Get Mystery Box with random crypto!

Ewnet Media

የቴሌግራም ቻናል አርማ ewnetmedia1 — Ewnet Media E
የቴሌግራም ቻናል አርማ ewnetmedia1 — Ewnet Media
የሰርጥ አድራሻ: @ewnetmedia1
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.06K

Ratings & Reviews

2.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 6

2023-04-15 20:08:53 የቀድሞው የሱዳን መከላከያ ሰራዊት ወደ ስራ ተመለሱ

በሱዳን ግጭት መከሰቱን ተከትሎ ጡረታ ወጥተው የነበሩ የቀድሞ የሀገሪቱ ብሔራዊ ጦር አባላት ወደ ስራ መመለሳቸው ተገልጿል።

በሱዳን ከዛሬ ረፋድ ጀምሮ በብሔራዊ ጦሩ እና በፈጥኖ ደራሽ ሀይሎች መካከል ጦርነት እየተካሄደ ይገኛል።

እስካሁን ንጹሀንን ጨምሮ በርካቶች ላይ ጉዳት መድረሱ ሲገለጽ ብሄራዊ ቴሌቪዥን፣ ኤርፖርት እና የጦር ካምፖችን ለመቆጣጠር ውጊያ እየተካሄደ ነው ተብሏል።
112 views17:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-15 15:44:40 " በሚዲያ ጥፋት የተጠረጠሩ ታሳሪዎች በሙሉ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ከእስር ሊለቀቁ ይገባል " - ኢሰመኮ

የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) የፖለቲካ ፓርቲዎች መሪዎችንና አባላትን፣ የሚዲያ አባላትንና የማኅበረሰብ አንቂዎችን ዒላማ ያደረገ እስር እና ወከባ በእጅጉ አሳሳቢ መሆኑን ገልጿል።

ኢሰመኮ በተለያየ ዓይነት ወንጀል ተጠርጥረው በፖሊስ ከተያዙ ሰዎች ውስጥ በተለይ የሚዲያ አባላትን፣ የተቃዋሚ ፖለቲካ ፓርቲ አመራሮችና አባላትን እንዲሁም የማኅበረሰብ አንቂዎችን (Activists) ጉዳይ በተመለከተ ክትትል ሲያደርግ የቆየ ሲሆን፣ ከእነሱም መካከል፦

ያለ ፍርድ ቤት ትእዛዝ በቁጥጥር ስር የዋሉ
የሚዲያ አዋጁን (የመገናኛ ብዙኃን አዋጅ ቁጥር 1238/2013) በሚጻረር መልኩ የታሰሩ
በተራዘመ ቅድመ-ክስ እስር ወይም ክስ ሳይመሠረትባቸው በእስር የቆዩ መኖራቸውን፣ በተወሰኑት ላይ የወንጀል ክስ ተመሥርቶ የነበረ ቢሆንም ክሱ በበቂ ማስረጃ የተደገፈ ባለመሆኑ በፍርድ ቤት ውሳኔ ውድቅ ተደርጎ ወይም በፖሊስ ውሳኔ ከተራዘመ እስር በኋላ በነጻ ወይም በዋስትና የተለቀቁ መኖራቸውን ኮሚሽኑ ተመልክቷል።

ኮሚሽኑ መጋቢት 21/2015 ዓ.ም. ባወጣው መግለጫ እስከ አሁን ድረስ በእስር ላይ ከሚገኙት የኦሮሞ ነጻነት ግንባር ፓርቲ አመራሮችንና የሌሎችም ተቃዋሚ ፓርቲዎች አባላት ላይ የሚደርሱ እንግልት እና እስሮችን ጠቅሶ መንግሥት የሰዎችን በሕዝባዊ ጉዳዮች ውስጥ የመሳተፍ መብታቸውን የሚገድቡ ተግባሮችን የመመርመርና ተጠያቂነትን የማረጋገጥ ኃላፊነት እንዳለበት ማሳሰቡን አስታውቋል።

