Get Mystery Box with random crypto!

Housing in Addis Ababa የአዲስ አበባ ቤቶች

የሰርጥ አድራሻ: @housinginaddisababa
ምድቦች: ዜና
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 68.66K
የሰርጥ መግለጫ

The interest of this Channel is giving continuous information about housing projects (40/60&20/80) & other Real Estates Updates.

Ratings & Reviews

1.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

2


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 121

2022-09-07 09:38:04 ጦርነቱ ተፋፍሞ ቀጥሏል፤ የጦርነቱ ውሎና አዳር በጥቂቱ እንዳስሳለን!
ሕወሓት ዳግም የከፈተውን ጦርነት የሚያወግዝ ሰላማዊ ሰልፍ በዋሺንግተን ዲሲ ተካሄደ!
በጎንደር የኬላ ፍተሻ 308 ሽጉጥ ተያዘ።
የ16 የፖለቲካ ፓርቲዎች ጦርነቱ በሰላማዊ ውይይት እንዲቋጭ ጥሪ አቀረቡ!
ከአንድ አመት በላይ በህወሓት ስር የቆየችው ማይ ጠብሪ ነፃ ወጣች !
ከህወሓት ጋር ሚስጥራዊ ግኑኝነት ፈጥረዋል የተባሉ ትናንት ፍርድ ቤት ቀረቡ!
አምባሳደሩ በፆታዊ ጥቃት ተጠርጥረው ተጠሩ!



7.5K views06:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-07 08:34:45
ባሌ ዞን ሮቤ ከተማ የእግረኛ መንገድ!!
8.4K views05:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-06 13:49:10
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ለአቅመ ደካሞችና ገቢያቸው አነስተኛ ለሆነ ነዋሪዎች ቤቶችን አስረከቡ

የበጎ ፈቃድ ቀንን በማስመልከት፣ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ አቧሬ አካባቢ ለአቅመ ደካሞችና በአነስተኛ ገቢ ለሚተዳደሩ የአቧሬ አካባቢ ነዋሪዎች የተሠሩላቸውን ቤቶች አስረክበዋል።

ይህ ርክክብ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ የተጀመረው የዓመታዊ የቤት እድሳት አንድ አካል መሆኑን ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጽህፈት ቤት ያገኘነወ መረጃ ያመለክታል ።
11.0K views10:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-06 13:40:13 በልደታ ክፍለ ከተማ በሁለት እና ሶስት ወራት ብቻ የተገነቡ ሦስት ባለ አስራ አንድ ወለል ዘመናዊ ህንጻዎችን ከንቲባ አዳነች አቤቤ በይፋ አስመረቁ!!

ጳጉሜን በመደመር ስንል ምክንያታችንም መልዕክታችንም ትልቅ ነበር በዚህና በሰው ተኮር ዕቅዳችን መነሻነት በዘጠና ቀናት ብቻ ዘጠኝ መቶ 952 ቤቶችን በጎ ፈቃደኞችን በማስተባበር ገንብተን ዛሬ በሁሉም ክ/ከተማ ቁልፍ ለማስረከብ በቅተናል ብለዋል ከንቲባ አዳነች

በሚቀጥለው አዲስ ዓመትም በ24-ሰባት መርህ በርካታ ሥራዎችን ለመስራት ዘርፈ ብዙ ቅንጅታዊ እንቅስቃሴ እያደረግን ነው ያሉት ከንቲባዋ በሚቀጥለው አዲስ ዓመትም በርካታ ስኬቶችን በቅንጅት ፣በአንድነትና በወንድማማችነት እንደምናስመዘግብ ዕምነቴ የጸና ነው ብለዋል ከንቲባ አዳነች

ስንተባበርና ተቀናጅተን ስንሰራ አቅማችን ትልቅ ነው ያሉት ከንቲባ አዳነች በዚህ ልክ ሁሉም የየድርሻቸውን ማህበራዊ ኃላፊነት መወጣት ቢችል የአቅም ደካማ ወገኖች የኑሮ ጫና በሚፈለገው ደረጃ ማቃለል እንችላለን ሲሉ አጽንኦት ሰጥተው ተናግረዋል።

