Get Mystery Box with random crypto!

Ewnet Media

የቴሌግራም ቻናል አርማ ewnetmedia1 — Ewnet Media E
የቴሌግራም ቻናል አርማ ewnetmedia1 — Ewnet Media
የሰርጥ አድራሻ: @ewnetmedia1
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.06K

Ratings & Reviews

2.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 8

2023-04-09 13:40:54 #Update

የአማራ ክልል ፕሬዝዳንት ዶ/ር ይልቃል ከፋለ ፤ የአማራ ልዩ ኃይልን በተለየ መንገድ ትጥቅ ለማስፈታት እና ለመበተን የተወሰነ ውሳኔ የለም አሉ።

ይህን ያሉት ዛሬ በሰጡት መግለጫ ነው።

ዶ/ር ይልቃል ከፋለ ምን አሉ ?

- በሀገር ደረጃ በሁሉም ክልሎች የሚገኙ ልዩ ኃይሎችን በፌዴራል የፀጥታ ተቋማት ለማደራጀት ተወስኖ ወደ ትግበራ ተገብቷል።

- ውሳኔው በፌዴራል መንግሥት እና በክልል መንግሥታት ስምምነት የተወሰነ ሲሆን በሁሉም ክልሎች ተግባራዊ ይደረጋል።

- በአማራ ክልል ውሳኔውን ለመተግበር እየተሠራ ነው። ይህንን በተመለከተ ከጸጥታ መዋቅሩ ጋር ተወይይተናል።

- በአፈጻጸም ላይ በታየ ክፍተት እና በተነዛው ፕሮፖጋንዳ ችግሮች ተከስተዋል። ችግር እንኳን ቢኖር ተወያይቶ መፍታት ይቻላል።

- አብዛኛው የልዩ ኃይል አባል ውይይቱን አጠናቆ ውሳኔውን በካምፕ ሆኖ እየተጠባበቀ ነው።

- ልዩ ኃይዩ ትጥቅ የሚፈታና የሚበተን አይደለም ፤ በላቀ አደረጃጃት ኃላፊነቱን እንዲወጣ የሚያስችል ነው።

- ልዩ ኃይሉ ዓላማውን ተገንዝቦ ለበለጠ ተልእኮ ሊዘጋጅ ይገባል።

- የአማራ ሕዝብ በሁኔታው #ቅሬታ ውስጥ ገብቷል።ቅሬታው የመነጨው በተሟላ መንገድ ለሕዝቡ መረጃ ባለመድረሱ ነው።

- አደረጃጀቱ የሚደገፍ፣ ዘርፈ ብዙ ጥቅም ያለው የሀገርን አንድነት የሚያረጋግጥ ነው።

- አደረጃጀቱ የአማራን ክልል በተለየ መንገድ የሚጎዳ አይደለም።

- የአማራ ክልልን ልዩ ኃይል በተለየ መንገድ ትጥቅ ለማስፈታት እና ለመበተን የታለመ ዓላማ የለም።

- በተፈጠረ የመረጃ ክፍተት በአንዳንድ ከተሞች የሰላማዊ ሰልፍ እንቅስቃሴ፣ የአድማ ጥሪ እና የሰዎች እና የተሸከርካሪዎች እንቅስቃሴን የመገደብ አዝማሚያዎች እያታዩ ናቸው። አላስፈላጊ አካሄዶች አውዳሚ እና አክሳሪ እንጂ አትራፊ አይደሉም።

- የአማራ ክልል በጦርነት የከረመ ክልል ነው ፤ በጦርነቱ ምክንያት ሕዝቡ ተጎሳቁሏል፣ በጦርነቱ ምክንያት የተጎዳው ኅብረተሰብ እና መሠረተ ልማት ገና ማገገም አልቻለም ፤ ከአንደኛው ችግር ሳናገግም ወደ ሌላ ችግር መሸጋገር ሕዝቡን መጉዳት ነው።

