገብቶ በካርቶን የለመድነዉ በኪሎ አፁመዉናል እኮ መታሰብ ያለበት ተምር የሚሸጡት 90% በላይ ሙስሊም ነጋዴዎች መሆኑን አንዘንጋ

እያየነዉ ባለዉ ተጨባጭ ከሌላ ሀይማኖት ሰልመዉ ወደ ኢስላም የገቡ ናቸዉ ለኢስላም እየሰሩ ያሉት...ሙስሊሙ የኢስላምን ፀጋ ስጦታ አላስተነተነዉም ግን የሰለሙ ትክክለኛ መሆኑን አረጋግጠዉ ቆርጠዉ ወደ ኢስላም ስለገቡ ቁርአን ቀርተዉ ሀዲስ ተፍሲር ቀርተዉ ሙስሊም ሁኖ የተወለደን እያስተማሩና ሌሎች ለመስለም ያልታደሉትን ወደ ኢስላም እየጠሩ እያስተማሩ እያሰለሙ እያየን ነዉ እናም አሁን ላይ በጣም ጭፍን ጥላቻ እነሱ ጋር ያለዉ አያስፈልግም ማስተማር እንጂ

እኛም ማወቅ ያለብን ነብዩ ሰዐወ አንድ ሰዉ እናንተን በባህሪ በሁሉ ነገር አይተዉ ለመስለም ጉጉት ካላደረጉ ኢማናችሁ ድክመት አለበት ብለዋል...የኛ ባህሪ ኢስላምን ይጣራል ወይ??



አሁንም በዚህ HIV+ ዙሪያ ገንቢ አስተያየት ካለ እቀበላሁ፡፡ሙሉ በሙሉ ችግሩን መቅረፍ ባንችል አንድ ወይ ሁለትም ቢሆን ትዳር ቢያገኙ ትልቅ ነዉና በተቻለን እንታገል እንረባረብ ...የነገን ማን ያቃል በጣም ከባድ ኬዝ ነዉ እናም  እስኪ HIV+ የሆኑትን ቀረብ ብላችሁ የተወሰነ ለመረዳት ሞክሩ እየሳቁ ብዙ የሚደብቁት ችግር የሙራል የሳይኮ ጉዳት ብቸኝነት ተስፋ መቁረጥ ተሸክመዉ ነዉ የሚዞሩት ወላሂ ብዙዎች ተስፋ የቆረጡ ናቸዉ

ከጎናቸዉ ልንሆን በሀሳብ ልንረዳቸዉ ይገባል ..ብዙዎች ሲወለዱ ከቤተሰብ ነዉ የሚይዛቸዉ ወደዉ ያልተቀበሉት በሽታ ነዉ እናም በሀሳብ ያለንን በመርዳት ትዳር በማፈላለግ ጭምር ከጎናቸዉ እንሁን

አስተያየት ለመስጠት
T.me/Aisuu_bot  T.me/Aisuu_bot
T.me/Aisuu_bot  T.me/Aisuu_bot
561 viewsedited  09:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-26 12:50:16 አሰላሙ አለይኩም ወራህመቱሏሂ ወበረካትሁ
እንዴት ናችሁ
             አሚር ሰይድ

    ከተወሰኑ ቀናቶች በፊት በተፓሰተዉ በHiv positive ያለባቸዉ ችግሮች እና እነሱ ትዳር እርስ በራሳቸዉ ለመገናኘት ከባድ ፈታኝ ችግር ስለሆነ በቻናል ላይ የጤና ባለሙያዎች እና ማንኛዉም ያነበበዉ ሙስሊም የራሱ ሀሳብ ካለዉ እና Hiv positive የሆናችሁ በአስተያየት መስጫ bot እንዲያሳዉቁኝ ሰፋ ያለ ፁሁፍ ፓስቼ ነበር
ከሞላ ጎደል ከአገሪቱ ወቅታዊ ጉዳይ አንፃር Data ስለተዘጋ በpisphon ብቻ ስለምንጠቀም በpisphon የማይጠቀምም ስላለ በተጨማሪም የተፓሰተዉ ረመዳን ሊገባ 10 ቀን ሲቀረዉ ስለሆነ በዚህ ቀናቶች ደግሞ አንዳንድ ወገኖች ረመዳንን ብቻ ሚዲያ አልጠቀምም ብለዉ የሚቶብቱ ስላሉ አላህ በዛዉ ከሚዲያ የሚጠፉ ያድርጋቸዉና እንደታሰበዉ ፁሁፉ ለብዙ ሰዉ ተደራሽ ባይሆንም ግን ከታሰበዉ እቅድ 55% ግብ ላይ ዉሏል

☞በአስተያየት ላይ ሰዉ በጣም ሰፊ ልዩነት ያለዉ እንደዉ ስለ Hiv አያቁም ወይ ያስብላል የሚሰጡት comment ደባሪ የሰጡ አሉ ምን ይባላል ጀሊሉ እዉቀትን ጨምርላቸዉ ከማለት ዉጭ.. ስድብም የሰደቡኝ ነበሩ እነሱ የማይጠቅም የማይጎዱ ስለሆኑ
ከቻናል ተጭረዋል መቀመጣቸዉ ቻናል ከማሞቅ ዉጭ ጥቅም የላቸዉም

☞ የተወሰኑ ወደ 5 comment ደግሞ Hiv ይለቃል የሚሉም አየሁ ይሄን እያዩ አንዳንድ ከተሞች ሰፈሮች የፈጣሪ ቁጣ እንጂ በሽታ አይደለም ብለዉ ራሳቸዉን ያሳመኑም አሉ ....
የለቀቀዉ ሰዉ ብሎ የነገሩኝ ግራ ገብቶኝ የጤና ባለሙያ ስጠይቅ አይለቅም ግን በሽታዉ ስለሚዳከም ስትመረመር ላያሳይ ይችላል ብለዉኛል እናም ይለቃል ብላችሁ ባይዳከሙ ባይ ነኝ፡፡ ግን አንድ አዲስ አበባ የተፈጠረ የማቃት ልጅ የነገረችኝ ገርሞኛል ግን መንገሩ ጥሩ ስለማይሆን በደንብ ማሰቡ ይሻላል

☞ በቻናል Hiv positive ራሳቸዉን ይፋ ያደረጉት ሴቶች ብቻ ሲሆኑ ..ግን ተማሪዎችም ስራ ላይ ያሉም የወለዱም አሉ ግን ፈጣሪ ይድረስላቸዉ 95% ተስፋ የቆረጡ ሁነዉ አግኝቻቸዋለሁ :: የተወሰኑትም ተስፋ ቆርጠዉ መድሀኒት እስከማቆም የደረሱ ነበሩ እነሱን በሶይኮ ማከምና እነሱን የስነልቦና ምክርን በመስጠት መድሀኒት በማስጀመርና ለወደፊት ህልም ሰንቀዉ ተማሪዎችም ተምረዉ እንደነሱ hiv+ የሆኑትን መርዳት እንዳለባቸዉ የተለያዩ ምክሮች ልምዶች በመስጠት እነሱን በፊት ካሉበት ዲፕሬሽን በማዉጣትና መድሀኒት ያቋረጡትን ደግሞ እንዲጀምሩ በማድረግ በቅርብ በመከታል 97% ተሳክቷል አልሀምዱሊላህ ለወደፊትም ከጎናቸዉ ሁኜ እከታተላቸዋለሁ

