Get Mystery Box with random crypto!

Ewnet Media

የቴሌግራም ቻናል አርማ ewnetmedia1 — Ewnet Media E
የቴሌግራም ቻናል አርማ ewnetmedia1 — Ewnet Media
የሰርጥ አድራሻ: @ewnetmedia1
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.06K

Ratings & Reviews

2.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2023-06-06 12:15:36 የፌደራል መንግስት የ2016 ረቂቅ በጀት 801 ነጥብ 6 ቢሊየን ብር እንዲሆን የሚኒስትሮች ምክር ቤት ውሳኔ አሳለፈ

የሚኒስትሮች ምክር ቤት በዛሬው ዕለት ባካሄደው 21ኛ መደበኛ ስብሰባ የ2016 በጀት ዓመት የፌዴራል መንግስት ረቂቅ የበጀት አዋጅ ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳልፏል።

የፌዴራል መንግስት የ2016 በጀት በአስር ዓመቱ መሪ የልማት ዕቅድ የተቀመጡ ግቦችን ታሳቢ በማድረግ፣ የሀገር ደህንነት ከማስጠበቅ፣ በተፈጥሮና በሰው ሰራሽ ችግሮች ምክንያት የተፈናቀሉ ዜጐችን ከመርዳት፣ በህግ ማስከበር ዘመቻው የወደሙ መሰረተ ልማቶች መልሶ ከማቋቋም፣ በቀጣይ ሊኖር የሚችለውን የማህበራዊና የኢኮኖሚ ትራንስፎርሜሽን አቅጣጫዎችና ዓላማዎች ከማሳካት አኳያ የተቃኘ ሲሆን የ2016_2020 የመካከለኛ ዘመን የማክሮ ኢኮኖሚ እና የፊሲካል ማዕቀፍን መሠረት በማድረግ ተዘጋጅቶ የቀረበ ነው።
220 views09:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-05 22:46:40 የሰኔ ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ባለበት ይቀጥላል

የሁሉም ነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ከግንቦት 29 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ሰኔ 30 ቀን 2015 ዓ.ም ድረስ በግንቦት ወር ሲሸጥ በነበረው ዋጋ እንደሚቀጥል ተገለጸ።

በዚሁ መሠረት :-

1. ቤንዚን ……………………………………… ብር 69.52 በሊትር

2. ነጭ ናፍጣ……………………………………ብር 71.15 በሊትር

3. ኬሮሲን ……………………………………...ብር 71.15 በሊትር

4. የአውሮፕላን ነዳጅ ……………………….ብር 65.35 በሊትር

5. ቀላል ጥቁር ናፍጣ………………………….ብር 57.97 በሊትር

6. ከባድ ጥቁር ናፍጣ…………………………..ብር 56.63 በሊትር
237 views19:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-05 16:53:08 ኩዌት ከኢትዮጵያ የሚመጡ ሰራተኞችን ልትቀጠር  መሆኑን አስታወቀች።

ኩዌት ሰራተኞችን ከኢትዮጵያ ለመቀበል ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር መስማማቷ ተገልጿል። በሁለቱ መንግስታት በኩል መግባባት ላይ መደረሱን ተከትሎ በጥቂት ቀናት ውስጥ የጋራ የሥራ ስምምነት የሚፈረም ይሆናል።

የኢትዮጵያ መንግስት ከዚህ ቀደም ኩዌትን ጨምሮ   ከቤሩት፣ ከእስያ እና አውሮፓ ሀገራ ጋር የስምምነት ሥራዎች እንደተጀመሩ መግለጹ ይታወሳል።

ከስምምነቱ በኋላ በኢትዮጵያ የሚገኙ 600 የሚሆኑ የሰራተኛ አገናኝ ኤጀንሲዎች የሰው ኃይል በማቅረብ እንደሚሰሩ የተነገረ ሲሆን ሰራተኞች ቢያንስ ብቃቱ ከተረጋገጠ ተቋም የ3 ወር ስልጠና መውሰድ አለባቸው ተብሏል።

ኩዌት ከፍተኛ ቁጥር ያላቸውን የቤት ሰራተኞች የምታገኘው ከፊሊፒንስ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት መካከል የተፈጠረውን ውጥረት ተከትሎ ሀገሪቱ የሰራተኛ እጥረት እንዳገጥማት ኢትዮጵያውያን ሰራተኞችን ለመቀበል ማቀዷ ነው የተገለጸው።