- በመወያየት አላስፈላጊ ጉዳዮችን ማስቆም ይቻላል ፤ ሁሉም አውዳሚ የሆነውን ጉዳይ መከላከል ይገባዋል።

- ግጭት እንዳይፈጠር ወጣቶች እና የሃይማኖት አባቶች የሚመሰገን ሥራ እየሠሩ ናቸው።

- የአማራ ክልል ሕዝብ ጉዳዩን በውል በማጤን፣ በመመካከር እና ሊደርስ የሚችለውን ጉዳት አስቀድሞ በማሰብ ማስከን ይገባል።

- የአማራ ልዩ ኃይል በተለየ መንገድ የሚጎዳ ውሳኔ አልተወሰነም፣ ወጥና ሀገራዊ ውሳኔ ነው የተደረገው፣ በሁሉም ክልል የሚፈጸም ነው፣ ውሳኔው ለሀገር ግንባታ ታላቅ አስተዋጽዖ አለው።

- ከወቅታዊ ጉዳይ አንጻር የሚነሳው ጥያቄ ትክክል ቢሆንም አፈጻጸሙ ለሀገር የሚጠቅም መሆኑን መገንዘብ ይገባል።

- ከካምፕ የወጡ የልዩ ኃይል አባላት እንዲመለሱ ማድረግ ይገባል።

- የአማራ ሕዝብ ጉዳዩን በሰከነ መንገድ ማየት አለበት ፤ ችግሩ ዳር ወጥቶ ግጭት እንዳይከሰት እያደረጉ ላሉ አካላት ምስጋና ይገባል።

- የልዩ ኃይል አባላት ትጥቅ አትፈቱም፣ የምትበተኑበት ነገር የለም፣ ወደ ላቀ ተልእኮ ነው የምትሸጋገሩት።

- በመደማመጥ ችግሮቻችን እንፈታለን፣ የአማራን ጥያቄዎች እናስመልሳለን።

#AMC
251 views10:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-09 12:18:06 " ሆሣዕና '' (የዐብይ ፆም 8ኛ ሳምንት)

እንኳን አደረሳችሁ !

ሆሣዕና ከስምንቱ የዐቢይ ፆም እሁዶች አንዱና የመጨረሻው ሳምንት ተብሎ የሚጠራው ከትንሣኤ ቀድሞ የሚገኝ የሕማማት መግቢያ ዋዜማ ነው።

ሆሣዕና ማለት የቃሉ ትርጉም  " እባክህ አሁን አድን " ማለት ነው።

ዕለቱ ፤ ኢየሱስ ክርስቶስ በአህያ ውርንጭላ ላይ ተቀምጦ ወደ ኢየሩሳሌም ሲገባ የሚቀድሙትና የሚከተሉት ሕዝብ በተለይም ሽማግሌዎች እና ሕፃናት '' ሆሣዕና ለዳዊት ልጅ ፣ በጌታ ስም የሚመጣ የተባረከ ነው ፤ ሆሣዕና በአርያም '' በማለት በክብር መቀበላቸው የሚታወስበት ነው፡፡ 

ይህ ዕለት በቤተክርስቲያን ውስጥ ዘንባባ ተይዞ፣ እየተዘመረ እጅግ ልዩ በሆነ ሁኔታ ይታሰባል።

በዐብይ ጾም ከሰርክ ሆሣዕና ጀምሮ እስከ ትንሳኤ ሌሊት ያሉት ዕለታት የሚገኙበት ሳምንታት ሰሙነ ሕማማት ይባላል፡፡ ዕለታቱም የዓመተ ፍዳ ፣ የዓመተ ኩነኔ መታሰቢያ ናቸው፡፡

በዚህ ጊዜ በተለይ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ስርዓት ካህናት መስቀል በእጃቸው አይዙም፣ አያሳልሙም ፣ ይፍቱኝ ተብሎ ወደካህን አይቀረብም፤ ይህ ሳምንት የጌታን የመጨረሻው ስቃይ የሚታሰብበት ነው።
234 views09:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-07 21:10:57 #SpecialForce

