Get Mystery Box with random crypto!

Housing in Addis Ababa የአዲስ አበባ ቤቶች

የሰርጥ አድራሻ: @housinginaddisababa
ምድቦች: ዜና
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 68.66K
የሰርጥ መግለጫ

The interest of this Channel is giving continuous information about housing projects (40/60&20/80) & other Real Estates Updates.

Ratings & Reviews

1.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

2


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 118

2022-09-23 08:28:39
11.7K views05:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-22 22:47:32
ሲንቄ ባንክ

ሲንቄ ባንክ በአዲስ መለያ (Brand) የተሟላ የባንክ አገልግሎት መስጠት መጀመሩን አስታውቋል።

ሲንቄ ባንክ ከማይክሮ ፋይናንስ ወደ ባንክ በማደግ ከዚህ ቀደም ይሰጠው የነበረውን የማይክሮ ፋይናንስ አገልግሎትም በማካተት የተሟላ የባንክ አገልግሎት ለመስጠት ከፍተኛ ዝግጅት ሲያደርግ መቆየቱንም ገልጸዋል።

ሲንቄ ባንክ የማይክሮ ፋይናንስ አገልግሎት ይሰጡ ከነበሩ 405 ቅርንጫፎቹ መካከል 250ዎቹ የባንክ አገልግሎት መስጠት የሚያስችላቸውን ፈቃድ ከብሔራዊ ባንክ አግኝቷል።

ሲንቄ ባንክ 15 ቢሊየን ብር የተመዘገበና 7 ነጥብ 4 ቢሊየን ብር የተከፈለ ካፒታል በመያዝ የአገሪቱን የባንክ ኢንዱስትሪ የተቀላቀለ ባንክ ነው።
13.4K views19:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-22 19:07:51 ትላንት ምሽት ባህርዳር ከተማ በጥይት የተገደሉት ኮማንደር ስርዐተ ቀብር ዛሬ ተፈጸመ
ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን በተመድ ጉባኤ ስለ ኢትዮጵያ ተናገሩ
በሰሜን ወሎ መርሳ ከተማ 63 ሰርጎገቦች ተያዙ
በወለጋ ንፁሀን እያለቁ ነው ተባለ
አቶ ገዱ አንዳርጋቸው የቦርድ ሰብሳቢ የሆኑበት ፀደይ ባንክ በመጪው ቅዳሜ ስራ ይጀምራል
ምርጫ ቦርድ የሀገር አቀፍ የምርጫ ቁሳቁሶችና ሰነዶችን አቃጠለ!
ከንቲባ አዳነች ስለመስቀል አከባበር መግለጫ ሰጡ!
ለህዳሴው ግድብ ከፍተኛ ገንዘብ እየተሰበሰበ ነው



14.6K views16:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-22 13:47:04
ፀደይ ባንክ በመጪው ቅዳሜ ስራ በ148 ቅርንጫፎች ስራ ይጀምራል

ባንኩ በ7 ነጥብ 8 ቢሊዮን ብር የተከፈለ ካፒታል እና በ11 ቢሊየን ብር ጠቅላላ ካፒታል፣ እንዲሁም 46 ቢሊየን ብር ጠቅላላ አሴት እና በ12 ሚሊየን ደንበኞች ይዞ ወደ ገበያው ይቀላቀላል።

ፀደይ ባንክ ቀደሞ የአማራ ብድር ተቋም (አብቁተ) በሚል በማይክሮ ፋይናንስ ደረጀ ሲሰራ የነበረው የፋይናንስ ተቋም በብሄራዊ ባንክ መመሪያ መሰረት ወደ ባንክነት ተሸጋግሮ የተመሰረተ ባንክ ሆኗል።
15.4K views10:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-22 11:06:32 ዐቃቤ ህግ ዶ/ር ሙሉቀን ሀብቱን ጨምሮ በ11 ተከሳሾች ላይ በሙስና ወንጀል ክስ መሰረተ

ዐቃቤ ህግ የኮንዶሚኒየም እጣ እንዲጭበረበር አድርገዋል የተባሉት የቴክኒክ ሙያ ሥልጠናና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ኃላፊ የነበሩትን ዶ/ር ሙሉቀን ሀብቱን ጨምሮ በ11 ተከሳሾች ላይ በሙስና ወንጀል ክስ መስርቷል።

ተከሳሾች፡-1ኛ. ዶ/ር ሙሉቀን ሀብቱ ምሩፅ (በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የቴክኒክ ሙያ ስልጠናና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የቢሮ ኃላፊ የነበረ)