☞አንድ እንኳ ወንድ ማግኘት አልቻልንም..ይሄ ማለት
ብዙዎች ደብቀዋል ወይም ከኑሮ ዉድነት አንፃር አሁን ላይ ትዳር ለመመስረት ስለከበደ ሊሆንም ይችላል እናም ለማገናኘት የተለባለዉ ወንድ ማግኘት አልቻልንም....
የHiv+ group አለ እዛ ወደ 20 ወንዶች ነበሩ ግን ከወሬ የዘለለ ቁም ነገር የላቸዉም...እነዚህን አግቡ ማለት ስስ የሆነ የሴት ልብን መጉዳት ነዉ፡፡ ለምን ብዙ ሴቶች በዚህ ኬዝ ያሉ እዉነት ስለሚመስላቸዉ የትዳር ፕሮሰስ ተጀምሮ ቢያፈገፍጉ የሴቱ ልብ ይጎዳል ከዚህ አንፃር ለማግባት የነየተን እንጂ እኔም የዚህ ኬዝ ካላት ጋር ወሬ ብቻ የሚወራን ማገናኘቱ ለሴቶቹ ጉዳት መጨመር እንጂ ጥቅም ስላልታየ ትተነዋል

☞ አዲስ አበባ ላይ መድሀኒቱን የሚሰጠዉ የጤና ባለሙያዉን ለማማከር በየጊዜዉ ይቀያየራሉ ብለዉኛል ይሄ ትንሽ ለማማከር ይከብዳል ግን ከአዲስ አበባ ዉጭ ያሉ ከተሞች መድሀኒቱን የሚሰጠዉ  አንድ የጤና ባለሙያ የተወሰኑ ወራቶች እስከ አመታትም ስለሚቆይ ብታማክሩ አሪፍ ነዉ መፍትሄ ግብ ላይ መድረስ ግዴታ ስበብ ማድረስ ስለሚያስፈልግ፡፡ Hiv+ ስለትዳር ሲታሰብ የመጀመሪያ ዉሳኔ መሆን ያለባቸዉ የጤና ባለሙያ ማማከር መሆኑን አንዘጋ...ግን የወሰኑ ሴቶች የጤና ባለሙያ ስናማክር የምናገኘዉ እድሜዉ ከ40 በላይ የሆነ ነዉ ያሉኝ አሉ በዚህ በእድሜ የተነሳ እንዳላገቡ ነግረዉኛል፡፡ይሄ በኔ የሚወሰን አይደለም ትዳር የፍላጎት ምርጫ ስለሆነ ገብቶ ከመጨቃጨቅ ከመናናቅ የሚወዱትን መስፈርታቸዉን የሚያሟሉ  ማግባት የራሳቸዉ ምርጫ ስለሆነ በእድሜ የገፋ አግቡ ብየ ማስገደድ አልችልም....
ፈጣሪ ያሰባችሁትን ያሳካለችሁ ከማለት ዉጭ


☞ አዲስ አበባ AHF Addis clinic /kolfe clinic የሚባል ለም ሆቴል አካባቢ አለ HIV positive ለሆኑ ሰዎች ትዳር ያገናኛሉ ብለዉኛል ይሄ የኮሚሽን ግን ይቀበላሉ ብለዉኛል እንደ አማራጭ ይያዛል


☞ለታዋቂ ሰዎች ማድረስ በሚለዉ ደግሞ ለተለያዩ ፀሀፊዎች ለተለያዩ ኡስታዞች የትላልቅ ሚዲያ ባለሙያዎች በማድረስ ከአንድ በኔ ሀሳብ በምትሄደዉ የዲን እህቴ ጋር በመናበብ 80% ያሳወቀን በዚህ ዙሪያ የቻሉትን እንዲሰሩ ታገለን ነበር ያዉ የዘንድሮ ሙስሊም ከኢንሻ አላህ ዉጭ የሚሰራ የለም ኢንሻ አላህ ብለዉ ዘግተዉናል
የአሁን ብዙዉ ሙስሊም ኢንሻ አላህ ብሎ ወደ ግራ የሚሄድ ነዉ ምንም ማድረግ አልችልም በተቻለን አላህን ይዘን መታገል ብቻ ..አሁን ላይ ከዳኢዎች ከኡስታዞች ጥሩ ምላሽ መጠበቅ ከብዷል አላህ ለዚህ የዋህ ሙስሊም ኡማ ይድረስልን

☞ አንድ ብቻ ሙስሊም ወንድም የጤና ባለሙያ ሙስሊሞችን Hiv+ የሚያገናኝ አለ ግን አሁን ረመዳን ነዉ ከረመዳን ቡሀላ ብሎኛል ፡፡ ግን ከአገናኘሁ ቡሀላ እየተጣሉ እየተፋቱ ተቸግሪያለሁ ለምን ይሁን ይሁን ችግር የለም በሚል ከተጋቡ ቡሀላ ብዙዉ ሳይግባቡ ስለሚጋቡ ሲግባቡ ችግር እየመጣ በጣም ተቸግሪያለሁ አለኝ...እናም ከረመዳን ቡሀላ ብሎኛል እናም እዚህ ያላችሁ
Hiv + የሆናችሁ የቻናል ቤተሰቦች ፈርታችሁ ያልተናገራችሁ በዚህ bot አሳዉቂኝ የእሱን ስልክ ቁጥር እሰጣችሆለሁ በዚህ bot ያሳዉቁኝ

T.me/Aisuu_bot  T.me/Aisuu_bot
T.me/Aisuu_bot  T.me/Aisuu_bot

☞  የተቸገሩን ኸይር መስራት የፈለገ Hiv+ ሆነ ከዛ ዉጭ ያሉ መርዳት የሚፈልግ ካለ እኔ ችግረኞችን በስልክ ወይ በtg acount አገናኛችሆለሁ ራሳችሁ መርዳት የምችሉበትን አመቻችላችሆለሁ ...እኔ ሚዲያ ላይ የማቃቸዉ በጣም ብዙ የተቸገሩ አሉ በራሴ አቅም የቻልኩትን ባደርግም ግን ብዙ ከአንድ ሰዉ አቅም በላይ ነዉ እናም ኸይር መስራት የሚፈልግ የተቸገረዉን እኔ ላገናኛችሁ ችግሩን ሁኔታ ራሱ ያስረዳችሆል የምረዱትን ቀጥታ እነሱ ጋር ማገናኘት እችላለሁ የመርዳት ንያዉ ያለዉ በዚህ bot ያሳዉቀኝ

T.me/Aisuu_bot  T.me/Aisuu_bot
T.me/Aisuu_bot  T.me/Aisuu_bot

☞ደግሞ በተሻለ መልኩ የክርስቲያን ሀይማኖት የሰጡት ገንቢ አስተያየት ነበር እነሱን ሳላደንቅ አላልፍም...አሁን ላይ እነሱ ይሰራሉ ለሀይማኖታቸዉ ደስ ይላሉ እኛ ግን እነሱ ሰሩ ቦታ ተቀበሉ ብሎ ጫጫታ ነዉ ለእምነታቸዉ የመስራት ፈጣሪ ብለዉ ከያዙት ግዴታ ስለተሰጣቸዉ ይሰራሉ ሰሩ ብሎ እርይ አያዋጣም ይልቅ እኛ ኢንሻ አላህ እያሉ ከመሹለክ እንደ እነሱ ተናቦ መስራት ያዋጣል፡፡ እናም ከልምድ አንፃር ለሰጣችሁኝ አስተያየት ጥቆማ ከልብ አመሰግናለሁ፡፡
537 views09:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-26 12:48:54
ሴትነት ምንድን ነዉ?

