Get Mystery Box with random crypto!

ጋሻ ƬƲƁЄ ꍟ꓄ꃅꀤꂦᖘꀤꍏ

የቴሌግራም ቻናል አርማ gasha_tube — ጋሻ ƬƲƁЄ ꍟ꓄ꃅꀤꂦᖘꀤꍏ
የቴሌግራም ቻናል አርማ gasha_tube — ጋሻ ƬƲƁЄ ꍟ꓄ꃅꀤꂦᖘꀤꍏ
የሰርጥ አድራሻ: @gasha_tube
ምድቦች: መዝናኛዎች
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 21.79K
የሰርጥ መግለጫ

News & Entertainment Channel
⭕️በቅርቡ በethio sat የቴሌቪዥን ስርጭታችንን ልንጀምር ዝግጁነታችንን ጨርሰናል⭐️
#በዚ_ቻናል_ያዘጋጀንላቹ_ፕሮግራሞች ።
➠ ዜናዎች ➠ መዝናኛዎች
➠ አስገራሚ ታሪኮች ➠ ስለ ጤናዎ አዳዲስ መረጃዎች
➠ የቢዝነስ አሳቦች ➠ አነቃቂ ምክሮች
➠የቴክኖሎጂ ዜናዎች
➠ ኢትዮጵያዊ የሆኑ እሴቶች በየቀኑ ለእናንተ
እናቀርባለን

Ratings & Reviews

2.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 10

2022-08-24 15:53:21
ከጭጋጉ ባሻገር!

የቀኑን ሙሉ የአየር ሁኔታ ጠዋት በምናየው ጭጋጋማ ሁኔታ ላይ ብቻ ተመርኩዘን መተንበይ፣ መገመትና መደምደም እንደማንችል ሁሉ የሕይወታችሁም ሁኔታ እንደዚያ መሆኑን አትርሱ፡፡ ምንም እንኳን የአሁኑ ሁኔታችሁ ጭጋግና ድብርት የተሞላበት ቢሆንም መለወጡ አይቀርም፡፡

ያልፋል! አይዟችሁ!

Eyob mamo
@gasha_tube
@gasha_tube
@gasha_tube
1.6K viewsЄαgℓє Advertisement, 12:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-24 11:23:06
አንዲት ሴት በአንድ ወቅት እንዲህ ተብላ ተጠየቀች፦
አዘውትረሽ ወደ እግዚአብሔር በመጸለይሽ ምን "ትርፍ" ታገኛለሽ?

እሷም መለሰች፡-
ብዙውን ጊዜ "ምንም አላገኘሁም" ይልቁንም "ነገሮችን አጣለሁ"
እናም ወደ እግዚአብሔር በመጸለይ ያጣችውን ሁሉ ጠቀሰች፡-
"ኩራቴን" አጣሁ።
"ትዕቢቴን" አጣሁ።
"ስግብግብነቴን" አጣሁ።
"ክፉ ፍላጎቴን" አጣሁ።
"ቁጣዬን" አጣሁ።
"ራስ ወዳድነቴን" አጣሁ።
"ተንኮለኛነቴን" አጣሁ።
"ምቀኝነቴን" አጣሁ።
"ፍትወትን" አጣሁ።
"የመዋሸት ደስታን" አጣሁ።
"የኃጢአትን ጣዕም" አጣሁ።
"ትዕግስት ማጣትን" አጣሁ።
"ተስፋ መቁረጥን" አጣሁ።

አንዳንድ ጊዜ የምንጸልየው አንድን ነገር ለማግኘት ብቻ ሳይሆን በመንፈሳዊ ህይወታችን እንድናድግ የማይፈቅዱልንን ክፉ ነገሮች እንድናጣ ነው።

ጸሎት ያስተምራል፣ ያጠናክራል እናም ይፈውሳል።
ጸሎት መልስ ይዞ ከመምጣቱ በፊት ለጸሎታችን መልስ ምቹ አድርጎ ይሰራናል።
"ጸሎት በቀጥታ ከእግዚአብሔር ጋር የሚያገናኘን ቻናል ነው"