" በመልሶ ማደራጀቱ ሂደት ምንም አይነት የሚበተን ኃይል የለም " - የአማራ ክልል መንግሥት

የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት በወቅታዊው የክልል ልዩ ኃይል መልሶ ማደራጀት ጉዳይ በተመለከተ ዛሬ ምሽት መግለጫ ሰጠ።

በዚህ መግለጫው የክልል ልዩ ኃይል አባላትን መልሶ የማደራጀቱ ተግባር በሁሉም ክልሎች የሚፈፀም ነው ብሏል።

ዓላማውም የኢትዮጵያን ሕልውናን የበለጠ የማበርታት መሆኑንና የጋራ ግብን ያነገበ ስለመሆኑ ገልጿል።

" ይህ ተግባር በተሟላ ሀገራዊ ጥናት ላይ የተመሰረተ፣ የህዝቦችን አንድነትንና ዘላቂ ሰላምን ለማረጋገጥ የተተለመ እንዲሁም የጋራ ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታን እውን ለማድረግ በሁሉም ክልሎች ታምኖበት የተገባበት ወሳኝ ተግባር ነው " ሲል ክልሉ አሳውቋል።

የአማራ ክልል ፤ የልዩ ኃይል አደረጃጀቶችን መልሶ የማደረጃት ወይም የሪፎርም ስራ በሁሉም የፌዴራልና ክልላዊ መንግስታት መሪዎች የጋራ ስምምነትና እንደ አንድ ሀገር አንድ ጠንካራ የፌዴራልና የክልል የፀጥታ መዋቅር እንዲኖረን ታስቦ የተለያዩ ማራጮች ለልዩ ኃይል አባላቶች ቀረቦ ኢትዮጵያንና ኢትዮጵያዊነትን በኩር በማድረግ የሚተገበር ሀገር አቀፍ ታሪካዊ ተግባር ነው ሲል አስገንዝቧል።

ተግባሩ ለሁሉም ክልል የልዩ ኃይል አደረጃጀቶች የሀገር መከላከያ ሰራዊት፣ የፌድራልና የክልል መደበኛ ፖሊስ፣ የፌዴራልና የክልል የማረሚያ ቤቶችን ፖሊስ አባል እንዲሆኑ አማራጮች ያቀረበ መሆኑን ክልሉ አመልክቷል።

የክልሉ መንግሥት " እውነታዉ ይሄ ሆኖ ሳለ አንዳንድ አካላት የአማራ ክልል ልዩ ኃይልን አየር ላይ እንዲበተን እየተደረገ ነው " የሚል ከእውነት የራቀ ፍፁም በተሳሳተ መንገድ ሀሰተኛ መረጃዎችን በማሰራጨት የአማራን ሕዝብ ውስጣዊ ሠላምና አንድነት የሚያደፈርስ፣ የልዩ ኃይሉን አንድነት የሚረብሽ፣ ባልተገባ መንገድ ጥርጣሬ ውስጥ እንዲገባ የሚያደርጉ እንቅስቃሴ ላይ ተጠምደው ይገኛሉ ብሏል።

ይህ ድርጊት ህዝቡን እና የልዩ ኃይል አባሎችን በተጨባጭ እየረበሸ እንደሚገኝ የሚገልፀው የአማራ ክልል ፤ " መንግስት ይህንን የመልሶ ማደራጀት ስራ የሚከውነው የልዩ ኃይላችንን የሰው ኃይል ለበለጠ ፋይዳ ላለው ተልዕኮ መልሶ የማደራጀትና ብቁ የማድረግ ሀገራዊና ክልላዊ ፋይዳ የማዘጋጀት ተግባር እንጅ በመልሶ ማደራጀቱ ሂደት ምንም አይነት የሚበተን ኃይል የሌለ መሆኑን ግንዛቤ ሊያዝበት ይገባል " ሲል አስረድቷል።