የኢትዮጵያ መንግስት ከኩዌት መንግስት ጋር በተስማሙት መሰረት አንድ ሰራተኛ በወር 90 ኩዌት ዲናር ይከፈለዋል የተባለ ሲሆን ይህም በወቅታዊው የምንዛሬ ተመን ወደ 16 ሺ ብር የሚጠጋ ይሆናል።
256 views13:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-05 13:53:10 በደቡብ ክልል 1 ሺህ 131 የሚሆኑ የትምህርት ማስረጃዎች ሀሰተኛ ሆነው ተገኙ።

በደቡብ ክልል ከ17ሺህ በላይ የትምህርት ማስረጃዎች ላይ በተደረገ የማጣራት ስራ 1 ሺህ 131 ማስረጃዎች ሀሰተኛ ሆነው መገኘታቸው ተገልጿል፡፡

በተጨማሪም፥ በክልሉ 5 ሺህ 672 የብቃት ማረጋገጫ ላይ በተደረገ ፍተሻ 767 የብቃት ማረጋገጫዎች ሀሰተኛ ናቸው ተብሏል።

የቢሮው ኃላፊ አቶ ዘይኔ ቢልካ በተቋማት ከ23 ሺህ በላይ መዝገቦች ላይ ፍተሻ ማድረግ መቻሉን ገልጸው  ከ4 ሺህ በላይ ቅጥር፣ ዝውውር እና የደረጃ እድገት በህገ ወጥ መልኩ መፈጸሙን ጠቁመዋል።

ከዚህ ጋር በተያያዘም በክልሉ ከ2 ሺህ በላይ አመራሮች እና ባለሙያዎችን ተጠያቂ ማድረግ መቻሉን ኃላፊው መግለጻቸውን የክልሉ ኮሙኒኬሽን መረጃ ያመላክታል፡፡
249 views10:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-05 12:17:49 ሳዑዲ አረቢያ በሀምሌ ወር በቀን 1 ሚሊዮን በርሜል ከምታመርተው ነዳጅ እቀንሳለሁ ማለቷ የዋጋ ጭማሪ ስጋት ፈጥሯል

ሳዑዲ አረቢያ በቀን አንድ ሚሊዮን በርሜል ወደ አለም አቀፉ ገበያ የምትልከውን የነዳጅ ዘይት መጠን። እንደምትቀንስ አስታውቃለች ፣ ምክንያቱ ደግሞ የዋና ዋና ዘይት አምራች ሀገራት ኦፔክ ጥምረት የነዳጅ ዋጋን ቀንሷል በሚል የደረሰበትን ስምምነት ተከትሎ ነው ። በኦፔክ አባላት ሀገራት ዘንድ ከዚህ ቀደም ለሁለት  የምርት ቅነሳ በማድረግ ዋጋውን ከፍ ማድረግ አለመቻሉን በማንሳት የምርት ቅነሳዎች በሐምሌ ወር እንደምታደርግ ሳዑዲ አስታውቃለች ።

የነዳጅ ላኪ ሀገራት ድርጅት እና አጋር በሆነችው ሩሲያን ጨምሮ በዋና መሥሪያ ቤቱ ቪየና ከሰባት ሰዓታት ውይይት በኋላ በምርት ፖሊሲ ላይ ከስምምነት ላይ ደርሰዋል። በዚህም መሰረት እስከ 2024 መጨረሻ ድረስ የአቅርቦት ቅነሳውን በተጨማሪነት ለማራዘም ተስማምቷል። እስከ 1.4 ሚሊዮን በርሜል የነዳጅ ቅነሳ አቅርቦት ቅነሳ ሳዑዲ በቀጣይ እንደምታደርግ ይጠበቃል።

የሳዑዲ ኢነርጂ ሚኒስትር አብዱልአዚዝ ቢን ሳልማን በሰጡት መግለጫ ላይ እንደገለጹት "ይህ ለእኛ ታላቅ ቀን ነው,ምክንያቱም የስምምነቱ ጥራት ከዚህ በፊት ታይቶ የማይታወቅ ነው" ብለዋል። በዓለም አቀፍ ደረጃ ያልተጣራው ድፍድፍ ነዳጅ በበርሜል እስከ 87 ዶላር ከፍ ብሎ የነበረ ሲሆን በቅርብ ቀናት ውስጥ ግን በበርሚል ከ75 ዶላር በታች ዝቅ ብሏል።። በዩናይትድ ስቴትስ ድግሞ ድፍድፍ ነዳጅ በበርሜል ከ70 ዶላር በታች ወርዷል።
252 views09:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-04 13:46:33 ሰበር መረጃ!!

