Get Mystery Box with random crypto!

Ewnet Media

የቴሌግራም ቻናል አርማ ewnetmedia1 — Ewnet Media E
የቴሌግራም ቻናል አርማ ewnetmedia1 — Ewnet Media
የሰርጥ አድራሻ: @ewnetmedia1
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.06K

Ratings & Reviews

2.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 67

2022-07-10 14:28:54 በምዕራብ ሸዋ ዞን በአሸባሪው ሸኔ ላይ በተወሰደ እርምጃ በርካቶች መደምሰሳቸው ተገለጸ

በምዕራብ ሸዋ ዞን ባለፉት ሶስት ወራት በአሸባሪው ሸኔ ላይ በተወሰደ እርምጃ በርካቶች መደምሰሳቸውና እጅ መስጠታቸውን የዞኑ የአስተዳደርና ፀጥታ ጽህፈት ቤት አስታወቀ፡፡

በዞኑ አሸባሪውን ሸኔን ለመደምሰስ በተካሄደው ኦፕሬሽን የሽብር ቡድኑ በተለያዩ ጊዜያት የዘረፈው የሕዝብ ሀብት እየተመለሰ መሆኑንም አስታውቋል። በዞኑ ተጠናክሮ በቀጠለው ሕግ የማስከበር ኦፕሬሽን በተለያዩ ወረዳዎች 55 የአሸባሪው ሸኔ አባላት በሰላም እጃቸውን ሲሰጡ፤ 18ቱ መያዛቸውን የጽህፈት ቤቱ ኃላፊ ኦብሳ ሞቱማ ለኢዜአ ገልፀዋል፡፡

ኃላፊው እንዳሉት በተለይ ባለፉት ሶስት ወራት በተካሄደው ኦፕሬሽን 109 የሽብር ቡድኑ አባላት በቁጥጥር ስር የዋሉ ሲሆን 254 የሚሆኑት ላይ ደግሞ እርምጃ ተወስዶባቸዋል። የዞኑ ሕዝብ ከፀጥታ ሀይሉ ጋር በመቀናጀት ባደረገው ኦፕሬሽን ተዘርፈው የነበሩ 251 የቀንድ ከብቶችና 120 በጎችና ፍየሎች ለባለንብረቶቹ መመለሳቸውን አስታውቀዋል። እንዲሁም 44 ሞተር ሳይክሎች፣ አንድ ተሽከርካሪ፣ 2ሺህ 100 ሊትር ናፍጣ፣ ከህብረተሰቡ የተዘረፈ ከ2 ሺሕ ኩንታል በላይ የምግብ እህል፣ ከ600 ሺሕ ብር በላይ መያዙን ተናግረዋል፡፡
198 views11:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-09 16:24:25 ኢትዮጵያ የበርበራ ወደብን አልምቶ ለመጠቀም ስምምነቷን ከሶማሊላንድ ጋር ዳግም ማጽናቷ ተሰምቷል!

ኢትዮጵያ ቀደም ሲል የነበረውን በበርበራ ወደብ አልምቶ የመጠቀም መብቷ እንደማይነካባት በሶማሊላንድ ፕሬዚደንት በኩል ይፋ ሆኗል ሲል የምሥራብ የሬድዮ መጽሔት አስነብቧል፡፡

ከትናንት በስቲያ ወደ ሶማሊላንድ ከተማ ሐርጌሳ የኢትዮጵያ ልዑክ ማቅናቱንና የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ወ/ሮ ዳግማዊት ሞገስ እንዲሁም በአምባሳደር ሬድዋን ሁሴን የተመራ የልዑካን ቡድን ከሶማሊላንድ ፕሬዚደንት ሙሴ ቢሂ አብዲ ጋር መነጋገሩን የሶማሊላንድ ብሔራዊ ጣቢያ ተናግሯል፡፡

ኢትዮጵያ የበርበራን ወደብ ለማልማት ከሶማሊላንድና ከዲፒ ወርልድ ኩባንያ ጋር የጋራ ስምምነት እንደነበራት ይታወቃል፡፡ በዚህ ስምምነት 19 በመቶ የወደቡና ድርሻ የምትይዝ ሲሆን ባለፈው ወር ክፍያ ባለማጠናቀቋ ድርሻዋ ተነጥቋል ሲሉ የሶማሊላንድ የገንዘብ ሚኒስቴር መናገራቸውም ይታወሳል፡፡

ይህን የተናገሩት ሚኒስትር ጭምር በተገኙበት ፕሬዚደንታዊ የእራት ግብዣ የተደረገለት የኢትዮጵያ ልዑክ ስምምነቱ ባለበት አንደሚቀጥል ማስተማመኛ ተሰጥቶታል፡፡

(ኤሊያስ-መሰረት)
258 views13:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-09 12:14:04 #Afar 1443ኛው የኢድ አልአድሀ አረፋ በአል በአፋር ክልል ሰመራን ጨምሮ በዱብቲ፣ በሎግያ እና በተለያዩ የክልሉ ከተሞች እና አካባቢዎች በድምቀት ተከብሯል።
252 views09:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-08 21:21:51 #AddisAbaba

ነገ የሚዘጉ መንገዶች !