2ኛ. አብርሃም ሰርሜሎ ኪዳኔ (በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የቴክኒክ ሙያ ስልጠናና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ምክትል የቢሮ ኃላፊ የነበረ )

3ኛ. ኩምሳ ቶላ ገኖ (በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን የአይሲቲ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር የነበረ )

4ኛ. መብራቱ ኪ/ማርያም በርሄ (በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የቴክኒክ ሙያ ስልጠናና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የሶፍትዌር ሲስተም ልማት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር የነበረ)

5ኛ. ስጦታው ግዛቸው ደገፋ (በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የቴክኒክ ሙያ ስልጠናና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የሶፍትዌር ፕሮግራመር የነበረ)

6ኛ. ባዩልኝ ረታ ጸጋ (በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የቴክኒክ ሙያ ስልጠናና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የሶፍትዌር ፕሮግራመር የነበረ)

7ኛ. ሚኪያስ ቶሌራ ወ/እየሱስ (በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን የሲስተምና ዳታ ቤዝ ባለሙያ የነበረ)

8ኛ. አሚ አምባዬ ማሞ (በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የቴክኒክ ሙያ ስልጠናና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የሶፍትዌር ፕሮግራመር የነበረ)

9ኛ. ዮናስ ወ/ጊዮርጊስ ነዳሳ (በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን የመረጃ ባለሙያ የነበረ)

10ኛ. ዘካርያስ አያለ ገቢ (በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን የሲሰተም ዳታ ቤዝ አድሚንስትሬተር)

11ኛ. ኤደን ካሳሁን ተሰማ ሲሆኑ፤ ዐቃቤ ህግ 3 ክሶችን የኢፌደሪ ፍትህ ሚኒስትር የጠቅላይ ዐቃቤ ህግ ዘርፍ የሙስና ወንጀል ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ጀኔራል ዐቃቤ ህግ በፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ የጊዜ ቀጠሮ ችሎት በትላንተናው ዕለት ክስ መስርቶባቸዋል፡፡

የሙስና ወንጀል ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ጀኔራል ዐቃቤ ህግ በ1ኛ የክስ ዝርዝር በ1ኛ፣ 2ኛ እና በ3ኛ ተከሳሾች ከፍተኛ የመንግስት ኃላፊነት ላይ ተመድበው ሲሰሩ የማይገባ ጥቅም ለማግኘት ወይም ለማስገኘት በማሰብ ስልጣናቸውን ወይም ሃላፊነታቸውን ተጠቅመው በሀምሌ 01 ቀን 2014 በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የጋራ መኖሪያ ቤቶች እድለኞችን በፍትሃዊ የሎተሪ እጣ በሲስተም ለመለየት ተብሎ ከወጣው የ14ኛ ዙር የ20/80 እና የ3ኛ ዙር የ40/60 የወጣበትን ሲስተምን የማልማት፣ እጣ የማውጣት እና የኮንደሚኒየም ቤት የቁጠባ ተመዝጋቢዎችን የዳታ ቅብብሎሽ ሂደትን በተሰጣቸው ኃላፊነት መሰረት ሊከላከሉት፣ ሊጠብቁት እና የጥራት ደረጃውን በጠበቀ መንገድ ለውጤት ማብቃት ሲገባቸው፤ 1ኛ እና 2ኛ ተከሳሾች በሥራ ሃላፊነታቸዉ ሊጠብቁትና ሊከላከሉት የሚገባዉን የመንግስትና የህዝብ ጥቅም ወደጎን በመተዉ እድለኞችን መርጦ የሚያወጣ ሲስተምን የማልማት፤ የፕሮጀክት ሥራ የጥራት ደረጃውን ጠብቆ እንዲለማ ማድረግ ሲገባቸው ሲስተሙ በትክክለኛ መንገድ ባለማበት እና ደህንነቱ ባልተጠበቀበት ሁኔታ፣ ከኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት ኤጀንሲ ለሲስተሙ የደህንነት ማረጋገጫ ሳይሰጠው ለእጣ ማውጣት እንዲወል በማድረግ፣ እጣው ዝቅተኛውን የቁጠባ መስፈርት የሚያሟሉ፣ ከአዲስ ተመዝጋቢነት ወደ ነባር ተመዝጋቢት የተቀየሩ፣ ቁጠባቸውን ያቋረጡ ግለሰቦች የእጣው ተጠቃሚ እንዲሆን የሚያስችል ክፍተት እንዲፈጠር በማድረጋቸው 3ኛ ተከሳሽ የተመዝጋቢዎች ዳታ እንዳይቀየር መጠበቅ እና መከላከል ሲገባው ዳታው ተጋላጭ እንዲሆን በማድረግ ህገ-ወጥ ጥቅሞችና ጉዳት እንዲደርስና እጣዉን ለመሰረዝ የሚያበቃ ከፍተኛ ክፍተት እንዲፈጠር በማድረጋቸዉ በዋና ወንጀል አድራጊነት ተካፋይ በመሆን በፈጸሙት የመንግስት ስራን በማያመች አኳኋን በመምራት ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ቀርቦባቸዋል፡፡