በቅርብ ጊዜ በተቃዋሚ ፖለቲካ ፓርቲዎች ላይ ያተኮሩ እስሮች እና ማዋከብ እናት ፓርቲን፣ በባልደራስ ለእውነተኛ ዴሞክራሲ ፓርቲን እና የጎጎት ለጉራጌ አንድነት እና ፍትሕ ፓርቲን ይጨምራል።

በዚህ ወር ውስጥ በርካታ የሚዲያ አባላት መታሰራቸውን ኢሰመኩ ገልጿል።

ከፊሎች በእስር ወቅት ተገቢ ላልሆነ አያያዝ የተዳረጉ፣ ከፊሎች ከዚህ በፊት ለተመሳሳይ እስር ተዳርገው የነበሩ እና፣ ከፊሎችም ከተለያየ ጊዜ መጠን እስር በኋላ የተለቀቁ ናቸው።

መንግሥት የወንጀል ተግባሮችን ሁሉ የመከላከል፣ የመመርመርና ተጠያቂነትን የማረጋገጥ ኃላፊነት ያለበት መሆኑ እንደተጠበቀ ሆኖ፤ በፖለቲካ ፓርቲዎች መሪዎችና አባላት፣ በሚዲያ አባላትና  የማኅበረሰብ አንቂዎች  ላይ የሚያተኩር እስር ሐሳብን በነጻነት የመግለጽ፣ የመደራጀትና  በሕዝባዊ ጉዳዮች የመሳተፍ መብቶች ላይ የሚያስፈራራ፣ የሚያሸማቅቅ እና የሚገድብ ውጤት እንዳይኖረው ከፍተኛ ጥንቃቄ የሚሻ ነው ብሏል ኢሰመኮ።

በመሆኑም የመንግሥት የጸጥታ አካላት፦
- በፖለቲካ ፓርቲዎች መሪዎችና አባላት፣ በሚዲያ አባላትና በማኅበረሰብ አንቂዎች ላይ ካተኮረ እስርና ማዋከብ እንዲቆጠቡ፣
- በወንጀል የተጠረጠሩና በበቂ ሕጋዊ ምክንያት በቅድመ-ክስ ሊታሰሩ የሚገባቸው ሰዎች በሚኖሩበት ሁኔታም በሕግ በተመለከተው መንገድ ብቻ በጥብቅ ጥንቃቄ አንዲፈጸም
- የተጠረጠሩ ሰዎችን ሁሉ ከምርመራ በፊት ከማሰር እንዲቆጠቡ፣
- በመገናኛ ብዙኃን አዋጅ ቁጥር 1238/2013 መሠረት በመገናኛ ብዙኃን አማካኝነት የወንጀል ድርጊት በመፈጸም የተጠረጠረ ማንኛውም ሰው ወይም አካል፣ በወንጀል ሥነ-ሥርዓት ሕግ ድንጋጌዎች መሠረት ለተጨማሪ ምርመራ በእስር እንዲቆይ ሳይደረግ ክሱ በቀጥታ በዐቃቤ-ሕግ አማካኝነት ለፍርድ ቤት መቅረብ ያለበት መሆኑ በግልጽ የተደነገገ በመሆኑ፤ በዚሁ መሠረት እንዲፈጸምና  በሚዲያ አማካኝነት ተፈጽሟል በተባለ ወንጀል ተጠርጣሪ የሆኑ ታሳሪዎች በሙሉ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ከእስር እንዲለቀቁ ኢሰመኮ አሳስቧል።
141 views12:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-15 12:49:38 ከዛሬ ጀምሮ የክልል ልዩ ኃይል የሚባል አደረጃጀት የለም

ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ

ከዛሬ ጀምሮ የክልል ልዩ ኃይል የሚባል አደረጃጀት የሌለ መሆኑን የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ገለጹ።

