Get Mystery Box with random crypto!

Ewnet Media

የቴሌግራም ቻናል አርማ ewnetmedia1 — Ewnet Media E
የቴሌግራም ቻናል አርማ ewnetmedia1 — Ewnet Media
የሰርጥ አድራሻ: @ewnetmedia1
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.06K

Ratings & Reviews

2.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 10

2023-03-31 14:18:09 " ክስ መቋረጥን ተከትሎ ከእስር የመፍታት ስራ ተጀምሯል " - አቶ ጌታቸው ረዳ

በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ የሚመራ የልዑካን ቡድን አዲስ አበባ ውስጥ ከፌዴራል መንግስት ጋር እየመከረ ይገኛል።

ቡድኑ ከፌዴራል መንግስት ጋር እየተወያየ የሚገኘው በትግራይ መልሶ ማቋቋም እና ሌሎች ወሳኝ በሆኑ ጉዳዮች ላይ ስለመሆኑ ተነግሯል።

ከዚህ ባለፈ ልዑኩ በአዲስ አበባ ካሉ የትግራይ ተወላጅ የንግድ ማህበረሰብ ጋር የተወያየ ሲሆን የትግራይ ተወላጆች ትግራይን መልሶ ለመገንባት እና ሁለንተናዊ ችግሯን በመቅረፍ የበኩላቸውን ለማበርከት " ዝግጁ ነን " ብለዋል።

አቶ ጌታቸው ረዳ በዚሁ መድረክ ላይ የሲቪል እና ወታደራዊ አመራሮች ክስ መቋረጥን ተከትሎ ከእስር የመፍታት ስራ መጀመሩን አሳውቀዋል።

የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ልዑክ ከፌዴራል መንግሥት ጋር የሚያደርገው ምክክር መቀጠሉን የክልሉ ቴሌቪዥን / ትግራይ ቲቪ ዘግቧል።
298 views11:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-31 08:35:28 ሰበር ዜና

የክልል ልዮ ሀይል የተባለው ወታደራዊ አደረጃጀት መሉ በሙሉ እንዲፈርስ ትዕዛዝ ተላልፏል። ልዮ ሀይሉ ሲፈርስ ወደ መደበኛ መከላከያ ስራዊት የሚቀላቀሉ ሲሆን የቀረው መደበኛ ፖሊስ ሆኖ ይቀጥላል። ልዮ ሀይሉ የያዛቸውን የስራ ድርሻ ፌደራል ፖሊስና መከላከያ ስራዊት ይረከባቸዋል።
አንድ ፖሊስ ( በፌደራል ፖሊስ ዕዝ የሚመራ) አንድ የኢትዮዽያ መከላከያ ስራዊት ብቻ ሆነው ይቀጥላሉ።
308 views05:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-30 23:12:08
36 የህወሓት ከፍተኛ አመራሮች ተፈተዋል።

በወንጀል ተጠርጥረው ክሥ ቀርቦባቸው የነበሩ የህወሓት ሲቪል እና ወታደራዊ አመራሮችን ክሥ ማቋረጡን የፍትሕ ሚኒስቴር ከአስታወቀ በኋላ እነ ወ/ሮ ኬሪያ ኢብራሂም፣ ዶ/ር አዲስአለም ባሌማ፣ ዶ/ር አብርሃም ተከስተን ጨምሮ 36 ከፍተኛ አመራሮች ዛሬ መጋቢት 21 ቀን 2015 ዓ.ም ከእስር ተለቀዋል።

ከጠበቆቻቸው አንዱ የሆኑት አቶ ሀፍቶም ከሠተ ለአሜሪካ ድምፅ ሬድዮ በሰጡት ቃል ፤ ከእስር ተፈቺዎቹ፣ በማረሚያ ቤት መኪኖች፥ ሳሪስ፣ ፒያሳ እና ሲኤምሲ ወደሚገኙ ቤተ ሰዎቻቸው እንደተሸኙና ቤተ ሰዎቻቸወም አቀባበል እንደ አደረጉላቸው ገልጸዋል፡፡

በዛሬው ዕለት ከእስር የተፈቱት 16ቱ የህወሓት የሲቪል እና ወታደራዊ ባለሥልጣናት፣ ላለፉት ሁለት ዓመታት በዶ/ር ደብረጽዮን ገብረ ሚካኤል የክሥ መዝገብ ሥር እንደነበሩ ጠበቃው ገልጸዋል።

በሌተናል ጀነራል ታደሰ ወረደ የክሥ መዝገብ ሥር ጉዳያቸው በፍርድ ቤት ሲታይ የቆየው 20 ተከሣሾች እንደሆኑም ጠበቃው ለሬድዮ ጣቢያው ጠቅሰዋል።