የዒድ አል-አድሃ በዓል የሶላት ፕሮግራም ተጀምሮ እስከሚጠናቀቅ የትራፊክ መጨናነቅ እንዳይፈጠር ፡-

- ከቦሌ አየር መንገድ ፣ በሚሊኒዬም አዳራሽ ወደ ለገሃር የሚወስደው መንገድ ደንበል ሲቲ ሴንተር ወይም ኦሎምፒያ አደባባይ አካባቢ

- ከመገናኛ ፣ በሃያ ሁለት ወደ ለገሃር እንዲሁም ከቦሌ መድሃኔአለም ፣ በአትላስ ሆቴል ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ኡራኤል ቤተ-ክርስቲያን አካባቢ

- ከአራት ኪሎ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ባሻ ወልዴ ችሎት ወይም ፓርላማ መብራት

- ከፒያሣ ወደ ለገሃር የሚወስደው መንገድ ቸርችል ጎዳና ቴዎድሮስ አደባባይ

- ከተክለ ኃይማኖት ፣ በሜትሮሎጂ ወደ ለገሃር የሚወስደው መንገድ ሜትሮሎጂ መስሪያ ቤት አካባቢ

- ከተክለ ኃይማኖት ፣ በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል የሚወስደው መንገድ ጥቁር አንበሳ የኋላ በር አካባቢ

- ከሲኒማ ራስ በጎላ ሚካኤል ወደ ለገሃር የሚወስደው መንገድ ጎላ ሚካኤል መስቀለኛ

- ከጌጃ ሰፈር ፣ ጤና ጥበቃ፣ ብሄራዊ ቲያትር የሚወስደው መንገድ ጎማ ቁጠባ

- ከባሻ ወልዴ ችሎት ፣ በኦርማ ጋራዥ ወደ ፍል ውሃ መስኪድ የሚወስደው መንገድ ንግድ ማተሚያ ቤት

- ከጎፋ ፣ በቂርቆስ ቤተ-ክርስቲያን ወደ ለገሃር አዲሱ መንገድ የሚወስደው መንገድ ቂርቆስ ቤተ ክርስቲያን መስቀለኛው ላይ

- ከጦር ኃይሎች ፣ ልደታ ፣ ፖሊስ ሆስፒታል ሜክሲኮ አደባባይ

- ከሳሪስ በጎተራ ወደ መስቀል አደባባይ የቀድሞ አራተኛ ክፍለ ጦር ይለፍ ለሌላቸው ተሽከርካሪዎች ከለሊቱ 10፡00 ሰዓት ጀምሮ ዝግጅቱ እስከሚጠናቀቅ መንገዶቹ ዝግ ይሆናሉ፡፡ ከሳሪስ በጎተራ ወደ ለገሃር የሚመጡ ከባድ ተሽከርካሪዎችም ከአጎና ሲኒማ ማለፍ እንደማይችሉ ተገልጿል።

(አዲስ አበባ ፖሊስ)
294 views18:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-08 13:44:59
ሽንዞ አቤ ተገደሉ።

የቀድሞ የጃፓን ጠ/ሚ ሺንዞ አቤ በጥይት ተመተው ተገደሉ።

ሺንዞ አቤ በምዕራባዊ ጃፓን በሚገኝና ናራ በተባለ ከተማ ጎዳና በአንድ ዕጩ ፖለቲከኛ ቅስቀሳ ላይ ንግግር በማድረግ ላይ ሳሉ ከበስተጀርባቸው በተተኮሰ ሁለት ጥይት ተመተው ነበር።

በኃላ ወደ ሆስፒታል ቢገቡም ህይወታቸዉን መታደግ አልተቻለም።

በቀድሞው የጃፓን ጠቅላይ ሚንስትር ላይ ተኩስ ከፍቶ ህይወታቸው እንዲያልፍ ያደረገው የ41 ዓመት ግለሰብ ሲሆን በፀጥታ ኃይሎች በቁጥጥር ሥር መዋሉም ተዘግቧል።

Video Credit : Mia
87 viewsedited  10:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-08 11:38:52
የዕጣ ማውጣት ሂደቱ ተጀምሯል።

የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ የጋራ መኖሪያ ቤቶችን ዕጣ ማውጣት ሂደትን ከሲስተም ባለሞያዎች ጋር በመሆን እያካሄዱ ነው።

(ውድ ቤተሰቦቻችን ፦ ዕጣው ወጥቶ ሲጠናቀቅ ሙሉ ዝርዝሩን እንልክላችኃለን)
119 viewsedited  08:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-08 11:17:53
#Update

ዛሬ የጋራ መኖሪያ ቤቶች ዕጣ የሚወጣበት ሲስተም ፦

- ዕጣ ሲወጣ በቀጥታ የአሸናፊዎችን ሙሉ መረጃ እና የቤት መረጃ ያሳያል።

- የዕጣ አወጣጥ ሲጠናቀቅ የአሸናፊዎችና የቤታቸውን መረጃ ያለ ሰው ንክኪ በቀጥታ ያሳያል ፤ ለህትመትም ያዘጋጃል።

- ዕጣ የወጣላቸው እድለኛ መሆን አለመሆናቸውን #በኦንላይን ማረጋገጥ ይችላሉ።

ውድ ቤተሰቦቻችን የ20/80 እንዲሁም 40/60 የጋራ መኖሪያ ቤቶች የዕጣ አወጣጥ ስነስርዓት መካሄዱን የቀጠለ ሲሆን በቀጣይም ያለውን ሂደት ተከታትለን እናሳውቃችኃለን።
116 viewsedited  08:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-08 10:45:10
#Update

የአዲስ አበባ ቤቶች ኮርፖሬሽን ዋና ዳይሬክተር አቶ ሽመልስ ታምራት ፦

" ... በዚህ ዙር የ20/80 ነባር ባለ ሶስት (3) መኝታ በ12ኛው ዙር ዕጣ ዝቅተኛ የቁጠባ መጠን ተወስዶ ለማጠናቀቅ የተቻለ በመሆኑ ነባር ባለ 3 መኝታ ብቁ ሆናችሁ የተገኛችሁ በቦርድ ውሳኔ የተቀመጠውን ላለመጣስ በዚህ ዕጣ #የማይካተቱ ሲሆን በቀጣይ በልዩ ሁኔታ ይስተናገዳሉ "

NB. በ20/80 የቤት ልማት ፕሮግራም የ1997 ተመዝጋቢዎች ብቻ ተሳታፊ ናቸው።
115 viewsedited  07:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-07 16:40:35
የ2015 የፌዴራል መንግስት በጀት 786 ነጥብ 6 ቢሊየን ብር ሆኖ ፀደቀ

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 786 ነጥብ 6 ቢሊየን ብር ሆኖ የቀረበለትን የ2015 የፌዴራል መንግስት በጀት አፀደቀ፡፡

ምክር ቤቱ ዛሬ መደበኛ ስብሰባውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በተገኙበት ያካሄደ ሲሆን፥ በ2015 የፌደራል መንግስት በጀት ላይ በምክር ቤቱ የተገኙ እና ከህዝብ የተሰበሰቡ ግብዓቶችን መሰረት አድርጎ በመወያየት ነው ያፀደቀው።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ፥ የ2015 የፌደራል መንግስት በጀት፥ ብድር መቀነስ፣ የበጀት ጉድለት መቀነስ፣ ያለን ሀብት በቁጠባ መጠቀም እና የዋጋ ንረትን ማረጋጋት የሚሉ ነጥቦችን የትኩረት አቅጣጫ እንዳደረገ ተናግረዋል።

እንደዚሁም መልሶ ማቋቋም፣ ሰብዓዊ እርዳታ እና የሀገር ደህንነት እና ሰላምን ማስጠበቅን በማጠናከር ላይ ትኩረት እንዳደረገም ተመልክቷል።
214 viewsedited  13:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-07 14:47:18
የትራንስፖርት ታሪፍ ላይ ጭማሪ ተደረገ

የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር ከሰኔ 29 ጀምሮ የነዳጅ መሸጫ ዋጋ ማስተካከያ ማድረጉ ይታወቃል፡፡

ሚኒሰቴሩ የተደረገውን የነዳጅ መሸጫ ዋጋ ማስተካከያ እንዲሁም የትራንስፖርት መለዋወጫ ጭማሪ ምክንያት በማድረግ የአገር አቋራጭ የህዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት ለሚሰጡ ተሸከርካሪዎች ላይ የትራንስፖርት ታሪፍ ማሻሻያ አድርጓል፡፡

(አዲስ ይፋ የተደረገው የትራንስፖርት ታሪፍ ከላይ ተያይዟል)
221 viewsedited  11:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