የክልል ልዩ ሃይሎችን በፌዴራልና የክልል የጸጥታ ተቋማት መልሶ የማደራጀት ስራ የመከላከያ ጀነራሎች፣ ፌዴራል ፖሊስ እና የክልል የስራ ኃላፊዎች በተገኙ ተገምግሟል።

በመድረኩ ላይ የተገኙት የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ፤ የክልል ልዩ ሃይሎች እንደገና በመደራጀታቸው ህብረ ብሄራዊ ጠንካራ የጸጥታ ተቋም ይገነባል ብለዋል።

ኢትዮጵያ ከነበረችበት የጸጥታ ችግር በፍጥነት መውጣቷን የገለፁት ፊልድ ማርሻሉ፤ የፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት በመልካም ሁኔታ እየተከናወነ መሆኑንም ጠቁመዋል።

የክልል ልዩ ኃይሎች አደረጃጀት ህጋዊ አለመሆን፣ በክልሎች መካከል እንደ ስጋት መተያየት እንዲሁም ችግሮችን በሃይል ለመፍታት የሚደረገው እንቅስቃሴ አደረጃጀቱን ለመቀየር አስገድዷል ብለዋል።

በአሁኑ ወቅት በሁሉም ክልሎች መልሶ የማደራጀት ስራው ተጠናክሮ መቀጠሉን ጠቁመው "ከዛሬ ጀምሮ የክልል ልዩ ኃይል የሚባል አደረጃጀትና መዋቅር የለም" ብለዋል።

በመሆኑም የጸጥታ መዋቅሩ መከላከያ፣ ፌዴራል ፖሊስና የክልል ፖሊስ ሲሆን በክልል ልዩ ኃይሎች ስም ተልዕኮም ሆነ ግዳጅ የሚቀበል ኃይል አይኖርም ሲሉ አረጋግጠዋል።

ከዚህ በኋላ በመረጡት አደረጃጀት መሰረት ሁሉንም ወደ ተመደቡበት የማጓጓዝና ወደ ስልጠና የማስገባት ስራ ይከናወናል ብለዋል።
158 views09:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-15 10:39:19 የኦሮሚያ ልዩ ኃይልን መልሶ የማደራጀት ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የክልሉ አስተዳደርና ጸጥታ ቢሮ ገለጸ

የልዩ ኃይል አባላቱ ወደ ካምፕ እየገቡ መሆኑንም ጠቅሰዋል።

ኮሚሽነር ጀነራል አራርሳ ለኢፕድ እንደገለጹት፣ የክልሉን ሰላም የሚያውኩ ሸኔና ጽንፈኛ ኃይሎች መኖራቸው እሙን ቢሆንም የክልሉ ልዩ ኃይል ሪፎርም ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ ይደረጋል።

በአንጻሩ የክልሉ ሰላም እንደማንኛውም ክልል በክልሉ ሚሊሻና መደበኛ ፖሊስ የሚጠበቅ ሲሆን ከሚሊሻና መደበኛ ፖሊስ አቅም በላይ የሆነ ችግር ካጋጠመ ደግሞ መከላከያ በቅርበት የሚከታተል ይሆናል ብለዋል።

አንዳንዶቹ በሕዝቡ ዘንድ ጥርጣሬ ለመፍጠር ኦሮሚያ የልዩ ኃይል ሪፎርም እንደማያደርግ በሬ ወለደ ወሬ እየነዙ መሆናቸውን የተናገሩት ኮሚሽነር ጀነራሉ፤ ዳሩ ግን በሌሎች ክልሎች ተግባራዊ የሚደረግ የፌዴራል መንግሥት አቅጣጫ በኦሮሚያ ተግባራዊ የማይደረግበት ምንም ምክንያት እንደሌለና ነገ በተግባር የሚታይ ነገር በመሆኑ ንትርኩ እምብዛም ጠቃሚ አይደለም ብለዋል።