2ኛ ክስ ከ4ኛ እስከ 10ኛ በተጠቀሱት ተከሳሾች ላይ ብቻ የቀረበ ሲሆን፤ 4ኛ ተከሳሽ የእጣ ማዉጫ ሶፍትዌሩን በበላይነት የሚመራዉ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የቴክኒክ ሙያ ሥልጠናና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የሶፍትዌር ሲስተም ልማት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር በመሆኑ ህገወጥ ድርጊቱን ማስቆም ሲገባዉ በድርጊቱ ተባባሪ በመሆንና የራሱንም ሥም በማስገባት እጣ እንዲወጣለት በማድረጉ፤ 5ኛና 6ኛና ሶፍተዌሩን እንዲያለሙ፣ 7ኛ ተከሳሽ ደግሞ ከቤቶች የተዘጋጀዉን ዳታ እንዲያስተዳድር የተሰጣቸዉን ሃላፊነት ወደጎን በመተዉ እርስ በዕርሳቸዉና ከ8ኛ፣ 9ኛ እና 10ኛ ተከሳሾች ጋር በጥቅም በመመሳጠር ለእጣ ብቁ ያልሆኑ ሰዎችን ብቁ እንደሆኑ በማስመሰልና በእጣዉ ዉስጥ በማካተት አብዛኛዎቹ እጣ እንዲወጣላቸዉ በማድረግ በህዝብና በመንግስት ጥቅም ላይ ከፍተኛ ጉዳት እንዲደርስ ያደረጉ በመሆኑ በዋና ወንጀል አድራጊነት በፈፀሙት በስልጣን አለአግባብ መገልገል የሙስና ወንጀል ክስ ቀርቦባቸዋል፡፡

3ኛ ክስ 5ኛ እና ከ7ኛ እስከ 11ኛ የተጠቀሱት ተከሳሾች ላይ የቀረበ ሲሆን ተከሳሾች ገንዘቡ የወንጀል ፍሬ መሆኑን እያወቁ ወይም ማወቅ ሲገባቸው በስማቸዉ በከፈቱት የባንክ ሂሳባቸዉ ላይ እንዲገባ በማድረግና እርስ በርሳቸዉ በማስተላለፍ በዋና ወንጀል አድራጊነት ተካፋይ በመሆን በፈፀሙት በወንጀል ድርጊት የተገኘ ገንዘብን ሕጋዊ አስመስሎ ማቅረብ ወንጀል ክስ እንደተመሰረተባቸው ከፍትሕ ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ አመላክቷል፡፡

ከ10 ኛ እና 11ኛ ተከሳሽ ውጪ ያሉት ኹሉም (9ኙ) ተከሳሾች ፍ/ቤት ቀርበው ክሱ እንዲደርሳቸው መደረጉም ታውቋል፡፡
አዲስ ማለዳ
15.0K views08:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-22 11:05:21
ዐቃቤ ህግ ዶ/ር ሙሉቀን ሀብቱን ጨምሮ በ11 ተከሳሾች ላይ በሙስና ወንጀል ክስ መሰረተ

ሐሙስ መስከረም 12 ቀን 2015 (አዲስ ማለዳ) ዐቃቤ ህግ የኮንዶሚኒየም እጣ እንዲጭበረበር አድርገዋል የተባሉት የቴክኒክ ሙያ ሥልጠናና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ኃላፊ የነበሩትን ዶ/ር ሙሉቀን ሀብቱን ጨምሮ በ11 ተከሳሾች ላይ በሙስና ወንጀል ክስ መስርቷል።
13.1K viewsedited  08:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-22 10:57:03 የኮንዶሚኒየም ቤቶችን ዕጣ አጭበርብረዋል በተባሉት ላይ ክስ ተመሠረ!
የሰላምና ግጭት ተመራማሪዋ በባረቀ ጥይት ህይወቷ አለፈ!
የቀድሞ ሊቀመንበር ስለ ዘመነ ካሴ መስከሩ !
በኤርትራ ወታደሮች መጠነ ሰፊ ጥቃት እንደተከፈተበት ህወሀት አስታወቀ!
አረብ ኢምሬትስ እና ኢትዮጵያ ወንጀለኞችን
ለመቀባበል ተፈራረሙ!
በመጠጥ ንግድ ፈቃድ የጦር መሳሪያ ሲነግድ የነበረ ግለሰብ በቁጥጥር ስር ዋለ
ፕሬዝዳንት ፑቲን የክተት አዋጅ አወጁ



