Get Mystery Box with random crypto!

Ethio Construction

የቴሌግራም ቻናል አርማ ethioengineers1 — Ethio Construction E
የቴሌግራም ቻናል አርማ ethioengineers1 — Ethio Construction
የሰርጥ አድራሻ: @ethioengineers1
ምድቦች: የውስጥ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 24.69K
የሰርጥ መግለጫ

በኮንስትራክሽን ዘርፍ ላይ ከዲዛይን ,ቅየሳ ጀምሮ እስከ ፊኒሺንግ ሁሉንም
👷‍♂እናማክራለን
🏢ዲዛይን እናደርጋለን
📚ሙያዊ ድጋፍ እና እገዛ እናደርጋለን
🏗በጥራት እና በጊዜ ፍጥነት እንገነባለን
📲 0953138434(eng sintayehu melese) ወይም
ለሃሳብ እና ኣስተያየት
@Ethiocon143bot ይጠቀሙ

Ratings & Reviews

1.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

2

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 10

2023-03-12 19:44:42 #በሰው_መሬት_ላይ_ለተሰራ_ቤት_ሕጉ_ምን_ይላል

አንድ ሰው የራሱ ይዞታ ባልሆነ መሬት ላይ ወይም በሌላ ሰው መሬት ላይ ቤት ከሰራ ከህግ አንፃር እንዴት ይታያል ለሚለው የፍትሀ ብሔር ሕጉን ቁጥር 1170 ና 1179 እናያለን።

የአንድ የመሬት ይዞታ ባለቤት በይዞታው ላይ የመጠቀም መብቱ የራሱ ነው፡፡ ሌላ ሰው በዚያ መሬት ላይ ህንፃ ወይም ቤት ሊሰራ አይችልም።ልስራ ካለም ባለይዞታውን በማስፈቀድ መስራት አለበት አለበለዚያ ባለይዞታው በመሬቴ ላይ ቤት መስራት አትችልም ብሎ መቃወም ይችላል።

ነገር ግን መሬቴ ላይ ቤት መስራት አትችልም እየተባለና ባለይዞታው እየተቃወመ በእምቢተኝነት በሌላ ሰው መሬት ላይ ቤት የሰራ ሰው በሰው መሬት ላይ በሰራው ቤቱ አንዳችም መብት የለውም። ባለይ ዞታው በመሬቱ ላይ እየተቃወመው ቤት የሰራው ሰው ሁለት አማራጭ የህገ መፍቴዎች አሉት

1. ለቤቱን መስሪያ ያወጣውን ወጪ ሳይመልስለት ቤቱን ለቆ እንዲሄድ ማድረግ ይችላል።

2. ቤቱን የሰራው ሰው በራሡ ወጪ ቤቱን አፍርሶ እንዲሄድ ለመፍቀድ ይችላል፡፡ ባለመሬቱ በይዞታው ላይ ባለመኖሩ ወይም በሌላ ምክንያት በመሬቱ ላይ ቤት የሚሰራውን ሰው በወቅቱ መቃወም ባይችልም ቤቱ መሰራቱን እንዳወቀ ቤቱን ማስለቀቅ ወይም ማስፈረስ ይችላል።

➥ስለዚህ የራስ ያልሆነ ይዞታ ላይ ቤት መስራት አይቻልም። ይቻላልም ከተባለ ባለመሬቱ ፍቃደኝነቱን መግለፅ አለበት።በመሬቱ ላይ ሌላ ሰው ቤት ቢሰራ እንደማይቃወም በግልፅ ወይም በዝምታ መፍቀድ ይችላል።