“ሳታቋርጡ ጸልዩ፤ በሁሉ አመስግኑ፤ ይህ የእግዚአብሔር ፈቃድ በክርስቶስ ኢየሱስ ወደ እናንተ ነውና።”
— 1ኛ ተሰሎንቄ 5፥17-18
@gasha_tube
1.6K viewsЄαgℓє Advertisement, 08:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-23 18:55:56 How to make your life exponentially better:

- Read a new book every month
- Lift weights 3-4 times a week
- Ignore nonsense and gossip
- Listen more, talk less
- Learn from mistakes
- Focus on your goals
- Invest in yourself
- Wake up early
- Sleep enough
- Smile more
- Eat well


@gasha_tube
1.5K viewsЄαgℓє Advertisement, 15:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-23 12:17:49
"ችግርህን ብቻ ለመናገር ወደ ቤተክርስቲያን ትሄዳለህ ደስታህን ለመግለፅ ደግሞ ጭፈራ ቤት ትገባለህ። ለዚህ እኮ ነው፡ገነት የመግባት እድልህ የጠበበው"
ሮበርት ሙጋቤ

I am in love with the ideas of this man!
I cant stop reading his sayings
@gasha_tube
1.5K viewsЄαgℓє Advertisement, 09:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-23 00:11:11
Make:Chevrolet
Model: Captiva Premier
Year: Real 2022
Body Type:SUV
Transmission:9-Speed Automatic
Steering: Original Left Hand Drive
Engine:V4 1.5L Turbo
Drive Type:FWD
Fuel:Benzine
Fuel Economy:13.5KM/L
Colors: Ivory
Option: Full Option
Plate No.: Telalafi
Condition: Brand New
#Chevrolet #Captiva #Premier #SUV

Features:
R18 Premier Trim
Keyless go
Touchscreen
Power sensor
Off road
Push Start
Air conditioning
Bluetooth system
Sunroof
Power locks
Power seats / electric seats
Power windows
Power sunroof
Tuner / radio
USB
Apple CarPlay | Android Auto
Rear Camera
ABS
Airbags (front and sides)
Traction Control
Parking Sensors (front and rear)
TPMS
ISOFIX
DRK LED lights
Halogen headlamps
Roof rails
Exterior mirrors with direction signs
Adjustable electric control
Power folding
Fog lights (front & rear)
Body Kit
New Premier Shape

Price :4.7 Million Birr
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
          𝐂𝐀𝐋𝐋 𝐓𝐄𝐗𝐓     
(𝙴𝚃) 𝙰𝚐𝚎𝚗𝚝 𝟷: +251928025669
(𝚄𝚂) 𝙰𝚐𝚎𝚗𝚝 𝟸:   +17026883480  
TELEGRAM @ETHIO_CARS_TEAM
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬

◤ ◢◢◤ ◢◤◢◤𝘿𝙍𝙄𝙑𝙀
1.0K viewsЄαgℓє Advertisement, 21:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-15 12:25:49 የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት የዶ/ር ሙሉቀን ሀፍቱን የህግ ከለላ አነሳ

የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት ያለመከሰስ መብት ያላቸውን የምክር ቤቱ አባል የዶ/ር ሙሉቀን ሀፍቱን የህግ ከለላ በአብላጫ ድምፅ አንስቷል።

ምክር ቤቱ ውሳኔውን በ93 ድጋፍ እና በ6 ድምፀ ታእቅቦ አፅድቋል።

የከተማውን ኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂን በበላይነት የሚመራው የአዲስ አበባ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ቢሮ ሃላፊ የሆኑት ዶክተር ሙሉቀን ሀፍቱን የህግ ከለላ የፍትህ ሚኒስቴር ባቀረበው ጥያቄ መሰረት እንዲነሳ በአብላጫ ድምፅ አንስተዋል።

የፍትህ ሚኒስቴር የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት አባልና የአዲስ አበባ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ቢሮ ሃላፊ የሆኑት ዶክተር ሙሉቀን ሀፍቱ የህግ ከለላ እንዲነሳ ባቀረበው ጥያቄ መሰረት ነው ከለላው እንዲነሳ የወሰነው።

የህግ ይነሳልን ጥያቄው ከቤቶች እጣ አወጣጥ ጋር የተያያዘ መሆኑን የምክር ቤቱ አፈጉባኤ ወ/ሮ ቡዜና አልቃድር ፍትህ ሚኒስትርን ደብዳቤ ለምክር ቤቱ ባቀረቡበት ወቅት ተናግረዋል።