የሀገር መከላከያ ሰራዊታችንና የጥምር ጦሩ አባላት ውድ አገራችንን አናስደፍርም በሚል በሚከፍሉት መስዋዕትነት አጠቃላይ የልማት ስራዎቻችንን ማስቀጠል ችለናል ለዚህም ልመሰገኑና አስፈላጊውን ድጋፍ ሁሉ ካለን ላይ ቀንሰን ልናደርግላቸው ይገባል ብለዋል ከንቲባዋ

መጪው ዘመን ኢትይጵያ ብቻ የምታሸንፍበትና አንድነታችን ከብረት ይልቅ የሚጠነቅርበት ግዜ እንደሚሆን አልጠራጠርም ያሉት ከንቲባ አዳነች በፍጹም ላንነጣጠል በአንድነትና በወንድማማችነት መንፈስ በመቆራኘት በሁሉም ረገድ አገራችን የሚፈጸምባትን ጥቃት ልንከላከልና ጸንተን ልንመክት ይገባል ብለዋል ከንቲባዋ

በልደታ ክፍለ ከተማ በአጠቃላይ አንድ መቶ ሃምሳ ቤቶችን የያዘ ሦስት በለአስራ አንድ ወለል ሕንጻ በኦቪድ የኮንስትራክሽን ዕቃዎች አቅራቢ ድርጅት ተገንብቶ ለአንድ መቶ 65 አባዎራዎች በዛሬው ዕለት ከንቲባ አዳነች አቤቤ አስመርቀዋል

በዛሬው ዕለት በልደታ ክፍለ ከተማ ምርቃት ከተደረገላቸው ሦስት የጋራ መኖሪያ የአፓርትመንት ህንጻዎች መካከል ኦሮሚያ ባንክ አንዱን ፣ማናዬ የኮንስትራክሽ ድርጅት በተመሣሣይ አንዱን ህንጻና ሚዲሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ሦስተኛውን ህንጻ አጠቃላይ ወጪ በመሸፈን በኦቪድ ኮንስትራክሽን እቃዎች አቅራቢ ድርጅት አማካኝነት ህንጻዎቹ በዘጠና ቀናት ተገንብተው ለምርቃት በቅተዋል።

አቶ ኃይሉ ሉሌ የልደታ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ዋና ሥራ አስፈጻሚ ይህ አቅመ ደኮሞች በአቪድ ኮንስትራክሽን የተገነባው ሕንጻ በአጭር ግዜ በዘጠና ቀናት ውስጥ ብቻ ተጠናቆ ለነዋሪዎች እንዲተላለፍ የከተማ አስተዳደሩ በየደረጃው ያሉ የሥራ ኃላፊዎች በቅንጅት ተንቀሳቅሰዋል ለዚህም ልመሰገኑ ይገባል ብለዋል ።
10.1K views10:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-06 13:40:10
አስጀምሮ ያስጨረሰን ፈጣሪ ይመስገን !!

በ 90 ቀናት ሶስት እያንዳንዳቸው ባለ 11 ወለል ህንፃዎች ፣ ለ165 አባወራዎች መኖሪያ የሚሆኑ ህንጻዎችን መርቀን ለወገኖቻችን የአዲስ አመት ስጦታ አበርክተንላቸዋል።
ይህ የግንባታ ሂደት 24/7 በትጋት የሰራንበት ፤ በግንባታው ዘርፍም አዲስ የግንባታ አሰራር ስርዓትና የስራ ባህል ያየንበት እና የእንችላለን መንፈስ የጎለበተበት ነው ።
ይህንን ድንቅ ስራ የሰራው ኦቪድ ኮንስትራክሽን ( Ovid construction) ሲሆን፣ የህንጻዎቹ ወጪ የተሸፈነው የከተማ አስተዳደሩ ከኦሮሚያ ህብረት ስራ ባንክ፣ከሜድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ እና ከ MWS ኮንስትራክሽን ጋር በመሆን ነው።