በግልፅ ወይም በዝምታ በመፍቀድ (ተቃውሞ ሳያቀርብ) በመሬቱ ላይ ሌላ ሰው ቤት ሲሰራ ያልተቃወመ ወይም የተስማማ ባለይዞታ እንደ ፌደራል ሰበር.በመዝገብ.ቁጥር 30101.ቅፅ 6 እና በመዝገብ.ቁጥር.105125.ቅፅ 20 በተወሰነው ውሳኔ መሰረት ቤቱን የሰራው ሰው ባለቤት ይሆናል። የመሬቱ ባለይዞታም በእንዲ አይነት ሁኔታ ቤቱን ለሰራው ሰው የቤቱን ግምት ከፍዬ ላስለቅቅ ማለት አይችልም።

የፍ/ህ/ቁ.1179ን አስመልክቶ ሰበር በቅፅ 25 የመ/ቁ. 189608 የሰጠው ትርጉም
***
በፍ/ህ/ቁ. 1179 ላይ የተመለከተዉ ድንጋጌ ተፈፃሚነት የሚኖረዉ በባለይዞታዉ እና ይዞታዉን ይዞ ቤት በሰራ ሰዉ መካከል የታወቀ ግንኙነት በሌለበት ሁኔታ ብቻ በመሆኑ የባድ ቦታ ሽያጭ ዉል መፍረሰን ተከትሎ በቦታዉ ላይ የተሰራ ቤት ህጋዊ ዉጤትን አስመልክቶ ለጉዳዩ ተፈፃሚነት ያለዉ በፍ/ህ/ቁ. 1818 ነዉ።

ሳሙኤል ግርማ
የሕግ አማካሪና ጠበቃ
0911 190 299


https://t.me/ethioengineers1
2.3K viewsENG Sintayehu Melese, 16:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-10 21:33:53 አዲስ አበባ

ለህንጻ ግንባታ በተቆፈረና ውሃ ባቆረ ጉድጓድ ዉስጥ ዋና ለመዋኘት የገባ የ27 ዓመት ወጣት ህይወቱ ማለፉን የእሳት አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አስታውቃል።

የወጣቱን አስከሬን የኮሚሽኑ ዋናተኞች ከአንድ ሰዓት ፍለጋ በኃላ ማግኘታቸውን የኮሚሽኑ የህዝብ ግንኙነት ባለሙያ አቶ ንጋቱ ማሞ በተለይ ለብስራት ሬድዮ ተናግረዋል።

አደጋው ዛሬ ዓርብ  ከቀኑ 8 ሰዓት በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 3 ልዩ ቦታዉ ሚሊኒየም አዳራሽ ጀርባ ለህንጻ ግንባታ በሚል በተቆፈረና ዉሀ ባቆረ ጉድጓድ ዉስጥ ደርሷል።

በአዲስ አበባ ተቆፍረዉ ክፍቱን በሚተዉ ጉድጓዶች ዉስጥ ዋና ለመዋኘትና በሌሎች ምክንያቶች በ2015 ዓ.ም ብቻ የአራት ሰዎች ህይወት አልፏል።(ብስራት ሬዲዬ)


https://t.me/ethioengineers1
2.4K viewsENG Sintayehu Melese, edited  18:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-10 07:41:14
The quality that illuminates
The energy of design for the people and for the environment.

Giulio Vinaccia
Product Designer
Italian Design Ambassador 2023
in Ethiopia

Registration is Mandatory
Use the link below
https://cutt.ly/N8PipmK
To attend the event.

Friday, Afternoon
March 10, 2022
04:00 pm - 06:00 pm

The Urban Center | @TheUrbanCenter
In Front of St.Estifanos Church,
Women federation building ground floor.

#Architecture #Italian #product #Designer #Awardwinner #TUC #TheUrbanCenter
545 viewsENG Sintayehu Melese, 04:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-01 11:02:11
የኮተቤ መንገድ ይሄን ሁሉ አደጋ የሚያስተናግደው በምን ምክንያት ይሆን ??