@gasha_tube
399 viewsЄαgℓє Advertisement, 09:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-13 18:43:58
የጋራ መኖሪያ ቤት ላይ የወጣው እጣ ውድቅ ተደረገ

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ20/80 እና የ40/60 የጋራ መኖሪያ ቤት እጣ ውድቅ አደረገ።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ለ25 ሺሕ 491 ያወጣው የ20/80 እና 40/6 ላይ እጣ የወጣበት ሲስተም ላይ የተአማኒነት ጉድለት እንደነበር በመረጋገጡ ነው የወጣውን ዕጣ ውድቅ ያደረገው፡፡

ከጋራ መኖሪያ ቤቶች ከዕጣ አወጣጥ ሥነ-ሥርዓት ጋር በተያያዘ የተለያዩ ጥቆማዎች በመቅረባቸው የኦዲት ሥራ የጀመረው ከተማ አስተዳደሩ በባንክ የተላከውና ለእጣ እንዲውል ወደ ኮምፒዩተር የተጫነው ዳታ ልዩነቶች መገኘታቸውን መግለጹ ይታወሳል::

@gasha_tube
717 viewsЄαgℓє Advertisement, 15:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-13 11:22:21
የሰላም አማራጭ አብይ ኮሚቴው ስራ መጀመሩን አስታወቀ

በሰሜን ኢትዮጵያ የተፈጠረው ችግር በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት የተቋቋመው አብይ ኮሚቴ ስራ መጀመሩን አስታውቋል፡፡

የጠቅላይ ሚኒስትሩ የብሄራዊ ደህንነት አማካሪ ሚኒስትር አምባሳደር ሬድን ሁሴን በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው በኩል እንዳስታወቁት፥የሰላም አማራጭ አብይ ኮሚቴው የመጀመሪያ ስብሰባውን አካሂዷል።

ኮሚቴው በአፍሪካ ህብረት መሪነት ለሚካሄደው የሰላም ውይይት የራሱን የአሰራርና ሥነምግባር አካሄድ ተወያይቶ መወሰኑንም አምባሳደር ሬድዋን ጠቁመዋል፡፡

አብይ ኮሚቴው በንዑሳን ኮሚቴዎች በመደራጃትም ኃላፊነት ተከፋፍሎ ስራውን መጀመሩንም አስታውቀዋል፡፡

በሰሜን ኢትዮጵያ ለተፈጠረው ችግር የሰላም አማራጮች እንዲታዩ እና የፌደራል መንግስቱን ወክለው በሰላም ውይይቱ ላይ የሚሳተፉ አባላት መመደባቸው ይታወሳል።

@gasha_tube
765 viewsЄαgℓє Advertisement, 08:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-13 00:15:15 ለትግራይ ክልል የመልሶ ማቋቋሚያ ፕሮጀክት የሶስተኛ ወገን የትግበራ ስምምነት ተፈረመ

 
የኢትዮጵያ መንግስት በትግራይ ክልል ለሚካሄደው የመልሶ ማቋቋሚያ ፕሮጀክት ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት የፕሮጀክቶች አገልግሎት ቢሮ ጋር የሶስተኛ ወገን የትግበራ ስምምነት ተፈራረመ።

ስምምነቱን የኢፌዴሪ የገንዘብ ሚኒስትር አቶ አህመድ ሺዴ እና የተመድ የፕሮጀክቶች አገልግሎት ቢሮ ተወካይ ወርቅነሽ መኮንን ተፈራርመውታል።ፕሮጀክቱ በኢትዮጵያ በጦርነት የተጎዱ ማኅበረሰቦችን መልሶ የማቋቋም ፕሮጀክት በሚል ዕቅድ የመንግስት ብሄራዊ ማገገሚያ ፕሮግራም አካል ሲሆን ከዓለም ባንክ በተገኘ የገንዘብ ድጋፍ በተመድ የፕሮጀክቶች አገልግሎት ቢሮ አማካኝነት የሚተገበር መሆኑን የገንዘብ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል።