የክልሉ ህዝብም በአሉቧልታ ሳይታለልና ሳይደናገር እንደ አንድ ሕዝብ ያለውን ታሪኩን እና ሥነ ልቦናውን በሚመጥነው የኢትዮጵያዊነት ላእላዊ ማእቀፍ ጥላ ስር በመሰባሰብ ኢትዮጵያንና ኢትዮጵያዊ አንድነትን የማጽናት ሂደትን እንዲደግፍ ጥሪ አቅርቧል።
275 views18:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-07 20:49:27 በነገው ዕለት በአዲስ አበባ ከተማ ለሚካሄደው የጎዳና ላይ ኢፍጣር ዝግ የሚሆኑ መንገዶች ይፋ ሆኑ

የረመዳን ጾምን አስመልክቶ በነገው ዕለት በአዲስ አበባ ከተማ ለሚካሄደው የጎዳና ላይ ኢፍጣር ዝግ የሚሆኑ መንገዶች ይፋ ሆነዋል።

የኢፍጣር ፕሮግራሙ በሰላም እንዲከናወን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስፈላጊውን ዝግጅት ማጠናቀቁ አስታውቋል።

"ኢፍጣራችን ለወገናችን" በሚል መሪቃል የፊታችን ቅዳሜ መጋቢት 30 ቀን 2015 ዓ/ም በአዲስ አበባ ከባምቢስ በመስቀል አደባባይ እስከ ሜክሲኮ አደባባይ ባለው ጉዳና ላይ የኢፍጣር ፕሮግራሙ የሚካሄድ ይሆናል።

ፕሮግራሙ በሰላም ተጀምሮ እንዲጠናቀቅ ቅድመ ዝግጅት ማጠናቀቁን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል።

በዚህም ፕሮግራሙ በሚካሄድበት ወቅት የትራፊክ መጨናነቅ እንዳይፈጠር፡-

* ከቅዱስ ኡራኤል ወደ መስቀል አደባባይ
* ከኦሎምፒያ ወደ መስቀል አደባባይ
* ከአራተኛ ክፍለ ጦር ወደ መስቀል አደባባይ
* ከልደታ ከፍተኛ ፍ/ቤት ፣ በለገሃር ወደ መስቀል አደባባይ
* ከጎማ ቁጠባ ወደ መስቀል አደባባይ
* ከአራት ኪሎ ወደ መስቀል አደባባይ
* ከካዛንቺስ ወደ መስቀል አደባባይ
* ከጥቁር አንበሳ ሼል ወደ መስቀል አደባባይ
* ከቴዎድሮስ አደባባይ ወደ መስቀል አደባባይ
* ከንግድ ማተሚያ ቤት ወደ መስቀል አደባባይ
* ከሜትሪዎሎጂ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስዱ መንገዶች ከቀኑ 6:00 ሠዓት እስከ ምሽት 2:00 ሠዓት ድረስ ድረስ ዝግ እንደሚሆኑ አዲስ አበባ ፖሊስ ገልፆ፤ አሽከርካሪዎች ሌሎች አማራጭ መንገዶችን እንዲጠቀሙ መልእክቱን አስተላልፏል።
251 views17:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-07 14:56:42 #SpecialForce

" ሂደቱ ከትጥቅ ማስፈታት ጋር የሚገናኝ አይደለም " - ወ/ሮ ሰለማዊት ካሳ

መንግሥት እያካሄደ ያለው የልዩ ኃይል አባላትን መልሶ የማደራጀት መርሃ ግብር ትጥቅ ከማያስፈታት ጋር እንደማይገናኝ አሳወቀ።

የመንግሥት ኮሚኒኬሽን ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ ሰላማዊት ካሳ ፤ " የሁሉንም ክልል ልዩ ኃይል አባላት መልሶ የማደራጀት ስራ ነው የሚሰራው እንጂ ሂደቱ ከትጥቅ ማስፈታት ጋር የሚገናኝ አይደለም " ብለዋል።