መጀመሪያውኑ የልዩ ኃይል አደረጃጀት በአንዳንድ ክልሎች ለተፈጠሩት የጸጥታ ችግሮች ጊዜያዊ እልባት ለመስጠት መጀመሩን ያወሱት ኃላፊው፤ በሂደት እንደ አገር የተስተዋለውን የጸጥታ ችግር ለመግታት ሁሉም ክልሎች ከመደበኛ ፖሊስ በተጨማሪ ልዩ ሀይል ማደራጀታቸዉን ተናግረዋል።

መከላከያና መደበኛ ፖሊስ እያለ በአንድ ሀገር ውስጥ መከላከያን የሚያክል ልዩ ኃይል መኖር ስጋት መሆኑ የህብረተሰቡ ጥያቄ በተደጋጋሚ ሲነሳ መቆየቱን ያስታወሱት ኮሚሽነር ጀነራል፤ ነገር ግን ከሕዝቡ ጋር ጥያቄ ሲያነሱ የነበሩ ኃይሎች መንግሥት ልዩ ኃይሉን በስታንዳርድ መሰረት ማደራጀት ሲጀምር “መንግሥት ልዩ ኃይልን እያፈረሰ ነው” በሚል ውዥንብር ሲፈጥሩ ማየት የሚያሳዝን ነው ብለዋል።

ሕዝቡ፣ እነዚህ ኃይሎች ፍጹም የትኛውንም ሕዝብ የማይወክሉ ሥራቸው ብጥብጥ መፍጠርና አገር ማፍረስ መሆኑን በመገንዘብ ክፉ ሃሳባቸውን እንዳይሸምት ጠይቀዋል።

እንደ ጀነራል አራርሳ ማብራሪያ፣ ሸኔና ጽንፈኞች በሕዝቦች መካከል መተማመን እንዳይኖር ብሎም ኦሮሚያ ሰላም እንዳትሆን በተደጋጋሚ ችግር እየፈጠሩ ይገኛሉ። መንግስት ለሸኔ የሰላም ጥሪ ማቅረቡን ተከትሎ ሸኔ የሰላም ጥሪውን ተቀብሎ ወደ ሰላም ቢመለስ እጅግ ጠቃሚ ነው። ካልሆነ ግን መንግሥት ሰላም ማስከበር ስለሚጠበቅበት እርምጃ መውሰዱ ይቀጥላል።

በተመሳሳይ፣ መልኩ ጽንፈኞች በሕዝቦች መካከል ጥርጣሬና ጥላቻ እንዲፈጠር በኦሮሚያ ክልል በተለያዩ ጊዜያት ዜጎች ላይ ጥቃት መፈጸማቸውን የገለጹት ኃላፊው፤ እነዚህ ኃይሎች በፈጸሙት ጥቃት ተጠያቂ ከማድረግ ባሻገር ከፌዴራል መንግሥት ጋር በመሆን ተመሳሳይ ጥቃት እንዳይፈጸም እንደሚሰራ አመልክተዋል።

ከዚህ በኋላ ችግር እየፈጠሩ መኖር የጊዜ ጉዳይ ካልሆነ በቀር ዘለቄታ እንደሌለው የተናገሩት ኃላፊው፤ ማንም ዜጋ ለእኩልነትና ለአንድነት ተገዥ ሆኖ ሌላው ጋር በሰላም የመኖር ባህል ማዳበር ግዴታው ነው ብለዋል።

መንግስት ከሶስት አመታት በፊት ባስቀመጠው አቅጣጫና በምርጫውም ወቅት ቃል በገባው መሰረት የአጠቃላይ የጸጥታ መዋቅሩ የሪፎርም አንዱ አካል የሆነውን የክልል ልዩ ኃይሎችን መልሶ የማደራጀት ስራ ሰሞኑን ተግባራዊ ማድረግ መጀመሩ ይታወሳል።