በጣም እናመሰግናቹሃለን !
ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ
9.9K viewsedited  10:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-06 10:34:36 ሰራተኛዋ በፍሪጅ ውስጥ የዘጋችበት ህፃን ከነ ህይወቱ መገኘቱ ተገለጸ!
ኢትዮጵያ 22 ቢሊዮን ዶላር በአንድ ዓመት አግኝታለች ተባለ!
የጋራ መኖሪያ ቤቶች ዛሬ ለተጠቃሚዎች !
ኢትዮጵያ ለህዳሴው ግድብ የሩሲያን የቴክኒክ ድጋፍ ልትጠይቅ ትችላለች ተባለ!
የግብጹ ፓትሪያርክ ዓባይን እንደ አባታችን ነው የምናየው አሉ !
በዓመት 10ሺ ትራክተሮችን ማምረት የሚያስችል ፋብሪካ ሊገነባ ነው!
የአፍሪካ ህዝቦች የወዳጅነት ቀን” ፌስቲቫል በሱዳን ተካሂደ!
አሜሪካ ለታይዋን የጦር መሳሪያ የመሸጥ እቅዷን እንድትተወው ቻይና አስጠነቀቀች!



11.8K views07:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-06 02:06:37 በጥቁር ገበያ የአንድ ዶላር ምንዛሬ ዋጋ ከ90 ብር በላይ መድረሱ ተስተዋለ።

ለጥቁር ገበያው መስፋፋት ዋና የዶላር ምንጭ የሆነውን ሕገ ወጥ የሃዋላ እንቅስቃሴ ነው ያለው ብሄራዊ ባንክ ዝውውሩ የሚከናወንባቸውን የሒሳብ ቁጥሮችን የመለየት ሥራ እየሠራ መሆኑን ለባላገሩ አብራርቷል።

ከብር አንፃር የዶላር ዋጋ እለት ከእለት እየጨመረ ይገኛል፡፡

በአዲስ አበባ መደበኛ ባልሆነው በጥቁር ገበያ ባለፉት ጥቂት ቀናት ዶላር ከፍተኛ ጭማሬ ማሳየቱን የባላገሩ ዘጋቢ ባደረገው ቅኝት ተረድቷል።

ካሳለፍነው ሳምንት ጀምሮ አንድ ዶላር በጥቁር ገበያው ከ85 እስከ 87 ብር ድረስ በመመንዘር ላይ እንደሚገኝ እና በተለያዩ ሁኔታዎች ይህ ዋጋ እስከ 92 ብር ድረስ ከፍ እንደሚል ባላገሩ ቴሌቪዥን ብሔራዊ ቴያትር አካባቢ ከሚገኙት የጥቁር ገበያ መንዛሪዎች መረዳት ችሏል፡፡

በመደበኛው የምንዛሬ ገበያ አንድ ዶላር በ53 ብር አከባቢ እየተመነዘረ ይገኛል። በአሁኑ ጊዜ በጥቁር ገበያ እና መደበኛ ገበያው መካከል ያለው ልዩነት ከ26 ብር በላይ ሆኗል።

የዶላር ዋጋ መጨመሩ በአገሪቱ ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ በመጣው ዋጋ ንረት ላይ የራሱን የሆነ ጫና የሚያሳድር መሆኑን የምጣኔ ኃብት ባለሞያው ዶ/ር አጥላው ዓለሙ ያነሳሉ፡፡

ለጥቁር ገበያው መናር የአገሪቱ ወጪ እና ገቢ ንግድ አለመመጣጠን መሠረታዊ ምክንያት መሆኑን የምጣኔ ሃብት ባለሞያው ደ/ር አጥላው ገልጸዋል፡፡

አገሪቱ በቂ የውጭ ምንዛሬ ማግኘት ባለመቻሏ ነጋዴው ማህበረሰብ በቂ ዶላር በባንክ ቤቶች በኩል ማግኘት አለመቻሉን አንስተዋል፡፡

በዚህም ምርት ከውጭ የሚያስገቡ ነጋዴዎች የጥቁር ገበያውን እንደ ዋና የውጭ ምንዛሬ ምንጭነት እየተጠቀመበት መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ ይህም የውጭ ምንዛሬ ፍላጎቱን እንዳሳደገው አብራርተዋል፡፡

የጥቁር ገበያውን ለመቆጣጠር በዋናነት የባንኮችን የዶላር ክምችት ማሳደግ እንደሚገባ የምጣኔ ሀብት ባለሞያው የነሱ ሲሆን ለዚህም ምርትን በማሳደግ ላይ በትኩረት ሊሠራ እንደሚገባ ጠቁመዋል፡፡