በአንድ መንገድ ላይ በተሰራ በአጭር ግዜ ውስጥ ተደጋጋሚ አደጋዎችን በተመሳሳይ መልኩ ከተከሰተ ችግሩ የአሽከርካሪዎች ሳይሆን የመንገዱ ዲዛይን ላይ ነው።

የኮተቤው መንገድ ላይ እየሆነ ያለው ይህ ነው።


https://t.me/ethioengineers1
1.8K viewsENG Sintayehu Melese, 08:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-01 10:37:52
በዳሎል ኮሌጅ የሚሰጠውን አድቫንስድ ኳንቲቲ ሰርቬይንግ ስልጠና ለመውሰድ የተመዘገባችሁ ተማሪዎች እሁድ የካቲት 17 ከጠዋቱ 3:00 ሰዓት ሳሪስ ካዲስኮ አጠገብ በሚገኘው ፍሬሕይወት ትምህርት ቤት እንድትገኙ እናስታውቃለን።

ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር 0911439855 ይደውሉ።
1.8K viewsENG Sintayehu Melese, 07:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-01 10:36:08
የጨረታ ማስታወቂያ

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ዲዛይንና ግንባታ ስራዎች ቢሮ በተለያዩ ወረዳዎች ለሚያሰራቸው ጤና ጣቢያዎች በሀገር ውስጥ ግልፅ ጨረታ ህጋዊና ብቁ ተጫራቾችን አወዳድሮ ለመቅጠር ይፈልጋል፡፡
ስለሆነም ይህ ጨረታ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት ተከታታይ 30 ቀናት (Calendar Day)ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ዲዛይንና ግንባታ ስራዎች ቢሮ 8ኛ ፎቅ ምሕንድስና ግዥ ዘርፍ የማይመለስ ብር 1000 (አንድ ሺህ)በመክፈል መውሰድና መወዳደር እንደምትችሉ እናሳውቃለን፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ዲዛይንና ግንባታ ስራዎች ቢሮ የካቲት 22/2015 ዓ/ም


https://t.me/ethioengineers1
1.8K viewsENG Sintayehu Melese, edited  07:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-27 14:13:49
"የአድዋ ዜሮ ዜሮ ፕሮጀክት በመጭው ጥቅምት ሙሉ በሙሉ ተጠናቆ ወደ ስራ ይገባል" - የአዲስ አበባ የትላልቅ ፕሮጀክቶች ግንባታ ጽህፈት ቤት
****

የአድዋ ዜሮ ዜሮ ፕሮጀክት ጥቅምት ተጠናቆ ሙሉ በሙሉ ወደ ስራ እንደሚገባ የአዲስ አበባ የትላልቅ ፕሮጀክቶች ግንባታ ጽህፈት ቤት አስታወቀ፡፡

የጽህፈት ቤቱ የኮንትራት አስተዳደር ዳይሬክተር ኢንጂነር ዳዊት ጥበቡ በተለያዩ ውጣውረዶች ውስጥም ቢሆን ፕሮጀክቱን 78 ነጥብ 2 በመቶ ማድረስ ተችሏል ብለዋል፡፡

በተያዘለት ጊዜ እንዲጠናቀቅም በከፍተኛ ተሳትፎ ስራዎች እየተሰሩ መሆናቸውን ዳይሬክተሩ ተናግረዋል፡፡

ፕሮጀክቱ መስከረም 19/2012 ዓ.ም መጀመሩ የሚታወስ ሲሆን በውስጡ ሙዚየም ፣ ምክር ቤት እና 3 የመሰብሰቢያ አዳራሾች ፣ መዝገብ ቤት እና ቤተ መጻሕፍት ፣ አምፊ ቲያትር፣ ፏፏቴዎች፣ ኤግዚቢሽኖች እና የስነ ጥበብ ጋለሪን ያካተተ ነው፡፡