ኡስታዝ ኑሩ ቱርኪ
490 views09:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-08 06:25:22 Page ➌
የሙስሊም ተቋም መጅሊስ ተስተካክሏል ካልን እንደዚህ የኡማዉ አንገብጋቢ ጉዳይ ፈልፍለዉ አዉጥተዉ የተቀናጀ ስራ ቢሰሩ ለዚህ ዘላቂ መፍትሄ ማምጣት ይችሉ ነበር...መጅሊሱ ከበፊቱ የተሻለ ስራ እንዲሰሩ ይሄንን ብታሳዉቋቸዉ ጥሩ ነዉ ባይ ነኝ



☞ አንዲት ደሴ የማቃት Hiv ያለባት የተሰቃየችዉን ስቃይ ሙሉ በሙሉ አቃለሁ በአካል ትነግረኝ ነበር ግን አልሀምዱሊላህ አዲስ አበባ እንደሷ ኬዝ ያለባት አግብታ የሶስት ልጅ እናት ሁናለች
አሁን ዘመኑ ተሻሽሏል የሚወለዱት ልጆች Hiv አይኖርባቸዉም በሀኪም ክትትል ስለሚወልዱ ..የእሷን ታሪክ ፅፎ ማቅረብ ይቻል ነበር ግን ጊዜ የለም ፅፎ ማዘጋጃ...,በጣም አሳዛኝ አስተማሪ ነዉ እኔን ትነግረኝ ነበር የሰፈሬ ልጅ አብሮ አደጌ ነበረች አብረን ስለአደግን የሚገጥማትን ትነግረኝ ነበር የአሁን ወንዶች መቼም ግማሹ ለትዳር ግማሹ ለስሜት ስጠይቃት የምታሳልፍበት ጥበብ የተለየ ነበር ግን በጣም ተሰቃይታ ነበር ግን ጀሊሉ ጋር የነበራት ቁርኝት የተለየ ነበርና አዲስ አበባ አግብታ ጥሩ ኑሮ እየኖረች ነዉ አልሀምዱላላህ እሷን ያገናኛት አዲስ አበባ የሚኖር ይሄን ኬዝ የሚያቅ አጎቷ ነዉ

Please የትችት ብቻ ሳይሆን የመፍትሄም ሀሳብ አፍላቂ እንሁን ..በፊት ፁሁፍ በማዘጋጅበት ጊዜ ከአቅም በላይ የሆነ  በጣጣጣም ትችት አስተናግድ ነበር ሰዉ የሚሰራን አያስተናግድም
የአሁን ዘመን ትዉልድ የኢንሻ አላህና የአላሁ አክበር ትዉልድ ነዉ....ለዲነል ኢስላም በቻልከዉ ስራ ሲሉት ኢንሻ አላህ ..ከዛ በጀመአ ወይ በመስጊድ ተሰብስቦ የሆነ ነገር ተሰራ ሲባል ተክብር አሏሁ አክበር ብሎ የሚሄድ እንጂ የሚሰራ 0.001% ነዉ ...የሚሰራን የሚተች ደግሞ 99.9% ነዉ፡፡
በፊት አስታዉሳለሁ ታሪክ ሳዘጋጅ ብዙ ቁርአን ሀፊዞች የአንተን ታሪክ ስናነብ ቁርአኑ እየጠፋን ነዉ እያሉኝ በጣም ግራ ገብቶኝ ነበር  እንዴት ቁርአኑ እስከምጥፋት ደረሱ?? ብየ..የአሁን ዘመን ሰዉ ሽንፈቱን የበታችነቱን የኔ
ጥፋት ነዉ ብሎ አያስብም በሰዉ ላይ መለጠፍ ይወዳል እናም የመፍትሄ ሀሳብ እንጂ ሽንፈትን ወደ ሰዉ በማላበክ ጥገኛ ባንሆን መልካም ነዉ...

አሁንም መፍትሄ አመንጭ እንሁን  ይሄ የHiv ኬዝ ከባድ ኬዝ ነዉ በኢንሻ አላህ የሚታለፍ አይደለም ብዙዎች ሀይማኖታቸዉን እየቀሩ ነዉ.. እንቅፋት ሳንሆን በዚህኳ የመፍትሄ ሀሳብ እናመንጭ

እናንተ Hiv ቢኖርባችሁ ትዳር ብትፈልጉ ምን ታደርጋላችሁ?? አስተያየታችሁን በዚህ bot ጀባ በሉን
T.me/Aisuu_bot  T.me/Aisuu_bot
T.me/Aisuu_bot  T.me/Aisuu_bot

አስተያየት ስትሰጡ ለምን ፁሁፍ አታዘጋጅም --ጠፍተሀል -- ቻናሉ ሰዉ እየቀነሰ ነዉ --ወደ ሚዲያ መቼ ነዉ የምትመለሰዉ ምናምን እንቶ ፈንቶ የሆነ አስተያየት አትፃፉ አልቀበለም..ተወስኗል ወደ ሚዲያም አልመለስም ታሪክም 100% ሁኜ ልንገራችሁ አላዘጋጅም የራሴ የሆነ እኔዉ ብቻ የማቀዉ አሳማኝ ምክንያት አለኝ ...አስተያየት የምትፅፉት ዛሬ ላይ በአነሳሁት ስለ Hiv ኬዝ ላይ ብቻና ብቻ ነዉ፡፡

ስሙኝ ወገን እኛም ቢሆን ተመርምረን እራሳችንን ተመርምረን ብናቅ ጥሩ ነዉ..ቆየትም ቢል ተመርምረን የምናቅ ይኖራል ያልተመረመርንም ይኖራል
አይታወቅም የአላህ ነገር በአመት በሁለት አመት ልዩነት ምን እንደሚፈጠር አናቅም ...ይሄኔ ራስን አዉቆ የህይወት ግብ መቅረፅ ያስፈልጋል በተለይ በትዳር ዙሪያ ላይ

   አሁን አስቸኳይ ጉዳይ ገጥሞናል ስለዚህ Hiv ኬዝ ብቻ እናዉራ ሀሳብ አስተያየታችሁን በዚህ bot ይላኩልኝ ቀጥታ ለኔ ይደርሰኛል
እኔም ይሄን ሀሳብ ላመጣዉ ልጅ እና በሀሳብ እኔን ከሚጋሩ ቤተሰቦች የላካችሁትን አስተያየት እልከዉና ተወያይተን ሀሳብ ላይ  እንደርሳለን