መንግስት "በምሥራቅ ጎጃም ዞን ደብረ ኤልያስ ወረዳ የሚገኘውን የሥላሴ ገዳም ከለላ በማድረግ መንግሥትን በትጥቅ ትግል ለመጣል ሲንቀሳቀሱ በነበሩ ጽንፈኛ ባላቸው ኃይሎች ላይ በተወሰደው እርምጃ በእስክንድር ነጋና በግብረዓበሮቹ  ለውጊያ ሲውል የነበረው ምሽግ መሰበሩንና
#በ200 ታጣቂዎችም ላይ እርምጃ መወሰዱን(መገደላቸውን) የጸጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረ ኃይል አስታወቀ!!


የፀጥታና ደህንነት የጋራ ግብረ ኃይል ግንቦት 26 ቀን 2015 ዓ.ም ምሽት ባወጣው መግለጫ <በደብረ ኤሊያስ ገዳም ሳካሂድ ቆይቻለሁ > ያለው < ወታደራዊ ዘመቻ ዓላማው እስክንድር ነጋ ላይ እርምጃ ለመወሰድ መሆኑን > አረጋግጧል። የጋራ ግብረሀይሉ በመግለጫው < በጎጃም ደብረ ኤልያስ ሥላሴ ገዳም መሽገው መንግሥትን በትጥቅ ትግል ለመጣል ሲንቀሳቀሱ > ነበሩ ባላቸው <እስክንድር ነጋና ግብረዓበሮቹ ላይ በተወሰደው እርምጃ ክልሉን የማተራመስ ሴራቸው ከሽፏል > ብሏል።

መግለጫው አክሎም < በምሥራቅ ጎጃም ዞን ደብረ ኤልያስ ወረዳ የሚገኘውን የሥላሴ  ገዳም ከለላ በማድረግ መንግሥትን በትጥቅ ትግል ለመጣል ሲንቀሳቀሱ በነበሩ ጥቂት ጽንፈኛ ኃይሎች ላይ እርምጃ ተወደስዷል> ሲል ይፋ አድርጓል።በዚህም <በእስክንድር ነጋና በግብረዓበሮቹ  ለውጊያ ሲውል የነበረው ምሽግ መሰበሩንና በ200 ታጣቂዎችም ላይ እርምጃ መወሰዱን > አስታውቋል፡፡ 

<የታጣቂ ቡድኑ መሪና አስተባባሪ  የነበረው > ያላቸው <እስክንድር ነጋና ጥቂት ግብረዓበሮቹ  ከአካባቢው ለመሰወር ቢሞክሩም በዋናነት የመከላከያ ሠራዊት እንዲሁም የአማራ ክልል የጸጥታ ኃይሎች በቁጥጥር ሥር ለማዋል እግር በእግር በመከታተል የተቀናጀ ኦፕሬሽን እያካሄዱ መሆኑንም > አመልክቷል

<ግለሰቡ[እስክንድር] ይህ እንዳልተሳካለት ሲያውቅ፤ መንግሥትን በኃይል ለመጣል በማቀድ የአማራ ሕዝባዊ ግንባር የተባለ አደረጃጀት በመፍጠር ሽመልስ ስማቸው፣ ሰውመሆን ወረታውና መንበሩ ካሴ ከተባሉ ግብረዓበሮቹ እንዲሁም ከሌሎች ጥቂት የክልሉ ጽንፈኛ ኃይሎች ጋር በመቀናጀትና በህቡዕ በመንቀሳቀስ  ታጣቂዎችን ሲመለምል፣ ሲያደራጅና ስምሪት ሲሰጥ ነበር > ሲል ወንጅሏል።

< ግንባሩን በሀገር ውስጥ ራሱ ሲመራ በውጭ ደግሞ ሻለቃ ዳዊት ወ/ጊዮርጊስ የተባለ ግለሰብ ያስተባብራል > ሲል የገለፀው መግለጫው፤ < ሁለቱ  በፈጠሩት ትስስር በክልሉ የትጥቅ ትግል በማድረግ ሕዝቡን ወደማያባራ ጦርነት ለማስገባት ሲንቀሳቀሱ ቆይተዋል > ሲል ከስሷል።

