Get Mystery Box with random crypto!

Ewnet Media

የቴሌግራም ቻናል አርማ ewnetmedia1 — Ewnet Media E
የቴሌግራም ቻናል አርማ ewnetmedia1 — Ewnet Media
የሰርጥ አድራሻ: @ewnetmedia1
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.06K

Ratings & Reviews

2.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2023-06-08 13:15:10 #Update

" ሕዝበ ሙስሊሙ ያቀረባቸውና የሚያቀርባቸው የመስጊድ ጥያቄዎች በፕላኑ መሠረት ምላሽ ይሰጣል " - አቶ ሽመልስ አብዲሳ

ከኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ጋር በተደረገው ውይይት በክልሉ ፕሬዝዳንት አቶ ሽመልስ አብዲሳ በኩል የተጠቀሱት ነጥቦች የሚከተሉት ናቸው ፦

1. ቀደም ብሎ በጉዳዩ ላይ ዉይይት አለመደረጉ ስህተት መሆኑን ገልጸዋል።

2. በተፈጠረው ሁኔታ ሕይወታቸውን ላጡት ሙስሊሞች ማዘናቸውን ገልጸዋል።

3. የሸገር ከተማ የሃይማኖትን እሴትን መሠረት አድረጎ እንደሚገነባ እና የእሰልምናን ጨምሮ የሌሎችም ቤተእምነቶችም ተቋማት በብዛት በሸገር ከተማ ፕላን ዉስጥ እንደተካተቱ።

4. አስፈላጊውን የቤተእምነት መሥሪያ መሬቶችን በፕላኑ መሠረት ለምዕመኑ እንደሚሰጥና በቆርቆሮ ሳይሆን የከተማዋን ፕላን የሚመጥን በርካታ ዘመናዊ መስጊዶች በከተማው እንዲሰሩ እንደሚፈልጉ።

5. በሸገር ከተማ ላይ በሀገር ደረጃ ሊጠቀስ የሚችል ትልቅና ዘመናዊ መስጂድና ለሌሎች እምነት ተቋማት መሥሪያ ቦታ እንደሚሰጥ።

6. በሸገር ከተማ ለኢስላማዊ ዩኒቨርሲቲ ግንባታ የሚሆን መሬት እንደሚሰጥ።

7. ሸገር ከተማ ከ20 እስከ 30 ሚሊዮን ነዋሪዎች ያላት፥ ዘመናዊና በፕላን ብቻ ግንባታ የሚካድባት ከተማ ሆኖ ለመግንባት ሕግ ወጥ ግንባታን መከላከል፥ የተገነቡትን #ማፍረስ_እንደሚቀጥል ለዚህ ሂደት የእምነት ተቋማት ተባባሪ እንዲሆኑ እንፈልጋለን ብለዋል።

8. አዲሱ የሸገር ከተማ ፕላን ወደ ተግባር እስኪገባ ድረስ ሙሉ ለሙሉ መኖሪያ ቤቶች ባልፈረሱባቸው አከባቢዎች ለሚኖሩ ሙስሊሞች በጊዜያዊነት የሚሰግዱባቸው መስጊዶች የኦሮሚያ ክልል መጅሊስና የሸገር ከተማ አስተዳደር በጋራ በመጋገር መስጂድ መሥሪያ ቦታ እንዲያዘጋጁ።

9. የሸገር ከተማ ማስተር ፕላን በመጪው ሀምሌ ወር ወደ ተግባር ማዋል ከመጀመሩ በፊት በማስተር ፕላኑ ለእምነት ተቋማት የተዘጋጀውን ስፍራዎችን የሙስሊም ተወካዮች ከክልሉ መንግስት ጋር በጋራ ቀድመው ፕላኑን እንዲመለከቱና እንዲያረጋግጡ፡፡

10. በሸገር ከተማ ሕዝበ ሙስሊሙ ያቀረባቸውና የሚያቀርባቸው የመስጂድ ጥያቄዎች በፕላኑ መሠረት ምላሽ እንደሚሰጥ።

11. ሸገር ከተማን ጨምሮ በመላው ኦሮሚያ ክልል ከዚህ ቀደም ሲደረግ እንደነበረው የእምነት ተቋማት እና የመቃብር ሥፍራ መስጠት እንደሚቀጥል።