በፊት ትዳር አገናኝም የምትሉም ነበራችሁ አደራ እኔ ማንንም አሁን አምኜ አግባዉ አግቢ ብየ ሀላፊነት አልወስም...እኔ  የምላችሁ ሰዉ የሚወዱትን የሚያፈቅሩትን አያገባም አርባ አራት ነጥብ ለምን አላህ ዱንያ የደስታ ምንጭ አይደለችም አላህ የትንኝ ክንፍ ያህል ቦታ የላትም ብሎ ነግሮን ከዱንያ ደስታን አጋኛለሁ ማለት ራስን ማሞኘት ነዉ፡፡ የሚወዳዱ የሚፋቀሩ  አይጋቡም ፡፡አፍቃሪ ማለት ከመጥፎ እድሉ ዉስጥ ደስታን የሚፈልግ ሰዉ ነዉ፡፡....ማፍቀር አንዱን ትዳርን ከሚከለክሉ ነገሮች ናቸዉ ..አጭተህ የሌላ ሁነህ እንኳ ፍቅሩን ልረሳዉ አችልም ልብህ ሌላ ቦታ ስሜትህ አገባሀት ጋር ሁኖ ልትቸገር ትችላለህ፡፡ አንዳንዴ ልቤን ከአሁን ቡሀላ አልሰጥም የሚሉ አሉ ልብ አንዴ በፍቅር ከተለያየዘ ያ ልብ እንዴት ተብሎ ነዉ ጡሀራ ሁኖ ለሌላ የሚሰጠዉ???
እናም አሁን የፍቅር ዝባዝንኬ አቁሞ ቀጥታ ማግባት ፍቅሩ ከዛ ቡሀላ ይመጣል ፡፡ በፍቅር ተይዘህ ተይዘሽ ያ ንፁህ ልብ ትዳርን ሊፈራ ይችላል የሚሻለዉ አግብቶ አብሮ ሁኖ የትዳር አጋርን መድሀኒት የሚወለዱ ልጆችን ያ የተጎዳን ልብ በልጆች በትዳር አጋር ፍቅር ማከም ብቻ ነዉ፡፡ ማወቅ ያለባችሁ አሁን ትዳር ሲያዝ ሴቶም ወንዱም ያሳለፈዉ ያልተሳካ የፍቅር ጉዞ ይኖረዋል ...ያለፈዉን ለወደፊቱ ችግር እንዳያመጣ አርጎ ዘግቶ
ትዳርን እርስ በርስ በመቀናጀት ህክምና ማድረግ ነዉ፡፡ ዘመኑ ገና 4 -8 ክፍል ያሉ ሴት ተማሪዎች ስለፍቅር በሚያወሩበት ዘመን ወደ ትዳር ወሬ ስጀምር ከአሁን በፊት ፍቅረኛ ነበረሽ ወይ እያልክ አጠይቅ፡፡ የሚሻለዉ ያለፈዉ አልፏል ስለወደፊቱ እናዉራ ብለህ አሁን ላይ የጠፋዉ እንደ ወንድ የሆነ ወንድ እንጂ ተራ ወንድ ነፍ አለ ሀቢቢ ስለሆነም ትዳር አገናኘኝ በፊት ጀምሩ የምትሉ ይሄ ጉዳይ እንዳይነሳ

   ወደ ላይ የተወረወረ ሁሉ ተመልሶ መምጣቱ እንደማይቀር ሁሉ በሰዉ ልጅ የህይወት ሂደትም ዉስጥ መሄድና መመለስ ያለ ነገር ነዉ..ወደ ሰማይ የወረወርከዉ ዲንጋይ ተመልሶ መጥቶ ከምድር ላይ በማረፉ መጨረሻዉ ነዉ ብለህ አትሰብ ብትፈልግ ዳግም አንስተህ ልትወረዉረዉ የምትችለዉ ነገር ነዉና ወደ ላይ መዉጫዉ ሆነ ወደ ታች መዉረጃዉ መንገድ አንድ ነዉ
እናም ህይወት ቋሚ አይደለችም ፍቅር ቋሚ አይደለም ሄድ መለስ ነዉ የሚለዉ እናም ህይወትህን ትዳርህን ማስተካክል የምችለዉ አንተ በእጂህ እንጂ በእድል በቁዘማና በማይለቅ ትዝታ አይደለም፡፡የሞተን ፍቅር ማቀፍ የዛሬን የነገን ህይወት ማበላሸት ነዉ
እናም ትዳር የአንቺ ወይ የእሱ ከዛ አንድ ላይ ስትሆኑ የእናንተ የእጅ ስራ ዉጤት እንጂ አንዴ ሳይሳካ ሲቀር የመጨረሻ ነዉ ብለን አንሰብ ፈጣሪ የተሻለ አለዉና

>>>>ግን Hiv ያለባችሁ የእናንተን ኬዝ ስራየ ብየ እስከመጨረሻዉ ድረስ በስልክ በtg የአቅሜን ከአቅሜም ለመስራት ወስኛለሁ ሌሎችም Hiv ያለባቸዉ ታማኝ  group ያላቸዉ ዲነኞች አንድ ወንድሜ እና እህቴ ጋር ለመስራት ስለወሰንኩ በአላህ ፍቃድ በቻልነዉ አቅም እንሰራለን
አደራ በአላህ ስም ይዣችሆለሁ አንብባችሁ እንዳታልፉ አስተያየት ስጡ አደራ ይሄ ሀሳብ ልፓስተዉ ስል በአገራችን ጉዳይ Data ሲቋረጥ ተዉኩት ሙሉ በሙሉ ሰዉም ባይገባ በSafaricom እና በpispon
እየተጠቀመ ስለሆነ ነዉ የፓሰትኩት

እናም አስተያየት ለመስጠት
አስተያየት ለመስጠት
T.me/Aisuu_bot  T.me/Aisuu_bot
T.me/Aisuu_bot  T.me/Aisuu_bot
662 viewsedited  03:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-08 06:24:02 Page ➋
አንዷ ከተማዉ ለጊዜዉ ይቆይ እዚህ ቻናል ልትኖር ስለምትችል  Hiv አለባት ቤተሰብም Hiv እንዳለባት ያቃሉ ትዳር በጣም በብዛት ይመጣል ትምህርት እየተማረች ነዉ ለሚመጣዉ አመት ትመረቃለች..ትዳር ይመጣል ሁሌ አልፈልግም እያለች ትመልሳለች ..ስትነግረኝ አልቅሳ ነዉ የነገረችኝ
ማግባት አልፈልግም እያልኩ እየመለስኩ ነዉ ግን በቃ በጣም ተቸገርኩ...ወንዶች ሲቀርቡኝ እየሸሸሁ ነዉ
በቃ እንጃ ህይወት ከብዶኛል ብላ ነግራኛለች ብሎ አጫወተኝ ..ሚስጥር ስለተደበቀ ነው የዚች ልጅ ሀገር የት እንደሆነ እኔ አቃለሁ በፁሁፍ ሀገሯን መግለፅ ስላልፈለኩ ነው

የሌላ ታሪክ ደግሞ ልንገራችሁ  በልጅነቷ አባት እናቷ በዚሁ ኬዝ ሙተዉ እሷ ቅርብ ቤተሰብ ጋር እየኖረች ነዉ እናም
በቃ ህይወት ፈተና ነዉ የሆነባት ለምን ትዳር እንደመጣ ማግባት አይቻልምና ብላ ይሄዉ ቀን ማታ እያለቀሰች ነዉ እንደዉም ህይወት መረረኝ ጀሊሉ ለኔ ምነዉ ሞት በላከልኝ እስከምትል ድረስ ...የዚችንም ልጅ ሀገር አቀዋለሁ ሚስጥር ለመደበቅ ነው

እናም አሚር ሰይድ እባክህ አንተ እንደተዋቂነትህ የተወሰነ መላ በል...በአንተ ጥረት Hiv ያለባቸዉ ተገናኝተዉ ቢጋቡ አንተ ከአላህ የምታገኘዉ አጅርና የተጋቡትን ሰዎች ደስታ እሰብና አንተ እንደምንም መፍትሄ ስጥ በተለይ ወንድ በተለያየ ስራም ቢዚ ይሆናል ስንት በሆዳቸዉ አፍነው የሚኖሩ ሴቶች አሉ እኔ ብዙ የማቃቸዉ  አለኝ ይሄን ሀሳብ ያመጣዉ ልጅ