<በተለይ የገዳሙ አስተዳዳሪ የሆኑትን አባ ኤልሳን ለዚህ ሕገወጥ ተግባር ሲጠቀሙ ነበር > ብሏል። አስተዳዳሪውም ከሃይማኖቱ አስተምህሮ ውጭ በገዳሙ ውስጥ ሕገ-ወጥ እንቅስቃሴ እንዲደረግ ከመፍቀድ ባሻገር ከሌሎች መነኮሳት ጋር በማበርና የጦር መሣሪያ ጭምር በማንገብ ከጽንፈኛ ቡድኑ አባላት ጋር  ተሰማርተው ነበር > ሲል ወንጅሏቸዋል።

<የጥፋት ቡድኑ አባላት ሕገ ወጥ እንቅስቃሴውን እንዲያቆሙና በውይይት ወደ ሰላም እንዲመጡ ከክልል እስከ ወረዳ በሚገኙ አካላት ተደጋጋሚ ጥረት > እንዳደረገ የሚገልፀው መግለጫው ይህ ግን ፍሬያማ ሊሆን እንዳልቻለ አስታውቋል።

<200 የጽንፈኛ ቡድኑ አባላት ታጣቂዎች  መደምሰሳቸውነና የቀሩትም ከመማረካቸውና ከመሸሻቸው ውጪ፤ ቡድኑ የሐሰት ፕሮፓጋንዳ በሚነዛባቸው የማኅበራዊ ትስስር ገፆች በመንግሥት ጸጥታ አካላት በገዳሙና በምዕመናን ጉዳት እንዳደረሰ ተደርጎ የሚሠራጨው መረጃ ከእውነት የራቀ ነው > ሲል አጣጥሏል።

መግለጫው በመቋጫው <በቀጣይም ክልሉ ከጥቂት ጽንፈኛ ኃይሎች ጸድቶ ሰላማዊ እንቅስቃሴ እንዲሰፍን ለሚደረገው ሕግ የማስከበር እንቅስቃሴ ኅብረተሰቡ የጋራ ጥረቱንና አጋርነቱን አጠናክሮ እንዲቀጥል >  ጥሪ አስተላልፏል፡፡
284 views10:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-30 23:55:26 #Update

ነገ የሚከበረውን የላብ አደሮች ቀንን አስመልክቶ በአዲስ አበባ ከተማ ምንም አይነት የአደባባይ ኩነቶችና ሰልፍ እንዲሁም ፖሊስም ሆነ የአስተዳደር አካላት የሚያውቁት ምንም ዓይነት ስብሰባ የለም ሲል የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል።
83 views20:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-29 15:33:44 ሰበር ዜና

ግብረ ኃይሉ “በአማራ ክልል ስልጣንን በኃይል ለመቆጣጠር በሚጥሩ ኃይሎች ላይ እርምጃ እየወሰደኩ ነው” አለ!!


የጸጥታና የደኅንነት የጋራ ግብረ ኃይል “በአማራ ክልል ሕገ መንግስታዊ ሥርዓቱን በማፍረስ ክልላዊ ስልጣንን በኃይል ለመቆጣጠር በሚጥሩ ጽንፈኛ ኃይሎች ላይ እርምጃ እየወሰድኩ ነው” አለ።

የጸጥታና የደኅንነት የጋራ ግብረ ኃይል ባወጣው መግለጫ፤ ለአማራ ሕዝብ እንታገላለን በሚል በውስጥም በውጭም በመቀናጀት የራሳቸውን ህቡዕ አደረጃጀት የፈጠሩ አካላት ከመሰል ቡድኖች ጋር በመቀናጀት የሕዝቡን የቁርጥ ቀን ልጆች መልሰው እየበሉ ይገኛሉ። “እነዚህ ኃይሎች በትናንትናው ዕለትም የአማራ ክልል ብልፅግና ጽሕት ቤት ኃላፊ የሆነውን ግርማ የሺጥላን በመግደል አስነዋሪ ድርጊታቸውን አስመስክረዋል” ብሏል ግብረ ኃይሉ።