Photo : File
287 viewsedited  20:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-25 20:54:41 #NewsAlert

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን " የሕገ ወጥ ቡድኑን የሹመት ይጽደቅልን " ጥያቄ #መቼም_ቢሆን የማትቀበለው መሆኑን አስታወቀች።

በዛሬ ዕለት በብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጅና በሕገ ወጥ መንገድ በተሾሙ የቀድሞ አባቶች መካከል ውይይት ተደርጎ እንደነበር ተሰምቷል።

ውይይቱን በተመለከተ የመንበረ ፓትርያርክ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ መግለጫ ሰጥቷል።

በመገጫውም ፤ ቅዱስ ሲኖደስ በቀኖና ቤተ ክርስቲያንና በሕገ ወጥ የተሾሙ ግለሰቦች በ5 የሥራ ቀናት ውስጥ ለመንበረ ፓትርያርክ ጠ/ጽ ቤት የይቅርታ ማመልከቻ እንዲያስገቡ ጥሪ አስተላልፎ እንደበር አስታውሷል።

ቢሆንም በይቅርታ ደብዳቤ አስገብተው ከተመለሱት ከአንዱ " አባ " ኃይለ ኢየሱስ ውጭ ሌሎች በይቅርታ ከመመለሰ ይልቅ ለውይይት እና ሕገ ወጥ ድርጊቱም #እንዲጸድቅላቸው መጠየቃቸውን ገልጿል።

" ቤተ ክርስቲያን የይቅርታ ቤት የሰላም ዓደባባይ የንስሓ ሰገነት በመሆኗ ለፍቅር ረጅም ርቀት በመጓዝ ከግለሰቦቹ ጋር በብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጅና በብፁዕ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሓፊ እንዲሁም በሌሎች ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት አማካኝነት ተወያይታለች " ያለው መምሪያው " ከዚህም አልፎ ቤተ ክርስቲያን የሀገር ሰላም የኢትዮጵያውያን የደኅንነት ኑሮ በእጅጉ ስለሚያሳስባት በብዙ ርቀት ለይቅርታ በሯን ከፍታ ስትጠባበቅ ነበረች " ብሏል።

ይሁን እንጂ በዛሬው ዕለት ወደ ጽርሐ መንበረ ፓትርያርክ የመጡ እና ሁሉንም እንወክላለን ያሉ 6 ግለሰቦች ከብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጅና ከብፁዕ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሓፊ ጋር የተወያዩ ሲሆን በውይይቱ ግን የተዘረጋው የቤተ ክርስቲያን የፍቅርና ይቅርታ እጅ በግለሰቦቹ ግን እንደመልካም አልታየም አሳውቋል።

ከዚህ ይልቅ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በተገኙበት ከተደረሱ 10 የስምምነት ነጥቦች መካከል በተራ ቁጥር 6 የሚገኘው ውሳኔ "በሕገ ወጥ መንገድ የተሾሙት "አባቶች" ወደ ቀደመ አገልግሎታቸው ይመለሳሉ" የሚል ቢሆንም ግለሰቦቹ ግን በመርሕ ደረጃ ስምምነቱን እንቀበለዋለን በአፈጻጸም ደረጃ ግን ቅዱስ ሲኖዶስ ሹመታችንን ያጽድቅልን" የሚል ጥያቄ ማቅረባቸውን መምሪያው በመግለጫው አስረድቷል።

ስለሆነም ከዚህ በኋላ ሕገ ወጦቹን በተመለከተ ቤተ ክርስቲያን የሚከተለውን ውሳኔ መወሰኗን መምሪያው አሳውቋል ፦

1ኛ. በየትኛውም መንገድ የጋራ ውይይት አይኖርም፤

2ኛ. ለይቅርታ የሚመጡ ከሆነ በቡድን ተሰባስቦ ሳይሆን በግለሰብ ደረጃ እንዲሆን፤

3ኛ. የይቅርታ ማመልከቻውን እያንዳንዳቸው ለመንበረ ፓትርያርክ ጠ/ቤተ ክህነት ጽ/ቤት ማስገባት ይኖርባቸዋል።

የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ በዚህና በሌሎች መሠረታዊ የቤተ ክርስቲያን ጉዳዮች ላይ ውሳኔ ለማሳለፍ 21/07/2015 ዓ/ም ምልዓተ ጉባኤ ጠርቷል።
108 views17:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-25 20:54:16
108 viewsedited  17:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-25 20:37:14
አቦይ ስብሃት ነጋ ለህክምና አሜሪካ ገብተዋል!