13.2K views07:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-22 10:54:41 የውጭ ምንዛሪ ፍላጎት በመጨመሩ፣ በትይዩ ገበያ ያለው የዶላር ምንዛሪ በከፍተኛ ሁኔታ የጨመረ ሲሆን ይፋዊ እና ትይዩ ገበያዎች ያለው የምንዛሪ ልዩነት ከፍተኛ እንዲሆን አድርጓል።
የጥቁር ገበያ ግብይት በሚካሄድባቸው አንዳንድ የከተማዋ አካባቢዎች በሳምንቱ አንድ የአሜሪካ ዶላር ከ90 እስከ 92 ብር ይሸጥ ነበር። ይህም ከመደበኛው የምንዛሪ ዋጋ ጋር ሲነጻጸር ከ70 እስከ 75 በመቶ ልዩነት ነበረው።

በካፒታል የገበያ ግምገማ በተለይ መኪና የሚያስገቡ አስመጪዎች አንድ የአሜሪካ ዶላር እስከ 100 የኢትዮጵያ ብር እየገዙ ነው። ባንኮች ካለው ምንዛሪ ልዩነት እስከ 90 በመቶ ይደርሳል።

የብሔራዊ ባንክ ምክትል ገዥ አቶ ፍቃዱ ድጋፌ በፍላጎትና በአቅርቦት መካከልም ክፍተት እንዳለ አመልክተው ሁኔታው በመቆጣጠር የሚቆም ነገር አይደለም ብለዋል።

ብሔራዊ ባንክ ትክክለኛ ምክንያቱ ምን እንደሆነ ለማወቅ ጥናት እያደረገ ነው” ያሉት ምክትል ገዢው ጥናቶች እንደተጠናቀቁ ሁኔታውን ለማረጋጋት እርምጃዎች የሚወሠዱ መሆኑን ጠቁመዋል ።

ባንኮቹ የሚያቀርቡት የውጭ ምንዛሪ በከፍተኛ ሁኔታ እየቀነሰ ሲሆን የሃርድ ምንዛሪ እጥረት እና በሀገሪቱ እየተባባሰ ያለው የዋጋ ንረት የአሜሪካ ዶላር በጥቁር ገበያ ላይ እንዲጨምር እያደረጉት እንደሆነ በሰፊው ይነገራል።
ሁኔታው ለመንግስት ፈታኝ እንደሆነ የሚናገሩት ባለሞያዎች
ጠንካራ የክትትልና የቁጥጥር ዘዴን በመዘርጋት ምንዛሪ ገበያ ላይ የተሰማሩ ደላሎችን ማስወገድ እንደሚቻል አስተያየት ይሰጣሉ ።

መንግስት የጥቁር ገበያን የምንዛሪ ልውውጥ ለመቆጣጠር እየታገለ ሲሆን ጥረቱ ግን የተሳካ አይመስልም።

Capital https://www.capitalethiopia.com/2022/09/18/normal-vs-parallel-exchange-rates-drift-astronomically-apart/
12.9K views07:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-21 22:29:47
14.8K views19:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-21 22:24:57
የጎጆ ብሪጅ እጣ መሰረዝ

መስከረም 10 ቀን 2015 ዓ.ም በወዳጅነት አደባባይ በነበረው የእጣ ማውጣት መርሀ ግብር ላይ ከዳሸን ባንክ ጋር የመግባቢያ ሰነድ የተፈራረመው ጎጆ ለስምንት ማህበራት እውቅና እንዲሁም ሰነድ ርክክብ ማድረጉ ይታወሳል።፣ እንዲሁም ጐጆ አፊሊዬት ፕሮግራም (GAP) ተዋውቋል። ይሁንና ብዙዎቻች ሲጠብቁት የነበረው የጎጆ ሮስካ ሎካል የመጀመሪያው ዙር እጣ የማውጣት ስነ-ስርአት፣ ይፋ በተደረገው የተመዝጋቢ ዝርዝር ተከትሎ እጣው ላይ ያልተካተቱ ሰዎች በመኖራቸው የእጣ ማውጣት ስነስረአቱ ተሰርዟል።
15.0K viewsedited  19:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