ይህ ፕሮጀክት በግጭት ለተጎዱ የማህበረሰብ ክፍሎች የመሠረታዊ አገልግሎቶችን እና ለአየር ፀባይ ለውጥ የማይበገር የማኅበረሰብ መሠረተ ልማትን መልሶ መገንባት እና የማሻሻል ውጥን ያለው ነው።ከዚህ ባለፈም በኢትዮጵያ በጦርነት በተጎዱ አካባቢዎች የሚገኙ እና የፆታ ጥቃት ለደረሰባቸው ሴቶች የባለብዙ ዘርፍ ምላሽ አገልግሎቶት ተደራሽነትን የማሻሻል ግብን የያዘ ነው።

በስምምነቱ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የፕሮጀክቶች አገልግሎት ቢሮ በትግራይ ክልል የመልሶ መገንባት፣ መሠረታዊ አገልግሎቶችን ማሻሻል እና የአየር ንብረት መቋቋም የሚችል ማኅበረሰባዊ መሠረተ ልማት የመገንባት ተግባራትን ያከናውናል ተብሏል።በተጨማሪም ማኅበራዊ ተቋማትን በመደገፍ እና ከማኅበረሰቡ ጋር በመምከር ማኅበረሰቡ ለሚፈልጋቸው አገልግሎቶች ፈጣን ምላሽ የሚያገኝበትን ምቹ ሁኔታ ይፈጥራል ነው የተባለው።

በግጭት ምክንያት የተጎዱ መሠረታዊ አገልግሎት የሚሰጡ መሠረተ ልማቶች መልሰው አገልግሎት እንዲሰጡ መስራትም ቢሮው ከመንግስት ጋር የገባው ስምምነት አካል መሆኑ ተገልጿል።ቢሮው በትግራይ ክልል አሁን ያለው ሁኔታ እስከሚስተካከል እና መንግሥት በክልሉ መደበኛ አገልግሎት መስጠት እስከሚጀምር ድረስ ብቻ ቆይታ ይኖረዋል ተብሏል።


@gasha_tube
753 viewsЄαgℓє Advertisement, 21:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-11 22:30:17 የመዲናዋ አስተዳደሩ ሰሞኑን በወጣው የጋራ መኖሪያ ቤቶች ዕጣ የዳታ ማጭበርበር መከሰቱን አስታወቀ

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር  ሐምሌ 01 ቀን 2014 በወጣው የ20/80 እና 40/60 የጋራ መኖሪያ ቤቶች ዕጣ  የዳታ ማጭበርበር ድረጊት በመከሰቱ ሁኔታውን እያጣራ እንደሚገኝ እና በድርጊቱ የተጠረጠሩ ግለሰቦችን በቁጥጥር ስር  እያዋለ መሆኑን አስታውቋል፡፡

የከተማ አስተዳደሩ ማምሻውን ባወጣው መግለጫ እንዳስታወቀው ከዕጣ አወጣጥ ስነ-ስርዓት በኋላ የተለያዩ ጥቆማዎች በመቅረባቸው የኦዲት ሥራ ሲጀመር በባንክ የተላከውና ለእጣ እንዲውል ወደ ኮምፒዩተር የተጫነው ዳታ ልዩነት ተገኝቶበታል፡፡ በጉዳዩ የተጠረጠሩ ባለሙያዎች እና አመራር በቁጥጥር ሥር ሆነው ምርመራ እየተደረገ ይገኛል ብሏል፡፡ በእስካሁኑ የማጠራት ስራም ላልቆጠቡ ሰዎች እጣ መውጣትን ጨምሮ የተለያዩ የተዓማኒነት ጉድለቶች ታይተዋል ነው ያለው፡፡

ከዚህ በመነሳትም “የቤት ማስተላለፉን ሂደት ግልፅነት ለማስፈን ሲባል እና ውጤቱን የሚያዛባ ተግባር ሲያጋጥም መልሰን ኦዲት እንዲደረግ በገባነው ቃል መሰረት የተፈጠረውን ችግር ከጉዳዩ ገለልተኛ በሆኑ በሚመለከታቸው ተቋማት የማጣራት ስራ በመከናወን ላይ ይገኛል” ብሏል፡፡

@gasha_tube
929 viewsЄαgℓє Advertisement, 19:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