የህወሓት ቁንጮ በመባል የሚታወቁት እና በሰሜኑ ጦርነት ወቅት ተይዘው በእስር ላይ የቆዩት ስብሀት ነጋ በአሜሪካ ዲሲ ገብተዋል።

ፎቶ፣ ማህበራዊ ሚዲያ (ስብሃት ነጋ አሜሪካ ሲገቡ)
119 viewsedited  17:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-24 19:43:06 ቤተክርስቲያኗ ፦

1. በትግራይ ክልል ለሚገኙ አህጉረ ስብከት በጀት እንዳይላክ በቅዱስ ሲኖዶስ የተወሰነ አንድም ውሳኔ የሌለና በተፈጠረው የእርስ በእርስ ጦርነት ምክንያት የባንክ አገልግሎት በመቆሙ የተከሰተ የግንኙነት መቋረጥ መሆኑን ገልጻ በጀቱ በአጭር ጊዜ ውስጥ ከቆመበት ጊዜ ጀምሮ ከአህጉረ ስብከት ጋር በመነጋገር ለመላክ ዝግጁ መሆኗን ገልጻለች።

2. በክልሉ የተከሰተውን ጦርነት ተከትሎ የደረሰውን ጉዳትና ችግር ቅድስት ቤተ ክርስቲያኗ የተሰማትን ሐዘንና በችግሩም ወቅት ለአህጉረ ስብከቱ በበጀት ተደራሽ ባለመሆኗ ያስከተለው ችግር ያሳዘናት መሆኑን በቅዱስ ፓትርያርኩ ፊርማ በተጻፈ ደብዳቤ መግለጿን አስታውሳ የተከሰተው ጦርነት እንዲቆም በጸሎትና በምሕላ ስትማፀን መቆየቷ ወደጐን ተትቶና ተዘንግቶ የጦርነቱ ደጋፊ በሚያስመስል መልኩ የተሰጠው መግለጫ ተቀባይነት የሌለውና ፍፁም የማይገልጻት መሆኑን ገልጻለች።

3. በኦሮምያ ክልላዊ መንግሥት በምዕራብ ሸዋ ሀገረ ስብከት በዳጩ ሆሮ ባለወልድ ቤተ ክርስቲያን የተፈጸመውን ሕገወጥ ሲመተ ኤጲስ ቆጶሳት ፈተና ለመፍታትና የቤተ ክርስቲያኗን ሲኖዶሳዊ አንድነትን ለማጽናት በከፍተኛ ኃላፊነት እየተሰራ ባለበት ሁኔታ ለዚህ የቤተ ክርስቲያኗ ተልዕኮና ተቅማዊ አንድነት መጽናት በጸሎትም በሐሳብም ልንታገዝ ሲገባ  የእምነትና የታሪክ መሠረት በሆነው የትግራይ ሊቃውንት እንዲህ ዓይነት ድርጊት መከሰቱ ለአገሩም ሆነ ለሕዝቡ የሚመጥን አድራጐት ባለመሆኑ በአስቸኳይ እንዲቆም አሳስባለች።

4. በክልሉ ያለው አጠቃላይ መዋቅራዊ ችግሮችን በሚመለከትና አጠቃላይ በቤተ ክርስቲያኗ ላይ የተከሰቱትን ችግሮች ተወያይቶ ለመወሰን መጋቢት 21/2015 ዓ.ም የቅዱስ ሲኖዶስ አስቸኳይ ምልዓተ ጉባኤ የተጠራ መሆኑን ያሳወቀችው ቤተክርስቲያን በክልሉ በቅዱስ ሲኖዶስ ተመድበው በመሥራት ላይ የሚገኙ ሊቃነጳጳሳት በጥሪው መሠረት ምልዓተ ጉባኤው ላይ እንዲገኙና ክልላዊ ችግሩን ለመፍታት በሚደረገው ውይይት ላይ በመሳተፍ የበኩላቸውን ሚና እንዲወጡ ጥሪ አስተላልፋለች።

5. ቤተክርስቲያኗ በትግራይ የሚገኙ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን እናት ቤተ ክርስቲያን በአባቶቻቸው ሐዋርያዊ ተልዕኮ ጸንታ እስከአሁን መቆየቷን ገልጻ በአገራችን በተከሰተው ፖለቲካዊ ችግር ዘመናትን በጽናት የተሻገረችውን እናት ቤተ ክርስቲያን መዋቅራዊ አንድነቷ መፍረስ ሲኖዶሳዊ ልዕልናዋ መጣስ የሌለበት መሆኑን በጽናት እንደሚያምኑ እምነቷን በመግለጽ ለቤተ ክርስቲያኗ ተቋማዊ አንድነት አስፈላጊውን ዋጋ ሁሉ በመክፈል በጽናት ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ ጥሪ አቅርባለች።