በጉዳዩ ላይ ማብራሪያ የጠየቅናቸው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ምክትል ገዥ አቶ ፍቃዱ ድጋፌ ከሰሞኑ ሰሜናዊ የአገራችን ክፍል ዳግም ያገረሸውን ጦርነት ተከትሎ የጥቁር ገበያው የምንዛሬ ዋጋ ጭማሪ ማሰየቱን ጠቁመዋል፡፡

ሩሲያ እና ዩክሬን የገቡበትን ጦርነት ተከትሎ የዓለም ምርት ዋጋ ጭማሪ በማሳየቱ የውጭ ምንዛሬ ፍላጎት መጨመሩንና ይህን ተከትሎ በጥቁር ገበያ የምንዛሬ ዋጋ እድገት ማሳየቱን ምክትል ገዥው አብራርተዋል፡፡

በዓለም ገበያ ላይ የዩሮ ዋጋ እየቀነሰ መምጣቱን ያነሱት አቶ ፍቃዱ በተቃራኒው የዶላር ፍላጎቱ ከቀን ወደ ቀን እየጨመረ መምጣቱን ጠቁመዋል፡፡

ለጥቁር ገበያው መስፋፋት ዋና የዶላር ምንጭ የሆነውን ሕገ ወጥ የሃዋላ መሆኑን ያነሱት አቶ ፍቃዱ፤ ባንኩ የዚህ እንቅስቃሴ ማካሔጃ የሒሳብ ቁጥሮችን የመለየት ሥራ እየሠራ መሆኑን ጠቁመዋል፤ በቅርቡም በዚህ እንቅስቃሴ ላይ ሲሳተፉ በተገኙ የሒሳብ ቁጥሮች ላይ እርምጀ እንደሚወሰድ ጨምረው አንስተዋል፡፡

በመደበኛ የዶላር ምንዛሬ ገበያውም ላይም ቢሆን ባለፉት ስድስት ወራት በአንድ ዶላር የምንዛሬ ዋጋ ላይ የ2 ብር ከ60 ሳንቲም ጭማሪ እንደተደረገበት ቁጥራዊ መረጃዎች ያመለክታሉ፡፡

ይሳቅ አበበ
ባላገሩ ቴሌቭዥን
5.1K views23:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-06 02:06:34
5.0K views23:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-05 22:12:03
የጋራ መኖሪያ ቤቶች ለተጠቃሚዎች ይተላለፋሉ
.
በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ በአነስተኛ ወጪ ተገንብተው የተጠናቀቁ የጋራ መኖሪያ ቤቶች በነገው ዕለት ተመርቀው ለተጠቃሚዎች ይተላለፋሉ።

ባለፉት 60/90 ቀናት በልዩ ድጋፍ በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ በአነስተኛ ወጪ ተገንብተው የተጠናቀቁት እነዚህ የጋራ መኖሪያ ቤቶች በነገው ዕለት ተመርቀው በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ ለሚገኙ 70 ያህል አባወራዎች ይተላለፋሉ ተብሏል።

ግንባታቸው የተጠናቀቀው እነዚህ ባለ ሶስት ብሎክ ጂ+1 የጋራ መኖሪያ ቤት እያንዳንዳቸው ባለ አንድ መኝታ ክፍል ያሏቸው ሲሆን የህዝብ ቤተ መጽሃፍት፣ የጋራ የሆነ የምግብ ማብሰያ ቦታዎች ያሉት መሆኑ ተገልጿል።
2.5K views19:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-05 10:18:27 የህወሀት ሚስጥራዊ ሰነድ ይፋ ሆነ!
የመምህራን ጥያቄ በጦርነቱ ምክንያት ሳይመለስ ቀርቷል ተባለ!
ልማት ባንክ 30 ቢሊዮን ብር ብደር ሊለቅ ነው!
መስቀል አደባባይ በዓለም አንደኛ የህዝብ አደባባይ ሆነ።
ለተከሰከሰው አውሮፕላን የተከፈለው የጉዳት ካሳ ካፒታሉን እንዳናጋበት የኢትዮጵያ መድን ድርጅት አስታወቀ!
የካቲት 12 ሆስፒታል ከታካሚዎቹ ጋር አልተግባባም ተባለ!
አሜሪካ በሰደድ እሳት አየተጠበሰች ነው!
ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን የአሜሪካ ጠላት ነው” ሲሉ ዶናናድ ትራምፕ ተናገሩ!



4.7K views07:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