“በአማራ ክልል ሕገመንግስታዊ ሥርዓቱን በማፍረስም ክልላዊ ስልጣንን በኃይል ለመቆጣጠርም ሲጥሩ መቆየታቸውን” መግለጫው አመላክቷል።

የጸጥታና የደኅንነት የጋራ ግብረ ኃይልም ይህን ተከትሎ አስፈላጊና ሕጋዊ እርምጃ መውሰድ መጀመሩን ነው የገለጸው።

ይሄ ጽንፈኛ ኃይል በአማራ ክልል ሳይገደብ እንደ ሀገርም መንግስትን በኃይል ከስልጣን ለማስወገድ ያልፈነቀለው ድንጋይ የለም ያለው የጋራ ግብረ ኃይሉ መግለጫ÷ ከዚህ የጥፋት መንገዳቸው እንዲመለሱ በተደጋጋሚ የተሰጣቸውን ዕድል ከመጠቀም ይልቅ አሁንም በሕ ገወጥ ተግባራቸው መቀጠላቸውን አመልክቷል፡፡

በዚህ ህገ ወጥ ተግባራቸውም በቁጥጥር ስር ውለው ጉዳያቸው በሕግ እየታየ የሚገኙ በርካታ የቡድኑ አባላት መኖራቸውንም ግብረ ኃይሉ አስታውቋል፡፡ መንግስት በሀገሪቱ ብሎም በክልሉ የሕግ የበላይነትን የማረጋገጥ ኃላፊነት ያለበት በመሆኑ በሌሎቸም የሕገ ወጥ ቡድኑና ቡድኑን በገንዘብና በሐሳብ በህቡእ በሚደግፉ አካላትና ግለሰቦች ላይ የማያዳግም እርምጃ እየወሰደ እንደሚገኝ ነው ያስታወቀው፡፡

በሀገር ውስጥም ሆነ በውጭ የሚገኙ የፅንፈኛ ቡድኖቹ ደጋፊዎች በዚህ ብርቅዬ የኢትዮጵያ ልጅ ላይ የተፈፀመውን ግድያ ከመኮነን ይልቅ አሳፋሪ በሆነ መልኩ ገዳይ ቡድኖቹን ሲደግፉ ተስተውለዋል ብሏል መግለጫው፡፡ሐሳብን በሐሳብ ከማሸነፍ ይልቅ ከኢትዮጵያዊ ጨዋነት ባፈነገጠ መልኩ በአሰቃቂ ሁኔታ ግድያ የፈጸሙትን ፅንፈኛ ቡድኖች ሕዝቡ በአንድነት በማውገዝ ኢትዮጵያዊ ጨዋነቱን ሊያስመሰክር ይገባልም ብሏል፡፡

በአቶ ግርማ የሺጥላ ላይ የተፈፀመው አሰቃቂ ግድያ የፅንፈኛ ኃይሎቹን ትክክለኛ መልክና ገፅታ ለሕዝቡ በይፋ ያጋለጠ ነው ብሏል የደኅንነትና የጸጥታ የጋራ ግብረ ኃይል፡፡ መንግስት ለሕዝቡ ሰላምና ደኅንነት መረጋገጥ ግዴታውን ለመወጣት አስፈላጊውን እርምጃ መውሰድ የጀመረ በመሆኑ÷ ሕዝቡም ይሄንን ተገንዝቦ የፌደራል እና የክልል የፀጥታ አካላት ተጠያቂነትን ለማስፈን የጀመሩትን እንቅስቃሴ ጥቆማና መረጃ በመስጠት እንዲደግፍ ጥሪ አቅርቧል፡፡ የፅንፈኛ ኃይሎቹን አስነዋሪ ተግባር በመሸፋፈን በተለያዩ የማህበራዊ ትስስር ገፆች መሰረተ ቢስ ወሬዎችን ከሚያሰራጩ የማህበራዊ ሚዲያ አንቂዎች ሕብረተሰቡ ራሱን እንዲጠብቅ ግብረ ኃይሉ አሳስቧል፡፡
258 views12:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-29 13:29:33 የትምህርት ሚኒስቴር ፤ በመጪው ሀምሌ ወር ላይ በዩኒቨርሲቲዎች በኦንላይን ለሚካሄደው የመውጫ ፈተና 30 ሺህ ኮምፒውተሮች ዝግጁ መሆናቸውን አሳውቋል