የተጀመረው መልሶ የማደራጀት ሂደት የሀገር ሉዓላዊነትን ከማስጠበቅ፣ ከሀገር ውስጥ ሆነ ከውጭ የሚሰነዘርን ማንኛውም አይነት ጥቃት ከመከላከል አንፃር ጠንካራ የመከላከያ ኃይል ለመገንባት የሚያስችል ዕድል ነው ሲሉ ገልጸዋል።

" ህወሓትን በተመለከተ ፤ በፕሪቶሪያው ስምምነት መሰረት ትጥቅ የመፍታት ሂደቱ ያለማወላወል የሚፈፀም ነው " ያሉት ወ/ሮ ሰላማዊት " ሂደቱ ከሌሎች ሀገራዊ እቅዶች ጋር የሚገናኝ አይደለም / የሚጣረስም አይደለም እራሱን ችሎ በራሱ መርሀግብር የሚከናወን ነው " ሲሉ አስረድተዋል።

ይህንን ሂደት ዓለም አቀፍ ታዛቢዎች እየተከታተሉት መሆኑ መታወቅ አለበት ሲሉ አክለዋል።

ወ/ሮ ሰላማዊት የክልል ልዩ ኃይል አባላትን መልሶ ማደራጀት " በሁሉም ክልሎች በተመሳሳይ ወቅት እየተተገበረ ያለ ነው " ያሉ ሲሆን ሂደቱ በጥንቃቄ እና በጋራ መግባባት እየተመራ ያለ ነው ሲሉ አሳውቀዋል።

በሂደቱ በሁሉም ክልሎች ሰላም እና ደህንነትን ለማረጋገጥ በተለይ የፀጥታ ስጋት / የማህበረሰብ ጥያቄ ያለባቸው ቦታዎች ላይ ሀገር መከለከያ ሰራዊት ሁሉም ቦታዎች ስምሪት ወስዶ እየተንቀሳቀሰ ነው በዚህ ረገድ ክፍተት አይፈጠርም ብለዋል።

እየተካሄደ ባለው የመልሶ ማደራጀት ስራ በልዩ ኃይል ውስጥ ያሉ አባላት እንደምርጫቸው / እንደ ፍላጎታቸው ፦
- በሀገር መከላከያ ሰራዊት
- በፌዴራል ፖሊስ
- በክልል ፖሊስ አባልነት መካተት ይችላሉ ተብሏል።

ወደነዚህ የፀጥታ መዋቅሮች የሚቀላቀሉት ትጥቃቸውን እንደያዙ መሆኑ ተመላክቷል።

በዚህ ውስጥ መካተት የማይፈልጉ የልዩ ኃይል አባላት መብታቸው እንደሚጠበቅ እና ወደ መደበኛ ሲቪል ህይወት እንደሚገቡ መንግሥት የማቋቋም ስራ እና ድጋፍም እንደሚያደርግ ገልጿል።
258 views11:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-07 09:59:25 የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ያወጣው መግለጫ
245 viewsedited  06:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-06 21:41:25 ከመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት የተሰጠ ወቅታዊ አገራዊ መግለጫ
262 viewsedited  18:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-06 21:36:46
በአማራ ክልል ልዩ ኃይልን እና በፌደራል የጸጥታ ኃይሎች መካከል ውጥረት መፈጠሩ ተገለጸ

የአማራ ክልል ልዩ ኃይልን በግዴታ ትጥቅ ለማስፈታት እንቅስቃሴ በመጀመሩ በአማራ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች፤ በክልሉ ልዩ ኃይል እና በፌዴራል የጸጥታ ተቋማት መካከል ከፍተኛ ውጥረት መፈጠሩን የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) አስታወቀ፡፡