እናም ይሄን ፁሁፍ ያነበባችሁ ሁሉ ለኔ ከባድ አማና
ተጥሎብኛል እኔም ለአላህ ብላችሁ ያነበባችሁ ሁሉ አማና አማና አስተያየት ስጡ ለምን ከእናንተ መሀል የትኛዉ የተሻለ ሀሳብ እንደሆነ አይታወቅምና እናም
በተጨማሪም አስተያየት ለመስጠት በዚህ bot ይላኩልኝ

T.me/Aisuu_bot  T.me/Aisuu_bot
T.me/Aisuu_bot  T.me/Aisuu_bot

ግን እኔ በራሴ አንድ ሀሳብ አለኝ
ይሄ ጉዳይ ተደፋፍኖ እንዳያልፍ ማግባት የምትፈልጉ HIV positive የሆናችሁ ይሄ ያማከረኝ ልጅ የHiv positive የሆኑ ብቻ group አለዉ ግን በgroup በእድሜ በሀገር ትዳር ስለሆነ በአስተሳሰብና በኑሮ ደረጃ የተለያዩ ስለሆኑ በእኔ ቻናል ያሉና ሀሳቡን የሚረዱ ካሉ እኔ እዚህ ልጅ ጋር ሁኜ የዚህ case ያለባቸዉ group ከፍተን በጥንቃቄ በSecurity
በሀላሉ ወደ ትዳር እንዲገቡ ለማድረግ አስቢያለሁ፡፡
ደግሞ group ዉስጥ ያሉት በዲን ጠንካራ ሀላል ፈላጊ ናቸዉ እኔ ከዚህ ቻናል ካለ ሀላፊነት እራሴ ወስጄ ከሚፈልጉት ጋር ላገናኛችሁ
በጣም ከባድ ኬዝ ነዉ ግን በቃ የታየኝ ለኔ በዚህ ቻናል ዉስጥ HIV ያለባችሁ ካላችሁ እና የምታቁት ትዳር ፈላጊ ካለ በዚህ bot አሳዉቁኝ
T.me/Aisuu_bot  T.me/Aisuu_bot
T.me/Aisuu_bot  T.me/Aisuu_bot


በተጨማሪ ከኔ የተሻለ ሀሳብ ያላችሁ በተለይ በዚህ ቻናል ላይ ያላችሁ የህክምና ባለሙያ የስነ-ልቦና ባለሙያ ነርሶች ወይም የዩኒቨርስቲ መምህራን ወይም የዩኒቨርስቲ ሜድስን ወይ ፋርማሲ ተማሪዎች ካላችሁ ከልምድ አንፃር ሀሳብ አስተያየት ብታካፍሉኝ በጣም ደስ ይለኛል ..እባካችሁ ይሄ ለብቻ የሚሰራ አይደለም በመወያየት ከአንዱ አንዱ ሀሳብ ተሽሎ ዘላቂ ለዉጥ እናመጣ እንችላለንና

በዚህ bot አስተያየት ይላኩልኝ
T.me/Aisuu_bot  T.me/Aisuu_bot
T.me/Aisuu_bot  T.me/Aisuu_bot

በነገራችን ላይ በአላህ ስም ይዣችሆለሁ ይሄን ፁሁፍ ያነበበ ሁሉ የተወሰነ ቀንም ቢሆን አስቦ ከተለምዶ ወይ የሰማዉ ታሪክ ካለ ወይ የተሻለ ሀሳብ እንዲነግረኝ እፈልጋለሁ

ለማንኛዉም Hiv ያለባችሁ ትዳር የምፈልጉ
☞ስም
☞የምትኖሩበት ከተማ
☞ የትዳር መስፈርታችሁን
በዚህ bot አሳዉቁኝ
T.me/Aisuu_bot  T.me/Aisuu_bot
T.me/Aisuu_bot  T.me/Aisuu_bot

>>> ይሄን ሀሳብ ያነሳዉ  ዲነል ኢስላም ያስተዋወቀን ወንድሜ እሱም ትዳር ፈላጊ ነው ከአገሩ ሙስሊም አላገኘም
☞የእሱ ሀገር ይቆይ ለጊዜዉ ግን ለትዳር ፈላጊዋ እነግራለሁ በቻናል ሚስጥር አይወጣም
☞የራሱ የሆነ ስራ አለዉ
☞በዲኗ ቁርአንና ኪቲብ የቀራች ይመረጣል፡፡
በዚህ Bot አሳዉቁኝ

T.me/Aisuu_bot  T.me/Aisuu_bot
T.me/Aisuu_bot  T.me/Aisuu_bot

ሴቶችም አትፍሩ እኔ አገናኛችሆለሁ ሚስጥር 100% ይጠበቃል

በተጨማሪ ደግሞ ዉጭ ሀገር ያላችሁ  አሜሪካ አዉሮፓም አረብ ሀገርም  አፍሪካም ዉስጥ  ካላችሁ የዚህ case ያለባችሁ ከእዛም የሚፈልግ ስላለ ማገናኘት እችላለሁ ....ብቻ ማንኛዉም ወንድም ሴት Hiv ያለባችሁ ትዳር ማግባት የምፈልጉ እዚህ ቻናል ያላችሁ ወይ የምታቁት ካለ በዚህ bot አሳዉቁኝ
☞ T.me/Aisuu_bot  T.me/Aisuu_bot

ሀሳቤን ጠቅለል ሳረገዉ  አላህን የሚፈሩ Hiv ያለባቸዉ የኢስላም ወንድም እህቶቼ በጣም እየተቸገሩ ነዉ ..የሌሎችም ሀይማኖት ተከታዮች እንደዚሁ በጣም ይቸገራሉ፡፡
በተለያዩ group ሙስሊሞች Hiv ኬዝ ያለባቸዉ ትዳር ሲያገኙ ሀይማኖታቸዉን እየቀየሩ ነዉ

እኛስ የነገን ማን ያዉቃል?? ምን መፍትሄ እናድርግ???  ማሰብ አለብን ..ሀሳቡን አንሸራሽሩት ለጓደኛ ለቤተሰብ ሳይቀር ትምህርት ቤት በተለያዩ ጀመአዎች ስብሰባዎች ሳይቀር