12. በሸገር ከተማ ዉስጥ ካሉት ስምንት መቶ (800) የሁሉም እምነት ተቋማት መካከል 656(ስድስት መቶ ሀምሳ ስድስት) የሚሆኑት ከፕላን ዉጭ የተሠሩ በመሆናቸው እነዚህን የሚገነባውን ከተማ ፕላን የማይመጡትን የተለያዩ ቤተእምነቶችን ወደ በሕጋዊና ከተማውን በሚመጥኑ ተቋማት ለመተካት የሚደረገውን ሂደት የኦሮሚያ ክልል መጅሊስም ባለበት የኦሮሚያ ክልል የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ አቅሙን በማጠናከር በዉይይት የእምነት ተቋማቱ ራሳቸው መፍረስ ያለባቸውን እንዲያፈርሱ እንጂ ከአሁን በኋላ መንግስት በራሱ ማፍረስ እንደሚያቆም ገልጸዋል።

ምንጭ፦ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት
130 views10:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-08 13:15:10
127 views10:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-08 11:51:30
ከኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት በሸገር ከተማ በፈረሱ መስጂዶች ዙሪያ ከኦሮሚያ ክልል መንግስት ጋር የተደረገውን ውይይት ተከትሎ የተሰጠ መግለጫ
145 viewsedited  08:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-07 22:47:17
ኢቢሲ “ነጋድራስ” የተሰኘ የስራ ፈጠራ ውድድር ሊጀምር ነው።

የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን በዓመት 5 ሚሊየን ብር፤ በሶስት ወር 1 ሚሊየን ብር የሚያሸልም አዲስ የሥራ ፈጠራ ውድድር እንደሚጀምር አስታወቀ።

"ነጋድራስ" የተሰኘው ይህ የሥራ ፈጠራ ውድድር በየሦሰት ወራት የሚጠናቀቁ ምዕራፎች የሚኖሩት ሲሆን በየምዕራፉ 25 ተወዳዳሪዎች ይቀርቡበታል ተብሏል፡፡ በውድድሩ በዓመት 100 ተወዳዳሪዎችን ለማሳተፍ ታቅዷል፡፡

የውድድር ቅፁን ለማግኘት ይህን ማስፈንጠሪያ (ሊንክ) ይጠቀሙ https://www.ebc.et/NegadRasApplicationForm.aspx 
307 views19:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-07 22:37:27
የ ኢንተር ሚያሚ ደጋፊ ናችሁ ??

ታዲያ ምን ትጠብቃላችሁ ትክክለኛውን የ ኢንተር ሚያሚ ክለብ ቻናል አሁኑኑ Join ይበሉ።


https://t.me/+j51-y5dpf5RkYTc8
https://t.me/+j51-y5dpf5RkYTc8
174 views19:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-07 14:54:15 #Update

በአዲስ አበበ ከተማ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ም/ቤት ፤ በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ በኢማሞች ህብረት የአቋም መግለጫ ተሰጥቷል።

መግለጫው ፤ በኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት በሸገር ከተማ እየተፈፀመ የሚገኘዉን የመስጅድ ፈረሳ በመቃወም በአዲስ አበባ ከተማ በታላቁ አንዋር እና ኑር መስጅዶች ህዝበ-ሙስሊሙ ድምፅ በማሰማቱ ምክንያት በተከሰተዉ ችግር በሰዉ ሕይወት እና አካል ላይ ጉዳት መድረሱን አስትውሷል።

ከዚሁ ጋር በተያያዘ ብዙ ዜጎች በህግ ጥላ ስር ይገኛሉ ብሏል።

የኢማሞች ህብረት ፤ በሸገር ከተማ እየተካሄደ የሚገኘዉ የመስጆዶች ፈረሳ ፍፁም ተገቢ ባለመሆኑ የሚያወግዝ መሆኑን ገልጾ የሚመለከተው አካል አፋጣኝ ምላሽ እንዲሰጥ ጥያቄውን አቅርቧል።

በተጨማሪም የኢማሞች ህብረት በሸገር ከተማ እየተፈፀመ የሚገኘዉን የመስጅድ ፈረሳ እና ከዚህ ጋር በተያያዘ በምዕመናን ላይ የተወሰደዉን ተገቢ ያልሆነ እርምጃ በፅኑ አውግዞ ባለ 5 ነጥብ የአቋም መግለጫ አውጥቷል።

