Get Mystery Box with random crypto!

ኢትዮጵያ የበርበራ ወደብን አልምቶ ለመጠቀም ስምምነቷን ከሶማሊላንድ ጋር ዳግም ማጽናቷ ተሰምቷል! | Ewnet Media

ኢትዮጵያ የበርበራ ወደብን አልምቶ ለመጠቀም ስምምነቷን ከሶማሊላንድ ጋር ዳግም ማጽናቷ ተሰምቷል!

ኢትዮጵያ ቀደም ሲል የነበረውን በበርበራ ወደብ አልምቶ የመጠቀም መብቷ እንደማይነካባት በሶማሊላንድ ፕሬዚደንት በኩል ይፋ ሆኗል ሲል የምሥራብ የሬድዮ መጽሔት አስነብቧል፡፡

ከትናንት በስቲያ ወደ ሶማሊላንድ ከተማ ሐርጌሳ የኢትዮጵያ ልዑክ ማቅናቱንና የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ወ/ሮ ዳግማዊት ሞገስ እንዲሁም በአምባሳደር ሬድዋን ሁሴን የተመራ የልዑካን ቡድን ከሶማሊላንድ ፕሬዚደንት ሙሴ ቢሂ አብዲ ጋር መነጋገሩን የሶማሊላንድ ብሔራዊ ጣቢያ ተናግሯል፡፡

ኢትዮጵያ የበርበራን ወደብ ለማልማት ከሶማሊላንድና ከዲፒ ወርልድ ኩባንያ ጋር የጋራ ስምምነት እንደነበራት ይታወቃል፡፡ በዚህ ስምምነት 19 በመቶ የወደቡና ድርሻ የምትይዝ ሲሆን ባለፈው ወር ክፍያ ባለማጠናቀቋ ድርሻዋ ተነጥቋል ሲሉ የሶማሊላንድ የገንዘብ ሚኒስቴር መናገራቸውም ይታወሳል፡፡

ይህን የተናገሩት ሚኒስትር ጭምር በተገኙበት ፕሬዚደንታዊ የእራት ግብዣ የተደረገለት የኢትዮጵያ ልዑክ ስምምነቱ ባለበት አንደሚቀጥል ማስተማመኛ ተሰጥቶታል፡፡

(ኤሊያስ-መሰረት)