የክልሉን ልዩ ኃይል ያለ በቂ ዝግጅት፣ ውይይት፣ የጋራ መግባባትና መተማመን ሳይደረስ በድንገት እና ያለበቂ የጸጥታ ዋስትና ለማፍረስ መንግሥት ያሳለፈው ውሳኔ እና ውሳኔውን ለማስፈጸም እየሄደበት ያለው መንገድ ኃላፊነት የጎደለው መሆኑን አብን አስታውቋል፡፡

ጉዳዩ በአማራ ክልል ብቻ ሳይወሰን በአገር አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ አለመረጋጋት የሚፈጥር፣ ክልሉን እና ኢትዮጵያን ወደ ሌላ የቀውስ አዙሪት የሚከት አደገኛ አካሄድ መሆኑን አብን ለፌዴራሉ መንግሥትና ለአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት አሳስቧል፡፡

በመሆኑም፣ የገዥው ፓርቲ ሥራ አስፈጻሚ ውሳኔውን በአፋጣኝ እንዲቀለብስ እና ከአማራ ክልል መንግሥት እና ከክልሉ ሕዝብ ጋር በጉዳዩ ላይ ውይይት እና ምክክር እንዲደረግ አብን ጠይቋል፡፡

በካምፕ እና በግዳጅ ላይ ተሰማርተው የሚገኙ የአማራ ክልል የልዩ ኃይል ፖሊስ አመራሮች እና አባላት በሙሉ የተፈጠረው ሁኔታ ከቁጥጥር ውጭ እንዳይወጣ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ አሳስቧል፡፡ ልዩ ኃይሉ በጥንቃቄ እና መረጋጋት ራሱን እንዲጠብቅ እና የተፈጠረው ችግር በውይይት እና በመነጋገር እንዲፈታ አብን ጠይቋል፡፡
258 viewsedited  18:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-06 20:40:29 " የክልል ልዩ ኃይል አባላትን ወደ ሌሎች የጸጥታ መዋቅሮች የማስገባት ፕሮግራም በመላ ሀገሪቱ የሚተገበር ነው " - መንግስት

መንግሥት የሀገሪቱን ሉዓላዊነትና የግዛት አንድነት መጠበቅ የሚያስችል አንድ ጠንካራ የተማከለ ሠራዊት ለመገንባት አቅጣጫ ማስቀመጡን ዛሬ ምሽት ባወጣው መግለጫ ገልጿል።

በዚህ መሠረት የየክልሉን ልዩ ኃይሎች ወደ ተለያዩ የጸጥታ መዋቅሮች እንዲገቡ የሚያስችላቸውን ተግባራዊ እንቅስቃሴ ማካሄድ መጀመሩን አሳውቋል።

በሁሉም ክልሎች የሚገኙ የልዩ ኃይል አባላት እንደ ምርጫቸውና እንደ ፍላጎታቸው ፦
- በመከላከያ፣
- በፌደራል ፖሊስ ወይም በክልል ፖሊስ አባልነት መካተት ይችላሉ ብሏል።

በዚህ ሐሳብ ላይም ከልዩ ኃይል አመራሮችና አባላት ጋር ከመግባባት ላይ መደረሱን ገልጿል።

ቀደም ብሎም በሁሉም ክልል አመራሮች ጥናት ተደርጎበት፣ በተገኘው ውጤት ያለምንም ልዩነት ውሳኔው ስምምነት ተደርሶበታል ሲል አስታውሷል።

የክልል ልዩ ኃይልን በተለያዩ የጸጥታ መዋቅሮች የማካተት ውሳኔና የተግባር እንቅስቃሴ በጥናት ላይ ተመሥርቶ የሚከናወን ነው ያለው መንግስት " ይህ አካሄድ የኢኮኖሚ ዐቅማችን በማሰባሰብ የሠራዊታችንን የሥልጠና፣ የትጥቅ እና የኑሮ ሁኔታ ለማሻሻል ከፍተኛ ፋይዳ አለው፤ ይሄንን በመረዳትም በሁሉም ክልሎች ሂደቱ በመግባባትና በውይይት እየተከናወነ ይገኛል " ብሏል።