1. ከዛሬ ቀን ጀምሮ እስከ ዙልቂዕዳ ወር መጨረሻ ድረስ በሁሉም መስጅዶች ቁኑት እና ዱዓ አንዲደረግ ጥሪ አስተላልፏል።

2. በሁሉም መስጂዶች የፊታችን ጁሙዓ የኩጥባ ይዘት በሠላም፣ በአንድነት እና በሰብር ላይ እንዲያተኩር እና ህብረተሰቡ ይበልጥ በሚረዳው በአማርኛ ቋንቋ ዳዕዋ እንዲደረግ ጥሪ አስተላልፏል።

3. በነገዉ እለት ሐሙስ ዙልቂዕዳ 19 ፤ 1444 ዓ.ሂ ሙስሊሙ ማህበረሰብ በመፆም፤ በሰደቃ፣ በዱዓ እና በኢስቲግፋር ወደ አላህ በመቃረብ እና አላህ የተፈጠረውን ችግር እንዲያነሳልን እንዲለምን ጥሪ ቀርቧል።

4. በተፈጠረዉ ችግር ሕይወታቸዉ ያለፈ እና የተጎዱ ቤተሰቦችን ሙስሊሙ ማህበረስብ የአዲስ አበባ ከተማ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ባዘጋጀው የባንክ ቁጥሮች እንዲረዳ ጥሪ ቀርቧል።

5. የጁምዓ ሰላት በሠላም ተሰግዶ እንዲጠናቀቅ እና ሙስሊሙ ማህበረሰብ በሰላም ወደ ቤቱ እንዲመለስ ጥሪ ቀርቧል።
206 views11:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-07 14:53:53
187 viewsedited  11:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-07 13:38:49 ​​መንግስት ሂዩማን ራይትስ ዎች ያወጣው ሪፖርት ተቀባይነት የለውም አለ

መንግስት ሂዩማን ራይትስ ዎች ያወጣውን ሪፖርት አስመልክቶ ምላሽ ሰጥቷል፡፡

ምላሹም እንደሚከተለው ይቀርባል፡-

ሂዩማን ራይትስ ዎች የተባለው ድርጅት እ.ኤ.አ. ጁን 1 ቀን 2023 (ግንቦት 24 ቀን 2015 ዓ.ም) በሀገራችን በአንዳንድ አካባቢዎች ጉልህ የሆኑ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች መፈጸማቸውን የሚገልጽ መሰረተ ቢስ ሪፖርት አውጥቷል ብሏል።

በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል የነበረው ግጭት በርካታ አካባቢዎችን ለጉዳት ያጋለጠ ቢሆንም በልዩ ሁኔታ የተወሰነ አካባቢን መርጦ ደጋግሞ ሪፖርት በማዘጋጀት በሰብዓዊ መብት አጀንዳ ሽፋን የተለየ የፖለቲካ ተልዕኮዉን ለማሳካት ዓላማ ያደረገ በመሆኑ ተቀባይነት የለውም። የመብት ጥሰት ተፈጽሟል ለማለት የቀረበው ሪፖርት ይዘት ሲታይም ተገቢው ምርመራ ያልተደረገበት እና በበቂ ማስረጃ ያልተደገፈ ከመሆኑ አንጻር እምነት የሚጣልበት አይደለም።

በአጠቃላይ በድርጅቱ የቀረበው ሪፖርት የተዛባና በአካባቢው ያለውን ነባራዊ ሁኔታ የማይገልጽ፣ ለዘመናት አብረው የቆዩ ሕዝቦችን አብሮ የመኖር እሴት የሚያጠለሽ፣ በሕዝቦች መካከል ግጭት ቀስቃሽ የሆነና ሀገራችን እያደረገች ያለውን የእርቅ እና ምክክር ሂደት የሚያደናቅፍ አሉታዊ ተፅዕኖ ያለው ሪፖርት ሆኖ አግኝተነዋል።

በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል የነበረው ግጭት በአፋር፣ አማራ እና ትግራይ ክልሎች ውስጥ የሚኖሩ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ላይ ጉዳት ያደረሰ መሆኑ የሚታወቅ ሆኖ ሳለ ድርጅቱ አንድ አከባቢን ለይቶ በመምረጥ ሪፖርት ማውጣቱና ሪፖርቱም ሀገራችን የእርቅ ሂደቱን በተሟላ መልኩ በመተግበር ላይ እያለች በመሆኑ ድርጅቱ ድብቅ አጀንዳውን በሀገራችን ላይ ለማራመድና የዓለም አቀፉ ማህበረሰብ የተዛባ ዕይታ እንዲኖረው ለማድረግ እየሰራ ለመሆኑ ማሳያ ነው። ሀገራችን ኢትየጵያ የሰብአዊ መብቶችን ለማክበርና ለማስከበር የሚያስችሉ የህግ እና ተቋማዊ አደረጃጀቶች ያሏት ሀገር ስትሆን ይህንኑ ክትትል ለማድረግም እንደ የኢትየጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን ያሉ ነጻና ገለልተኛ ተቋማትን አቋቁማለች።

መንግስት የሰብአዊ መብት ጥሰቶችን ፈጽሞ የማይታገስ በመሆኑ ምክንያት በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል በነበረው ግጭት ተፈጸሙ የተባሉ የሰብአዊ መብቶች ጥሰቶችን የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን እና የተ.መ.ድ. የሰብአዊ መብቶች ከፍተኛ ኮሚሽነር ጽ/ቤት ጥምር የምርመራ ቡድን እንዲያጣሩ አስፈላጊውን ሁኔታ በማመቻቸትና ሪፖርቱም ሲወጣም በሪፖርቱ የተሰጡ ምክረ-ሃሳቦችን ለመተግበር የሚኒስቴሮች ጥምር ግብረ-ኃይል በማቋቋም መጠነሰፊ የሆኑ ተጎጂዎችን መልሶ የማቋቋም፣ ተፈጸሙ የተባሉ የመብቶች ጥሰቶች ምርመራ እና የህግ ማሻሻያ ስራዎችን ሲሰራ ቆይቷል።

ከዚህ በተጨማሪም በሰሜኑ ሀገራችን ክፍል የነበረውን ግጭት ለማቆም በፕሪቶሪያ የተደረሰውን የሰላም ስምምነት ለማስፈጸም ብሎም በሀገራችን የሚታዩ አለመግባበቶችን በዘላቂነት ለመፍታት የሽግግር ፍትህ ፖሊሲ አማራጮችን በማዘጋጀት በሀገር አቀፍ ደረጃ በርካታ ውይይት እየተደረጉ ይገኛሉ።

የቀረቡ የሽግግር ፍትህ ፖሊሲ አማራጮች ላይ ከመንግስታዊ ተቋማት፣ ከሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች፣ ከፖለቲካ ፓርቲዎች ተወካዮች እና ከአለም አቀፉ ማህበረሰብ አባላት ጋር ሰፊ ምክክሮችና የግብአት ማሰባሰቢያ ስራዎች ተሰርተዋል፤ እየተሰሩም ይገኛሉ፡፡ የሽግግር ፍትህ ሂደቱ የሰብአዊ መብቶች ጥሰት የፈጸሙ ወገኖች ላይ ተገቢው ማጣራትን በማድረግ ተጠያቂነትን ማስፈንን ጨምሮ እውነትን የማፈላለግ እና ተጎጂዎችንም መልሶ ለማቋቋም የሚያስችል ማእቀፍ ይፈጥራል። በተጓዳኝ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽኑ በሀገራችን የሚታዩ ግጭት እና አለመግባባቶችን ከስር መሰረታቸው በመለየት በዘላቂነት ለመፍታት እየተንቀሳቀሰ ይገኛል።

በሀገራችን ያሉ ችግሮችን ከመሰረቱ ለመቅረፍ በራስ አቅም እየተሰሩ ካሉ ስራዎች በተጨማሪ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን እና የተ.መ.ድ. የሰብአዊ መብቶች ከፍተኛ ኮሚሽነር ጽ/ቤት ጥምር የክትትል ቡድን ተደራጅቶ ግጭቱ በነበረባቸው አካባቢዎች ያለውን የሰብአዊ መብቶች ሁኔታ ክትትል እንዲያደርጉ በመጋበዝ መንግስት በሀላፊነት መንፈስ እየሰራ ባለበት ወቅት ይህንን ከግንዛቤ ሳያስገባ እና በቂ ማስረጃ በሌለበት ከላይ በተጠቀሰው ድርጅት የወጣው ሪፖርት ገንቢ ያልሆነና ፈጽሞ ተቀባይነት የሌለው ነው።
184 views10:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-07 12:27:39
በኮንስትራክሽን ሥራ ለመሠማራት ሥልጠና ያጠናቀቁ ባለሙያዎች ወደ ጀርመን ሊሠማሩ ነው።