እስኪ ታዋቂ ፀሀፊያን ጋር እባካችሁ አድርሱት ለምሳሌ እኔ እነ ፉአድ ሙና እነ አብደል ሀኪም አሰፋ እነ ነጃት ሀሰን እነ ፋይሰል አሚን  ወዘተ ታዋቂ ፀሀፊያን እና ሰዎች ጋር አድርሱት እና በዚህ ጉዳይ ላይ ቢሰሩና መፍትሄ ሊፈጥሩ ይችላሉ በተለይ ፉአድ ሙናን የምትግባቡት ካላችሁ አስረዱት ለምን እሱ በሚዲያ ላይ ስላለ ተፅእኖ ይፈጥራል
ለፉአድ ሙና በዚህ ጉዳይ group ከፍቶ ይሄን ችግር ቢቀርፍ ጥሩ ነዉ እኔ ይሄ የራሴ ሀሳብ ነዉ
እኔ ለራሴ ተዋዛግቤ የምኖር ሰዉ ነኝ እንደነሱ መፍትሄ ሀሳብ መፍጠር ይከብደኛል እናም ማንም ጋር ስለማልግባባ በራሴ መስመር ብቻ ነዉ የምሄደዉ ግን ሌሎች ፀሀፊዎች አንዳንድ ላይ ተናበዉ አስበዉ ስለሚሰሩ ሀሳቡን አቅርቡላቸዉ ይሄ ግዴታም ጭምር ነው
☞ ወይም Mimber tv ሴቱንም ወንዱንም በማቀላቀል በማዉራት ብዙ ስራ ስለሚሰሩ ጥርት ያለ
ለትዉልድ የሚያስቡ ከሆነ ይሄን በሀሳብ ደረጃ አቅርቡቡላቸዉ በዚህ ላይ ቢሰሩ ..Minber ያልኩት እነሱን ደግፌ ሳይሆን ሰዉ ብዙ ጊዜ የሚጠቅመዉን ስለማያቅ ወደ እነሱ tv ትኩረት ስለሚያደርግ በዛ
እነሱ ሚስጥር ደብቀዉ ቢያገናኙ ብየ ነዉ አንዳንድ ሚዲያ ብንጠላም ግን ይሄን ቢሰሩ ኸይር ነዉ..ይሄን ያነበባችሁ እንደ አስተያየት ስጧቸዉ
☞Nisiha tv በዚህ ጉዳይ ቢሰሩ ወይም የምትግባቡ ካላችሁ ሙራድ ታደሰን ሀሳቡን ሰጥታችሁት ይሄን ከNiseha tv ከነኡስታዝ ኤልያስ አህመድ ጋር ቢሰራ ዘላቂ መፍትሄ የሚገኝ ይመስለኛል
እናም በቻላችሁ አቅም ሁላችንም የኢስላም ሀላፊነት አለብን ይሄም አንዱ ግዴታችን ነዉ እናም የመፍትሄ ሀሳብ አመንጭ እንሁን ብዙ Hiv ያለባቸዉ ወንድም እህቶች እየተቸገሩ ነዉ...ይሄ በደንብ ቢሰራበት የሌላ ሀይማኖት ተከታይ Hiv ያለባቸዉ ለራሱ ከእኛ አልፈን እንጠቅማቸዉ ይሆናልና ..በጣም አስቡበትና ወደ መፍትሄ እንሸጋገር ተመካክረን
584 views03:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-08 06:22:54
በአላህ ያነበባችሁ ሁሉ አስተያየት ስጡ ለምን የአንዳችሁ መፍትሄ ሀሳብ ሊሆን ይችላልና አደራ
    አሚር ሰይድ

አሰላሙ አለይኩም ወራህመቱሏሂ ወበረካትሁ
አሚር ሰይድ እንዴት ነህ??
ፍቃደኛ ከሆንክ አንድ ነገር ላማክርክ ነበር ማለትም እንደ አስተያየትም ጭምር ነው ለምን የብዙዎች ሙስሊሞች ችግር እኔ በድፍረት ላወያይህ ነዉ

    እኛ ሙስሊም ወንድም እህቶቻቹ የምንችገርበት አንድ ነገር አለ እኔ ለምሳሌ Hiv postive የሆነዉ ትዳርም ወይም እጮኛ ለመያዝ እንቸገራለን፡፡ሴቲቱም Hiv ካለባት ትዳር ለማግኘት በጣም ትቸገራለች ...ምክንያቱም እንደ ነሷራዎች አይደለም እምነታችን  በቻልነው አቅም እንከታተለን ልክ እኛው አይነት ተመሳሳይ አቂዳ ወይም ሸሪዓው አይነት ነገር የሚከተል ሰው ልንፈልግ እንችላለን ያው ትዳር ነውና እናም ያንን ነገር ግን እኛ ማድረግ አንችልም b/c እንደማንኛው ሰው ኢማን አላት ብለክ የምታጨው አይደለም postive ይሁን አትሁን ምታውቀው ነገር የለም ለመጠየቅ ስለምንፈራ ሙስሊም ላታገኝ ትችላለክ ፡፡ ያው ሀሳቤን ትረዳዋለክ ብዬ አስባለው ያው በፁሁፍ ለመግለፅ ትንሽ ይከብዳል መሰለኝ እና አንተ ታሪክ በመፃፍ ታዋቂ ነህ ብዙ ሰዉ ተከታይም አለህ ...አንተን እኔም ስለማምንህ ሌሎች እንደሚያምኑህ አልጠራጠርም  በቻናልህ ላይ ይህ አይነት ኬዝ ያለባቸው ኑረዉ ለሰዉ መንገር ፈርተዉ በሽታቸዉን ደብቀዉ ላያገቡ ይችላሉ...እኛ Hiv positive ያለብን የምንገናኝበት  ጠባብ ነው እና አንተ በዚህ  ኬዝ ላይ ሚስጥራዊ ግሩፕ ከፍተክ ይሄን ነገር ብትቀርፍልን ባይ ነኝ ከሌሎች አንተን አምነሀለሁ አሚር ሰይድ  ይሄን ጉዳይ ለተወሰኑ ታዋቂ ሰዎች ነግሬ መፍትሄ አላገኘሁም ግን አንተ ከሌሎች ትሻላለህ ቶሎ ሀሳብን ተረድተህ መፍትሄ እንደምታመጣ እተማመንብሀለሁ

መልስህን እጠብቃለሁ አሚር ሰይድ ወሰላሙ አለይኩም



ወደራሴ ሀሳብ ስመጣ
ወላሂ ቢላሂ ይሄን አስተያየት ልጁ የላከልኝ ከዛሬ 6 ወር በፊት ነበር  ምን ማድረግ እንዳለብኝ ግራ ገባኝ ..ከዛ አስተያየት ለሰጠኝ ቢያንስ የተወሰነ ቀን ስጠኝና ልሰብበት ነበር መልሴ ...ይሄዉ እሱም ጋር ስንደዋወል ስናወራ ስለሁኔታዉ ሲያጫዉተኝ 6 ወራትን አለፍን

አስባችሁታል እስኪ ራሳችንን   Hiv positive እንዳለብን አርገን እንሰበዉ .
☞ ትዳር ላግባሽ ብሎ ሲጠይቅሽ ወይ በቤተሰብ ቢመጣ ምን ይሰማናል ምን ይሆን መልሳችን??አይከብድም
☞ አባትሽ እናትሽ ዛሬ የማመልሽዉ እምቢ የማትይበት ትዳር መጥቷል ይሄን ያመጣሁልሽን ታገቢያለሽ እምቢ ካልሽ ከአሁን ቡሀላ አባቴ ብለሽ እንዳጠሪኝ ወይ እናቴ ብለሽ እንዳጠሪኝ ያመጣንልሽን ታገቢያለሽ ቢሉሽ እናት አባትሽ አንቺ Hiv አለብሽ
ቤተሰቦችሽ አያቁም
ለእናት አባትሽ ምን ብለሽ ትመልሻለሽ አይከብድም????
☞ ወይም የሰዉ ልጅ ነሽ ፍቅር ቢይዝሽ ያን ልጅ ትወጅዋለሽ ግን የእሱ መሆን አትችይም Hiv አለብሽ እሱን እወድሀለሁ አንተ ጋር መኖር እፈልጋለሁ ግን Hiv አለብኝ ትይዋለሽ?? በጭራሽ አትይዉም ይከብዳል
☞ እኔ እራሴን Hiv positive አድርጌ ልሰብ እስኪ አንተም የምታነበዉ Hiv አለብህ እንበል ትዳር ማግባት ፈለክ ወይም ልጅቷን ወደድካት ከዛም  አወረሀት ብዙ ነገር ተግባባችሁ  Hiv አለብኝ  አንቺስ ብለህ መጠየቅ ትችላለህ???አየህ አትጠይቃትም እኔም እኔ Hiv ቢኖርብኘ  አለብኝ አልልም ለምን ከዚህ ከማይረዳ ማህበረሰባችን አንፃር ይከብዳልና፡፡
☞ቤተሰቦችህ ትዳር መርጬልሀለሁ ይቺን ልጅ አግባ ብለዉ አማከሩህ ይቺን ልጅ የማታገባ ከሆነ እኔና አንተ አባትና ልጅ አይደለህም ብትባል
ልጂቱን ወደሀታል ግን አንተ Hiv አለብህ እንዴት ታደርጋለህ??? አይከብድም