ሚኒስቴሩ ፤ ከ240 ሺህ በላይ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የቅድመ ምረቃ ተማሪዎች የመውጫ ፈተና ለመስጠት ዝግጅት መጠናቀቁን ገልጿል። 

በዩኒቨርሲቲዎች የሚሰጠውን የመውጫ ፈተና የማያልፉ ተማሪዎች ድግሪ የማይሰጣቸው በመሆኑ ተማሪዎች ለሚሰጠው ፈተና ራሳቸውን አንዲያዘጋጁ ማሳሰቢያ ተላልፏል።

በሀምሌ ወር ከሚሰጠው ፈተና በፊት በግንቦት ወር መጨረሻ ላይ የሙከራ ፈተና እንደሚሰጥ ተገልጿል።

ሚኒስቴሩ ፤ በኦንላይን ፈተናው መሰጠቱ ኩረጃን ለማስቀረት፣ የወረቀት ወጪና ማጓጓዣን ለመቀነስ ይረዳል ብሏል።

ለፈተናው በአጠቃላይ ከ15 በላይ ኮርሶች በየትምህርት መስኩ ተወጣጥተው ዝግጁ መሆናቸውን የገለፀው ሚኒስቴሩ " የፈተናው ውጤት በኦንላይን ይፋ የሚደረግና ሚስጥራዊነቱ የተጠበቀ ይሆናል " ብሏል።

ፈተናውን የማያልፉ ተማሪዎች ያለገደብ በተደጋጋሚ የመፈተን እድል እንደሚኖራቸው በመመሪያ መቀመጡን ያስታወሰው ትምህርት ሚኒስቴር " የመውጫ ፈተናው የተለየ ዓላማ የሌለው እና የተማሩትን ብቻ የሚመዝን በመሆኑ ተማሪዎች ሳይደናገጡ እንዲዘጋጁ ለተማሪዎች ጥሪ አቅርቧል።

ሁሉም የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የመፈተኛ ጣቢያ እንደሚሆኑ ይፋ ተደርጓል።
251 views10:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-28 23:11:59 መንግስት የገቢ ግብርን እንዲቀንስ የሚጠይቅ ሰላማዊ ሰልፍ ለማካሄድ መታሰቡ ተገለጸ

የኢትዮጵያ ሰራተኞች ማህበራት ኮንፌደሬሽን (ኢሰማኮ) መንግስት የገቢ ግብርን እንዲቀንስ ለመጠየቅ አዲስ አበባን ጨምሮ በአምስት ከተሞች ሰላማዊ ሰልፍ ለማድረግ ማቀዱን ገልጿል።

የኮንፌደሬሽኑን ፕሬዝዳንት ካሳሁን ፎሎን ጠቅሶ አል ዐይን አማርኛ በሰራው ዘገባ ሰልፉ ከፊታችን ባለው የሰራተኞች ቀን (ሜይ ዴይ) በአዲስ አበባ፣ ድሬዳዋ፣ አዳማ፣ ሀዋሳ፣ ጅማና ሌሎችም ከተሞች እንደሚደረግ ተናግረዋል ብሏል።

የሰልፉ ዋነኛ ዓላማ የተባለውም፥ ቆይታ፤ ሰራተኛው በኑሮ ውድነቱ መኖር ባለመቻሉ የገቢ ግብርን እንዲቀንስ ለመጠየቅ ሲሆን በተጨማሪም ዝቅተኛ የደሞዝ ወለል እንዲወሰን፣ የኤጄንሲ ሰራተኞች 20/80 ክፍያ ገቢራዊት እንዲሁም የመደራጀት መብትን ለመጠየቅ ያለመ መሆኑን አንስተዋል።

ይህን ጥያቄ ለመንግስት የሚያቀርቡና ከተለያዩ የሰራተኛ ማህበራት ይውጣጣሉ የተባሉ በመቶ ሽህዎች የሚቆጠሩ ሰልፈኞች የፊታችን ሰኞ ድምጻቸውን ያሰማሉ ተብሎ ይጠበቃል ሲል ዘገባው አክሏል።

ሰልፉ ከሚመለከተው አካል ፈቃድ ስለማግኘቱ እንዲሁም የት እና በምን ሁኔታ ይካሄዳል የሚለው ዝርዝር መረጃ በዘገባው አልተካተተም።
276 views20:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