6. የትግራይ ክልል ጊዜያዊ የሽግግር መንግስት በክልሉ ተፈጥሮ የቆየው ችግር በሰላማዊ መንገድ በውይይት በመፈታቱ ቤተ ክርስቲያን የተሰማትን ደስታ የገለፀች ሲሆን አስቀድሞ ችግሩ ከመከሰቱ በፊት አለመግባባቶች በውይይት እንዲፈቱ በብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ የተመራው የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ለቀረበው የሰላም ጥሪ እናት ቤተ ክርስቲያን ከፍተኛውን ሚና እንደተጫወተች አስታውሳለች። በተከሰተው ችግር የተፈጠሩ ጉድለቶች ካለ ጉድለቶችን ለማረምና ችግሮቹን ለመፍታት ቤተ ክርስቲያኗ ያላትን የጸና አቋም የገለፀች ሲሆን በክልሉ የተከሰተውን ተቋማዊ አንድነትን የሚጥስና ቀኖና የጣሰ አደረጃጀት እንዲቆም የበኩሉን ሚና በመጫወት ለቤተ ክርስቲያኗ ተቋማዊ አንድነት ኃላፊነቱን እንዲወጣ ጥሪ አስተላልፋለች።
202 views16:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-24 19:42:51
182 viewsedited  16:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-24 13:00:34 #Update

የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ ዛሬ በክልሉ ለሚገኙ መገናኛ ብዙሃን መግለጫ ሰጥተዋል።

በዚህም መግለጫቸው ፤ " የትግራይ ህዝብ እራሱን ከጥፋትና ውድመት ለማዳን ሁሉንም አይነት መስዋዕትነት ከፍሏል። " ያሉ ሲሆን " ጊዜያዊ አስተዳደሩም የትግራይ ህዝብ የታገለለትንና መስዋእትነት የከፈለበትን ዓላማ ለማሳካት ይሰራል " ብለዋል።

አቶ ጌታቸው አስተዳደራቸው የትግራይን ግዛታዊ አንድነትን ማረጋገጥ፣ የተፈናቀሉ ዜጎችን ወደ ቄያቸው መመለስ እና የህዝቡን ሁለንተናዊ ችግሮች በፍጥነት መፍታት ዋነኛው አላማው አድርጎ እንደሚሰራ በሰጡት መግለጫ መናገራቸውን ከክልሉ ቴሌቪዥን ያገኘነው መረጃ ያሳያል።

አቶ ጌታቸው ረዳ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደርን እንዲመሩ በህወሓት ማዕከላይ ኮሚቴ አብላጫ ድምፅ አግኝተው ከተመረጡ በኃላ የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ክልሉን እንዲያስተዳድሩ ርዕሰ መስተዳደር አድርገው እንደሾሟቸው ትላንት የጠ/ሚ ፅ/ቤት ማሳወቁ ይታወሳል።
210 views10:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-23 22:05:37 #አብን #ኢዜማ

የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኀበራዊ ፍትህ ፓርቲ (ኢዜማ) እና የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) በሀገራዊ ወቅታዊ የፖለቲካ ጉዳዮች ላይ የመጀመሪያ ዙር ገንቢ ውይይት ማድረጋቸውን በማህበራዊ ትስስር ገፆቻቸው ላይ አስታውቀዋል።

በቀጣይም #በሚያግባቡ_ሀገራዊ_ጉዳዮች ላይ ውይይቶችን ለማድረግና #የጋራ_አቋም ለመያዝ ከስምምነት ላይ መደረሳቸውንም ገልፀዋል።

ሁለቱ ፓርቲዎች የ " ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ / ህወሓት " ን ከሽብርተኝነት መዝገብ መሰረዝን በቅድሚያ የተቃወሙ ፓርቲዎች ናቸው።

ፓርቲዎቹ ተቃውሟቸውን በየተናጠል ባወጡት በመግለጫ አሳውቀዋል።

ይህ ከተሰማ ከሰዓታት በኃላ ነው ሁለቱ ፓርቲዎች በሚያግባቡ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ውይይቶችን ለማድረግና የጋራ አቋም ለመያዝ ከስምምነት ላይ እንደደረሱ የተነገረው።
84 views19:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