ነገር ግን በ " አማራ ክልል " በሚገኙ የተወሰኑ የልዩ ኃይል ክፍሎች ውስጥ ሂደቱን የሚያውኩ ተግባራት መታየታቸውን ገልጿል።

ይህ ሊሆን የቻለው ደግሞ የመልሶ ማደራጀት ሥራውንና ዓላማውን በአግባቡ ባለመረዳት፤ በሌላ በኩል የጥፋት አጀንዳ አራጋቢዎች ሆን ብለው በሚነዙት የሐሰት ወሬ በመጠለፍ ነው ሲል አስረድቷል።

መንግስት በመግለጫው ፤ " ከሚነዙት የሐሰት አጀንዳዎች መካከል፤ የመልሶ ማደራጀቱ መርሐ ግብር በአማራ ክልል ብቻ እየተካሄደ ነው፤ ሕወሐት ትጥቅ ሳይፈታ እንዴት የክልሉ ልዩ ኃይል ትጥቅ ይፈታል የሚሉትና ሌሎችም ይገኙበታል " ብሏል።

" የክልል ልዩ ኃይል አባላትን ወደ ሌሎች የጸጥታ መዋቅሮች የማስገባት ፕሮግራም በመላ ሀገሪቱ የሚተገበር ነው። " ያለው መንግስት " ሥራውም በሁሉም ክልሎች በተመሳሳይ ጊዜ እየተካሄደ የሚገኝ ነው። ሂደቱንም መንግሥት በጥናት፣ በዕቅድ እና በጥንቃቄ እየመራው ይገኛል። " ሲል አሳውቋል።

ወደ ሌሎች የጸጥታ መዋቅሮች የማስገባት ተግባር በሚፈጸምበት ጊዜ በክልሎች አስተማማኝ ሰላምና ጸጥታን ለማረጋገጥ የሀገር መከላከያ ሠራዊት በሁሉም ቦታዎች ሥምሪት መውሰዱ ተገልጿል።

በሌላ በኩል ሕወሐት በፕሪቶሪያው ስምምነት መሠረት ሙሉ በሙሉ ትጥቅ እንዲፈታ እየተደረገ መሆኑ ሊታወቅ ይገባል ብሏል።

" የሕወሐት ትጥቅ የመፍታት ሂደት በተፈረመው ስምምነት መሠረት ያለማወላወል የሚፈጸም እንጂ ከሌላ ሀገራዊ ዕቅድ ጋር የሚቀናጅም የሚጣረስም አይደለም። የሂደቱ ዋና ዓላማ የትኛውንም ልዩ ኃይል ትጥቅ ማስፈታት አይደለም። " ሲል መንግስት አስረድቷታ።

ዋናው አላማ ልዩ ኃይሉ ትጥቁን ይዞ እና የተሻለ ዐቅም ተፈጥሮለት በምርጫው መሠረት የክልል ፖሊስን፣ የፌደራል ፖሊስን ወይም የሀገር መከላከያ ሠራዊትን እንዲቀላቀል ማድረግ ነው። በዚህ ሂደት መካተት የማይፈልግ ማንኛውም የልዩ ኃይል አባል ካለ መብቱ ተጠብቆ ወደ መደበኛ የሲቪል ሕይወት እንዲገባ መንግሥት አስፈላጊውን የማቋቋም ሥራዎች ይሠራል ፤ እንዲቋቋምም ድጋፍ ያደርጋል ብሏል።

(ሙሉ መግለጫው ከላይ ተያይዟል)
246 views17:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-06 20:40:09
213 viewsedited  17:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