መልሶ ማደራጀቱ በአንድ በኩል በሁሉም የሃገሪቱ ክፍሎች ዘላቂ ሰላምን ለማጽናትና በክልሎች መካከል የሚታዩ አላስፈላጊ የኃይል ፉክክሮችን ለመግታትና ክልሎች ትኩረታቸውን በማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች ላይ እንዲያደርጉ ለማድረግ የታለመ ሲሆን፤ በሌላ በኩል ደግሞ ጠንካራ ህብረብሄራዊ የመከላከያና የፖሊስ ሰራዊትን ለመገንባት ትልቅ እርምጃ ነው።

ከዚህም ባሻገር ክልሎችን ለልዩ ኃይሎች ከሚያወጡት አላስፈላጊ ወጪ በመታደግ በጀታቸውን ለልማትና ለህዝብ ልማት እንዲያውሉ እድል የሚሰጥ እንደሆነ መገለጹ ይታወሳል።
177 views07:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-14 19:57:22
የ1 GB የኢንተርኔት ዳታ ስጦታ ከኢትዮ ቴሌኮም

ኢትዮ ቴሌኮም የስቅለት በአልን ምክንያት በማድረግ የ1 GB የኢንተርኔት ዳታ አገልግሎት ስጦታ ለደንበኞቹ አበርክቷል።

የትንሳኤን ጥቅል ገዝታችሁ ስትጠቀሙ 1GB ነፃ ታገኛላችሁ

እንደ ወግ ልማዳችን እንኳን አደረሰን የምንባባልበትን ልዩ የትንሳኤ የሞባይል ጥቅል እስከ 50% በሚደርስ ቅናሽ ከ1ጊ.ባ ዳታ ስጦታ ጋር ማቅረባችንን በደስታ እንገልጻለን!

ልዩ የትንሳኤ ጥቅሎቹን በቴሌብር ሱፐርአፕ ከተጨማሪ 10% ስጦታ ጋር እንዲሁም በማይ ኢትዮቴል እና *999# ለራስዎ በመግዛት እና ለወዳጅ ዘመድ በስጦታ በማበርከት በዓሉን በደስታ ያሳልፉ!
216 viewsedited  16:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-14 19:16:10
የሶማሊያው ፕሬዚዳንት ሀሰን ሼክ ማህሙድ ለይፋዊ የሥራ ጉብኝት አዲስ አበባ ገቡ

የሶማሊያው ፕሬዚዳንት ሀሰን ሼክ ማህሙድ ለሁለት ቀናት ይፋዊ የሥራ ጉብኝት ዛሬ አዲስ አበባ ገብተዋል።

ፕሬዚዳንቱ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ አደም ፋራህ እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ምስጋኑ አርጋ አቀባበል አድርገውላቸዋል።

በሚኖራቸው ቆይታ የሁለቱን አገራት ግንኙነት በሚያጠናክሩ ጉዳዮች ላይ ውይይት ይደረጋል ተብሎ ይጠበቃል።
213 viewsedited  16:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-14 10:37:52 የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድን የዶክተሬር ዲግሪ ለመሰረዝ በቂ ማስረጃ መኖሩ ተገለጸ

ሐሙስ ሚያዚያ 5 ቀን 2015 (አዲስ ማለዳ) ጥያቄ ሲነሳበት የነበረው የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ የዶክተሬት ዲግሪን ሊያሰርዝ የሚችል በቂ የጥናት “ስርቆት” ማስረጃ ማግኘቱን የዓለም ሰላም ፋውንዴሽን አስታወቀ፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ እ.ኤ.አ. በ2017 የዶክተሬት ዲግሪያቸውን በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሰላም እና ደህንነት ጥናት ተቋም (IPSS) ከተቀበሉበት ጊዜ አንስቶ፤ በዶክትሬት ዲግሪያቸው ላይ የሕጋዊነት ጥያቄዎች ሲነሱ እንደነበር ተቋሙ አስታውሷል፡፡

ፋውነዴሽኑ ከዚህ በፊት ጥያቄ ሲነሳበት የነበረውን የጠቅላይ ሚኒስትሩን የዶክተሬት ድግሪ ላይ ሰፊ ማጣራት በማድረግ ያገኘው ማስረጃ፤ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጠቅላይ ሚኒስትሩን ጥናት እንደገና ሊመረምር የሚችልበት በቂ ማስረጃ ማግኘቱን ጠቁሟል፡፡