በኮንስትራክሽን ሥራ ለመሠማራት የሚያበቃቸውን ሥልጠና ያጠናቀቁ የመጀመሪያውዙር ባለሙያዎች ወደ ጀርመን ሊሠማሩ መሆኑን የሥራ እና ክህሎት ሚኒስቴር አስታውቋል።

በሲቭል ኢንጂነሪንግ፣ በኮንስትራክሽን ማናጅሜንት ቴክኖሎጂ፣ በአርክቴክቸር እና መሰል ሙያዎች የመጀመሪያ ዲግሪ ከተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች የተመረቁ ተማሪዎች ስልጠናቸውን ሲከታተሉ ነበር ተብሏል።

ሥልጠናው፥ ከዛሬ ሦሥት ዓመት በፊት በቀድሞው ከተማ ልማት እና ኮንስትራክሽን ሚኒስቴር እና የጀርመን ኮንስትራክሽን ማኅበራት ፌዴሬሽን በጋራ እንደተጀመረ ነበር።

‘ጎኤቴ’ በመባል በሚታወቀው የጀርመን ባህል እና ቋንቋ ኢንስቲትዩት ሥልጠናቸውን ሲከታተሉ የነበሩት ከተለያዩ ክልሎች የተውጣጡ ከ50 በላይ የሚሆኑ ሠልጣኞች ናቸው።

ከዚህ ውስጥ 11ዱ ሥልጠናውን ካጠናቀቁ በኋላ የጀርመን ኮንስትራክሽን ፌዴሬሽን የሚፈልገውን መስፈርት አሟልተው የመጨረሻውን ፈተና በማለፍ ለጉዞ ዝግጁ ሲሆኑ 6ቱ ጀርመን ከሚገኙ አሠሪዎቻቸው ጋር የሥራ ውል ተፈራርመዋል።

ሥልጠናቸውን አጠናቀው፣ የመጨረሻው ምዘና አልፈው እና አስፈላጊውን የሥራ ትዕዛዝ ተቀብለው ወደ ጀርመን ሀገር ለመጓዝ ዝግጀታቸውን ያጠናቀቁ እንዲሁም በመሠልጠን ላይ የሚገኙትን ምሩቃንን የሥራ እና ክህሎት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታው አቶ ንጉሡ ጥላሁን ማነጋገራቸውን ሚኒስቴሩ ገልጿል።
185 viewsedited  09:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-06 12:30:54
ጽንፈኛ የፖለቲካ ኃይሎች ጫና እያሳደሩብኝ ነው ሲል ኢዜማ አስታወቀ

የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) ጽንፈኛ የፖለቲካ ኃይሎች ጫና እያሳደሩብኝ ነው ሲል ኢዜማ አስታወቀ።

ኢዜማ በፓርቲው ወቅታዊ ሁኔታ ላይ መግለጫ ሰጥቷል።

ፓርቲው ባለፉት 4 ዓመታት በጽንፈኛ የፖለቲካ ኃይሎችና የሀገሪቱን ሁኔታ ከግምት ማስገባት ያልቻሉ አካላት ጫና እያደረሱበት መሆኑን ገልጿል።

ከፓርቲው የለቀቁ 7 አመራሮች ባለፉት ሳምንታት ሰፊ የስም ማጥፋት እንደፈጸሙበትም ፓርቲው አስታውቋል።

ይህን በማድረግ ላይ ያሉት በፓርቲው 1ኛ ጠቅላላ ጉባኤ ወቅት ለአመራርነት ተወዳድረው የተሸነፉ አካላትን ጨምሮ በየጊዜው ከፓርቲው የሚለቁ አባላት መሆናቸውን የፓርቲው የድርጅት ጉዳይ መምሪያ ኃላፊ ዋስይሁን ተስፋዬ ተናግረዋል።

ፓርቲው “የሃሳብ ብዝሃነትን አይቀበልም” በሚል በለቀቁ አባላቱ የሚቀርበው ክስም ሐሰት መሆኑን ኃላፊው ገልጸዋል።
239 viewsedited  09:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