በአሸናፊ እንዳለ

https://t.me/ethioengineers1
1.8K viewsENG Sintayehu Melese, 11:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-27 09:23:46
በተሰማሩበት ኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪ እና ድርጅቶ ያለውን ሂሳብ አያያዝ ምን ያህል ያውቃሉ ?
Class starts on February 28/2023
+251995016195
https://t.me/BeGetEngineering
2.1K viewsBelay #1, 06:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-27 09:10:37
የቤት እድለኞች ለመዋዋል በወጣላቸው ጊዜ ሰሌዳ መሰረት ቀርበው ካልተዋዋሉ ቤቱን እንዳልፈለጉት ተቆጥሮ ለመንግስት ተመላሽ ይሆናል ተባለ።

የቤቶች ኮርፓሬሽን በ20/80 ለ14ኛ ዙር ፣ በ40/60 ለ3ኛ  ዙር የጋራ መኖሪያቤት አጣ ወጥቶላቸው  ውል እንዲዋዋሉ ከጥር 1/2015 ዓ.ም.  ጀምሮ ቦሌ ክ/ከተማ ውስጥ በሚገኘው የአንድ ማእከል አገልግሎት መስጫ በመምጣት ቅፅ 09 ወደ መኖሪያ ቀበሌዎች ወስደው አስሞልተው ለማምጣት ቀርበው የወሰዱ 23,813 ሲሆኑ የቀበሌውን ቅፅ 9 አስሞልተው በመመለስ ቅፅ 03 ወደ ባንክ ቀርበው የወሰዱት ሰዎች ብዛት 11,865 ሰዎች ሲሆኑ ከነዚህ መካከል የባንኩን ሂደት ጨርሰው ወደ አንድ ማእከል ተመልሰው እስከ የካቲት 18/2015 ዓ,ም. ድረስ ውል የተዋዋሉ 9,568 ሰዎች ሲሆኑ የባንኩን ቅፅ 03 ወስደው እስካሁን ውል ያልተዋዋሉ ደግሞ 2,297 ሰዎች ናቸው ።

ከጥር 1 እስከ የካቲት 18/2015 ዓም ድረስ አስፈላጊውን ፕሮሰስ ጨርሰው የይዞታ ማረጋገጫ ካርታ እንዲሰራላቸው የተላኩ 8,416  ሰዎች ብቻ መሆናቸውን የኮርፓሬሽኑ አስታውቀዋል ።

በሁለቱም የቤት ልማት ፕሮግራሞች ከ25,773 ሰዎች ውላቸውን ተዋውለው ካርታቸውን ሊወስዱ እንደሚገባ ካለው ቁጥር አንፃር ግን እስካሁን ውል የጨረሱት ሲታይ ገና ብዙ እንደሚጠበቅ እና ሰውጋ መዘናጋት እንደሚታይ ታውቋል።

የቤት እድለኞች በመመሪያችን መሰረት በቀረበላቸው ጥሪ መሰረት እና ለመዋዋል በወጣላቸው ጊዜ ሰሌዳ መሰረት ቀርበው ካልተዋዋሉ ቤቱን እንዳልፈለጉት ተቆጥሮ ለመንግስት ተመላሽ ስለሚሆን ባለ እድለኞች አሁንም ወደ አንድ ማእከል አገልግሎት መስጫ በመምጣት እንዲዋዋሉ ጥሪ አቅርበዋል


https://t.me/ethioengineers1
2.0K viewsENG Sintayehu Melese, 06:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-25 21:03:26
Dear Construction Industry Professionals:                                                                                                               Greetings:  
BeGet Engineering is preparing a new course in Accounting and Business Management that suits for all Construction Industry participants focusing on the important applicable points with software use and supported by Practical applications.       
For the 2 Months , here is summary of the package with our Instructor's profile (Accountant Tazebew Tsegaw and Eng. Fikru Kinfu)

Class Option 1.
Tuesday & Thursday evening,11:30-1:30
Class Option 2.
Sunday 8:00-12:00
Class starts on February 28/2023
+251995016195
https://t.me/BeGetEngineering
890 viewsENG Sintayehu Melese, 18:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