በዚህ መጥፎ ዘመን አንዳንዶች HIV ሲገኝባቸዉ በበቀል የሌለባቸዉን ለማስያዝ የሚያደርጉትን ጥረት እየታዘብን ነዉ...አንዳንዶች Hiv በደማቸዉ ሲገኝ girl frind ይይዙና አላህ በከለከለዉ ዚና አማካኝነት እንደነሱ Hiv አስይዘዉ ሲያገቡ እያየን ነዉ ..ሴቶችም Hiv ሲገኝባቸዉ ወንዱን በማስያዝ ሲጋቡ እያየን ነዉ ግን ይሄ ወንድሜ አላህ የሚጠላዉን የከለከለዉን አልሰራም የሴቶች ህይወት አላበላሽም ግን እንደኔ Hiv ያለባት ዲነኛ  ፈልግልኝ ሲለኝ ወላሂ ከባድ በጣም ከባድ የአእምሮ ስራ ነበር የገጠመኝ...ደግሞ እንደኔ Hiv ያለባቸዉ የተለያዩ ሀገር አሉ group አለ ግን መቼም ትዳር ሲሆን የራስ የስራ ቦታና መስፈርት ይኖራል በዛ ላይ መስፈርት ስላልመጣ እንደሆነ በስልክ ጭምር ስንደዋወል ያሳዉቀኛል፡፡

እንደዚሁ ሀላል ፍላጋ Hiv ያለባቸዉ አዉሮፓ አረብ ሀገር አፍሪካ ዉስጥ የብዙ ሰዉ ጥያቄ ነዉ
ፈርንሳይ አሜሪካ ወዘተ ብዙ ሙስሊሞች አሉ
አሜሪካ ፈረንሳይ ሱዳን ወዘተ

ከዛ ቡሀላ ያላማከርኩት ሰዉ የለም ስደዉል ምን ስል መፍትሄ አጣሁ..የሚገርማችሁ በሚዲያ የምናቀቸዉ ታዋቂ ኡስታዞችን በሰዉ እንዲጠየቁ አድርጌ ነበር ግን
ምንም መፍትሄ ሀሳብ እንደሌላቸዉ ነዉ ያሳወቁኝ...

መቼም አላህ እድሜዉን ይጨምርለት ምርጥ መካሪየ አስተማሪየ የዲን ወንድሜ በደሀ ፍቅር የምናቀዉ ከድር አህመድ ከሀርቡ ሳማክረዉ አሳማኝ ምርጥ መልስ ሰጠኝ
>>አንድ የማቀዉ Hiv positive ነበር እሱ መድሀኒት ከሚቀበልበት ሆስፒታል የሚሰጠዉን ዶክተር አማክሮ
የሚሆነዉን አግኝቶ አግብቶ እየኖረ ነዉ እናም መድሀኒቱን ከሚቀበልበት ጤና ጣቢያ የሚሰጠዉን ዶክተር ቢያማክር  ጥሩ ነዉ አለኝ ...ምርጥ በላጭ ሀሳብ ነበር ለልጁም ነገርኩት በጣም ትክክል እንደሆነ ነገረኝ..Hiv መድሀኒት ከሚቀበልበት ጤና ጣቢያ ሲያማክር ሙስሊም ሴት እኛ ጋር የሚወስድ የለም አሉት የልጁ ሀገር መግለፁ ለጊዜዉ ይቆይ ፡፡ እሱ የሚኖርበት  ሙስሊም በብዛት የለምና

በስልክ በተደዋዉለን ቁጥር ከአንድ ሰአት በላይ እናወራለን Hiv ኬዝ ያለባቸዉ በጣም ብዙ ሰዉ እንዳሉ ግን ሁሉም እየደበቁ ነዉ እኔም ቤተሰብ ተጨነቀብኝ ቶሎ ማግባት አለብኝ አብረን በአላህ ፍቃድ መፍትሄ እንፈልግ አለኝ
የሚገርማችሁ በስልክ ካጫወተኝ ወላሂ ከወንዱ በላይ ሴቶች በጣም እየተቸገሩ እንደሆነ እምባ የሚያለቅሱ እህቶች እንዳሉ ብዙ ታሪክ አጫዉቶኛል፡፡ እኔስ ወንድ ልጅ ነኝ እቋቋመዋለሁ ግን ሴቶች ያሳዝኑለል ከባድ ጊዜ የሚያሳልፉ አሉ አሚር ብሎ በጣም ብዙ ነገር አጫዉቶኛል

ለHiv positive ብቻ የተከፈቱ ቻናሎች አሉ አንዳንዶች ያስተዋውቁና ከተጋቡ የደላላ ኮምሺን የሚቀበሉ አሉ::በዚህ group የተለያዩ ሀይማኖት አሉ ለትዳር ብለዉ በዚሁ Hiv ኬዝ ስላለባቸዉ ትዳር ስለሚያጡ ብዙዎች ሀይማኖታቸዉን እየቀየሩ ነዉ፡፡
እኔ ደግሞ በነዚህ አይነት ቻናሎች የመጡ ማግባት ይከብዳል ዲን አይኖራቸዉም ሀይማኖታቸዉ ሌላም ቢሆን ለትዳሩ ሲሉ  እስከመቀየር የሚደርሱ አሉ እናም ከነዚህ group ማግባት በጣም ከባድ ነዉ አለኝ

እስኪ ከነገረኝ ታሪኮች ልንገራችሁ
675 viewsedited  03:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-04 07:26:13
በፊት ሴት ልጅ ሰነፍ ከሆነች አትማር ማንበብ መፃፍ ካወቀች ይበቃል እስከ 8 ከተማሩ በቂ ነዉ የትምህርት ቤት እና የቤት ዉስጥ ባህሪያቸዉ የተለያየ ነዉ ...ሰነፍ ከሆነች አትማር መማሯ ጉዳት ያመጣል በዲን አሳድጎ በልጅነቷ መዳር ይሻላል....
ወንድም ያዉ ነዉ ግን ጉዳቱ ለሴት በጣም ያመዝናል ስል..... በተደጋጋሚ አንተ የድሮ ሰዉ ነህ ለሴት መጥፎ የተጣመመ አመለካከት አለህ ተብየ ነበር

እድሜ ለትምህርት ሚኒስራችን ለዶክተር ብርሀኑ ነጋ እንኳን ሰነፍ ሴት ተማሪ ወንድም ቢሆን ሰነፍ ከሆነ መማር እንደሌለበት ትክክል መሆኑን ዘንድሮ በ12 ክፍል ፈተና ዉጤት አሳይቶናል

በጣምም ብዙ ትምህርት ቤቶች አንድ እንኳ ተማሪ ያላሳለፉ እንዳሉ መቼም ሰሞታችሆል...ለወደፊት የትምህርት ጥራትን በአሁኑ አጀማመሩ ጥርት ያለ ትዉልድ እንደሚፈጥር ባለሙሉ ተስፋ ነኝ...