ተቋሙ የዶክትሬት ዲግሪውን ለማገድ ወይም ለመሻር በቂ ነው ያለውን ማስረጃ ሲያቀርብ፤ በሌሎች ጥናቶች ላይ የተጠቀሱ ጽሑፎች በቀጥታና በጥቂት ማሻሻያ በጠቅላይ ሚኒስትሩ ጥናት ላይ ተደግመው መገኘታቸው በማስረጃ አስደግፎ አብራርቷል፡፡

የጠቅላይ ሚኒስትሩ የዶክተሬት መመረቂያ ፅሑፍ ላይ “የሌብነት” ምልክቶች እንዳሉ ባደረገው ማጠራት መታዘቡን ፋውንዴሽኑ ይፋ ባደረገበት ጽሑፍ ላይ፤ አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ጉዳዩን እንደገና ሊመለከት የሚችልበትን ሁኔታ ጠቁሟል፡፡

በዚህም ዩኒቨርስቲው ፕላጂያሪዝምን ወይም የሰው ጥናት ስርቆትን በሚከለክለው አሰራር እንደ ሌሎች ዩኒቨርስቲዎች የዶክትሬት ዲግሪያቸውን መሰረዝ እንደሚል ተጠቁሟል፡፡ በኹለተኛ ደረጃ እንደ አማራጭ የተጠቆመው፤ ጥናቱ እንደገና ተሻሽሎ ድጋሚ እንዲሰራ በማድረግ እሰከዚያው የዶክተሬት ዲግሪ ማገድ ነው፡፡

የመመረቂያ ጥናቱ “Social Capital and its Role in Traditional Conflict Resolution: The Case of Inter-religious Conflict in Jimma Zone of the Oromia Regional State in Ethiopia” በሚል ርዕስ የተሰራ ሲሆን፤ የጥናቱ ትኩርት ማኅበራዊ ካፒታል በባህላዊ የግጭት አፈታት ውስጥ ያለው ሚና ላይ ትኩረት ያደረገ ነው፡፡

“ፕላጂያሪዝም” የሰውን ጽሑፍ ወይም ሥራ መስረቅ ወይም የራስ አስመስሎ ማቀረብ የሚል ተቀራራቢ ትርጉም የሚሰጠው ሲሆን፤ የጠቅላይ ሚኒስትሩ ጥናትም ይህ አይነቱ ችግር እንደታየበት ፋይንደሽኑ ትናንት ይፋ ባደረገው ጽሑፍ አስታውቋል፡፡

የዓለም ሰላም ፋውንዴሽን በጠቅላይ ሚኒስትሩ የዶክተሬት ዲግሪ ላይ ያቀረባቸውን ማስረጃዎች ለመመልከት https://t.co/rnnNneqRIl
353 views07:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-14 10:37:47
219 views07:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-14 09:49:35
ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች
እንኳን ለብርሀነ ስቅለቱ በሰላም አደረሳችሁ!

መልካም በዓል!!
212 views06:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-13 12:55:19 #አሁን

በትግራይ ስለተፈፀሙ የሰብአዊ መብት ጥሰቶች እና የሽግግር ፍትህ በማረጋገጥ ሂደት ዙርያ ያለመ የውይይት መድረክ በመቐለ እየተካሄደ ይገኛል።

ውይይቱ ፤ የፍትህ ሚኒስትሩን ዶክተር ጌዲዮን ጢሞቲዮስ እና የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ዋና ኮሚሽነር ዶ/ር ዳንኤል በቀለን ያካተተ የፌደራል ልኡካን ቡድን እንዲሁም የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር የመንግስት ከፍተኛ ኃላፊዎች በተገኙበት እየተካሄደ እንደሚገኝ ድምፂ ወያነ ዘግቧል።
241 views09:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