መቼም መምህሮቹ ማሰቢያቸዉ ከሰራ  ከአሁን ቡሀላ ትምህርት ቤቶች እንዳይወቀሱ እንዳይተቹ እየጓፈፉ የሚያሳልፉ አይመስለኝም ለምን በአሁኑ የትምህርት ሚኒስተር አያያዝ ስወድቁ ትምህርትቤቱን እንደሚገመግም ባለሙሉ ተስፋ ነኝ...
ለማንኛዉም በተለይ ለሴቶች ሰነፍ ተማሪ ከሆነ ይሄኔ በሀላሉ ጥግ ቢይዙ ኸይር ነዉ ባይ ነኝ

ለወደቃችሁ ተማሪዎች የስራ ዉጤት ነዉ ምንም ማለት አይቻልም ያለፋችሁ ግን ከእናንተ ጀምሮ ያለዉ ተማሪ ምርጥ ትዉልድ እንደሆነ አርጋችሁ አስባችሁ ጥሩ ደረጃ እንየምደርሱ ባለሙሉተስፋ ነኝ ለምን ዝምብሎ ግቢ ገብቶ ላይፍ እንቅጭ;boy frind ..girl frind እያለ ከሚያለቃቅስ ስራፈት እና
በዘር በፓለቲካ ዝባዝንኬ እያነሳ የሚበጠብጠዉን ቦዘኔ የማይጠቅም የማይጎዳን የአፈር ገንፎን ዶክተር ብርሀኑ ነጋ ደህና አድርጎ አበጥሮታልና አሁን ዩኒቨርስቲ የሙህራን ህልም ያለዉ ለሀገር ለወገን የሚበቁ ትዉልዶች ማፍሪያ ይሆናል፡፡



ደግሞ በፊት ያልኳቸዉ ሙነሾዶች የያዙት አቋም ከባድ ነዉ ተጠንቀቁ ስል ነበር...የዛን ጊዜም እተች ነበር ግን ይሄዉ ሁሉም ነገር ይፋ እየወጣ ነዉ

የእነሱም ጉድ ሚዲያ ላይ እያያችሁ ነዉ ሲያገቡም ሲፈቱም በአዳራሽ  ሰብስበዉ ሲጨፍሩ ሲያስጨፍሩ....
እኔ የምመኘዉ ቦዘኔ ተማሪን ዶክተር ብርሀኑ ነጋ አደብ እንዳሲያዘልን ..በዲን የሚያላግጡ ሙነሺዶችን ቁርአን መቅራት ሀዲስ ማዳመጥ ትተዉ አብረዉ እያንጎራገሩ የሚዉሉ የሙነሺድ ተከታይ አድናቂዎች 80% በላይ የሚሆን ሴቱን ከነሺዳ አዉጥቶ በቁርአን በተዉሂድ የሚያረጥብ አንድ ጀግና እንደሚፈጠር ኢንሻ አላህ ተስፋ አደርጋለሁ፡፡

ጀሊሉ ሆይ ለሰነፍ ለቦዘኔ ተማሪ ዶክተር ብርሀኑ ነጋን እንደላክልን በዲን ለሚቀልዱና እነሱን ለሚከተሉ ሁሉ ቀጥተኛ መንገድ የሚመራን የማንም ፊርቃ አባል ያልሆነ ከዚህ ትዉልድ አዉጣልን ያረብ

ለማንኛዉም ለዶክተር ብርሀኑ ነጋ ትልቅ ክብር አለን
ይህን ፁሁፍ ለመፃፍ የዘገየሁት ያዉ ከሚዲያ ራሴን ሳላገለልኩ ነዉ ያለፋችሁ እንኳን ደስ ያላችሁ

የወደፊት የሚፈጠረዉን ደግሞ አብረን እናያለን
መልካም ጥሩ የህይወት ዘመን ተመኘሁ



اسلام عليكم ورحمة الله وبركاته
Amir  seid dena neh?
Abshr hulum neger yalfal bcha ante tegstegna hun ALLAH kante ga new,ALLAH SUBHANEHU WETEALA ytebkh,enam bekrbu wede telegram alem endemtmeles  tesfa aregalehugn
ALLAH Imanh ychemrlh ...

ye mekelle lij negn

Channelhn befit awkow neber  abzagnawochu  tarikoch anbibyachaw nebere enam bzu tmrt kante Channel aggnichalow جزاك الله خيرا but 2 amet yakl  internet alneberem....
Be gugt yante channel etebk neber
Alhamdulilah ahun tekefto egna sngeba ante tefahbn ALLAH be kheyr ymelsh...

Yetefahbet mknyat balekewm انشاء الله tmelesaleh biye tesfa argalehugn...
Ende mitaweqew egnam betam bekebad chgr lay new yenebernew bihunm hulum neger alfo  negerochn be ALLAH fkad eyetestekakelu ygegnalu...
Slehonem yedunya musibawoch ena fetenawoch ayalkum ena hulum neger lekheyr new bleh dua arg انشاء الله
ALLAH SUBHANEHU WETEALA kalehbet chgrh yawtah...جزاك الله خيرا

ትግራይ ክልል ያሉ በፊት የኔን ቻናል ሲከታተሉ የነበሩ ብዙዎች በአስተያየት ከመቀሌ ከአድዋ ወዘተ እየላኩልኝ ነዉ ይሄ የአንዱ ቤተሰብ አስተያየት ነዉ፡፡ አልሀምዱሊላህ ያ ቀን አልፎ ለመገናኘት በቃን አልሀምዱሊላህ
ከትግራይ ክልል ኢንተርኔት እንደተከፈተ የኔ ደህንነት አስስቧችሁ ለጠየቃችሁኝ ከልብ አመሰግናለሁ


አሚር ሰይድ
491 views04:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-21 07:18:13 ታላቅ የምስራች ተጅዊድን መማር ለምትፈልጉ ተማሪዎች

#ዚክራ_ኦንላይን_የቁርአን_ማእከል
የሁለት ወር ጥቅል የተጅዊድ ትምሀርት ይዞላችሁ መጥቷል

     #የትምህርቱ_አሰጣጥ
1,በዙም አፕልኪሼን
2,በቴሌግራም አፕልኬሽን

    
        #የቆይታ_ጊዜ
በሳምንት 3 ቀን


#ትምህርቱን_ለመከታተል_የሚያስፈልጉ
ዋይፋይ(ፈጣን ኔትወርክ)
ስማርት ስልክ


        #ያሉን_ቦታዎች
##በጀመአ (በግሩፕ)
##vip (በ ግል)

ከተሟላ በሰርተፍኬት ጋር

በግል ለመመዝገብ

@redwan6910

ወደ ተጅዊድ ትምህርት መስጫ ግሩፕ
https://t.me/+V3lxqKjWQHxiYzFk

ወደ public group

https://t.me/+-zHkXQeSZdc4MjY0

ምዝገባ የሚያበቃበት ቀን
በኢትዮጵያ ህዳር 15

#zikra_Qur'anic_academy
507 views04:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